diff --git a/19-PSA.usfm b/19-PSA.usfm new file mode 100644 index 0000000..afd600b --- /dev/null +++ b/19-PSA.usfm @@ -0,0 +1,5037 @@ +\id PSA +\ide UTF-8 +\h መጽሐፈ መዝሙር +\toc1 መጽሐፈ መዝሙር +\toc2 መጽሐፈ መዝሙር +\toc3 psa +\mt መጽሐፈ መዝሙር + +\s5 +\c 1 +\p +\v 1 በክፉዎች ምክር የማይሄድ በኃጢአተኞች መንገድ የማይቆም በፌዘኞች ወንበር የማይቀመጥ ምስጉን ነው፡፡ +\v 2 ነገር ግን ደስ የሚሰኘው በያህዌ ሕግ ነው ሕጉንም ቀንና ሌሊት ያሰላስላል፡፡ + +\s5 +\v 3 እርሱም ፍሬዋን በየወቅቱ እንደምትሰጥ፣ ቅጠሏም እንደማይጠወልግ፣ በወራጅ ውሆች እንድ ተተከለች ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል፡፡ + +\s5 +\v 4 ኃጢአተኞች ግን እንዲህ አይደሉም ነገር ግን ነፋስ ጠራርጐ እንደሚወስደው ገለባ ናቸው፡፡ +\v 5 ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ ኃጢአተኞችም በጻድቃን ጉባኤ አይቆሙም፡፡ + +\s5 +\v 6 ያህዌ የጻድቃንን አካሄድ ይጠብቃልና የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች፡፡ + +\s5 +\c 2 +\p +\v 1 አሕዛብ ለምን ያሤራሉ? ሕዝቦችስ ለምን በከንቱ ያድማሉ? +\v 2 የምድር ነገሥታት በአንድነት ተነሡ ገዦችም በአንድነት አሤሩ እንዲህ በማለትም በያህዌና በመሲሑ ላይ አሤሩ +\v 3 «እግር ብረታቸውን ከእግራችን እንቁረጥ፣ ሰንሰሰታቸውንም በጥሰን እንጣል፡፡» + +\s5 +\v 4 በሰማያት የሚቀመጥ እርሱ ያፌዝባቸዋል ጌታም ይሳለቅባቸዋል፡፡ +\v 5 ከዚያም በቁጣው ያናግራቸዋል እንዲህ በማለትም በመዐቱ ያስፈራቸዋል + +\s5 +\v 6 «እኔ ራሴ በጽዮን፣ በተቀደሰውም ተራራዬ ንጉሤን ሾምሁ፡፡» +\v 7 የያህዌን ዐዋጅ ዐውጃለሁ፡፡ እርሱም እንዲህ አለኝ፣ «አንተ ልጄ ነህ! በዚህ ቀን አባትህ ሆኛለሁ፡፡ + +\s5 +\v 8 ለምነኝ፤ አሕዛብን ለርስትህ የምድር ነገሥታትንም ለግዛትህ እሰጥሃለሁ፡፡ +\v 9 በብረት በትር ትቀጠቅጣቸዋለህ ሸክላ ሠሪው እንዳበጀው ዕቃ ታደቃቸዋለህ፡፡» + +\s5 +\v 10 ስለዚህ አሁን እናንት ነገሥታት ተጠንቀቁ እናንት የምድር ገዦች አስተውሉ፡፡ +\v 11 ያህዌን በፍርሃት አምልኩት በመንቀጥቀጥ ተገዙለት፡፡ + +\s5 +\v 12 እንዳይቆጣ በመንገድም እንዳትጠፉ ልጁን ሳሙት፡፡ ቁጣው ፈጥኖ ይነዳልና፡፡ እርሱን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ የተባረኩ ናቸው፡፡ + +\s5 +\c 3 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ጠላቶቼ ምንኛ በዙ! በእኔ ላይ የተነሡ ብዙዎች ናቸው፡፡ +\v 2 ብዙ ሰዎች፣ «እግዚአብሔር አያድነውም» እያሉ ስለ እኔ ይናገራሉ፡፡ + +\s5 +\v 3 አንተ ግን ያህዌ ሆይ፣ ዙሪያዬን እንደ ጋሻ ትከልለኛለህ፣ ክብሬንና ራሴንም ከፍ የምታደርግ አንተ ነህ፡፡ +\v 4 ድምፄን ወደ ያህዌ አነሣለሁ እርሱም ከተቀደሰው ተራራው ይመልስልኛል፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 5 በሰላም እተኛለሁ፤ እንቀላፋለሁ ያህዌ ስለ ጠበቀኝ ከእንቅልፌ ተነሣሁ፡፡ +\v 6 በየአቅጣጫው ከተነሡብኝ ሰዎች ብዛት አልፈራም፡፡ + +\s5 +\v 7 ያህዌ ሆይ ተነሥ፤ አምላኬ ሆይ አድነኝ! አንተ የጠላቶቼን መንጋጋ መታህ የክፉዎችን ጥርስ ሰበርህ፡፡ +\v 8 መዳን ከያህዌ ነው በረከትህ በሕዝብህ ላይ ይሁን፡፡ + +\s5 +\c 4 +\p +\v 1 የጽድቄ አምላክ ሆይ፣ በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ ከጭንቀቴም አሳርፈኝ ማረኝ ጸሎቴንም ስማ፡፡ + +\s5 +\v 2 እናንተ ሰዎች እስከ መቼ ክብሬን ታወርዳላችሁ? እስከ መቼ ከንቱ ነገር ትወዳላችሁ፤ ሐሰትንስ ትፈልጋላችሁ? ሴላ +\v 3 ያህዌ ጻድቁን ለራሱ እንደ ለየ ዕወቁ፡፡ በጠራሁት ጊዜ ያህዌ ይሰማኛል፡፡ + +\s5 +\v 4 የቱንም ያህል ብትፈሩ ኃጢአት አትሥሩ! በመኝታችሁ እያላችሁ በልባችሁ አሰላስሉ፤ ጸጥም በሉ፡፡ ሴላ +\v 5 ለያህዌ የጽድቅ መሥዋዕት አቅርቡ እምነታችሁንም እርሱ ላይ አድርጉ፡፡ + +\s5 +\v 6 ብዙዎች፣ «መልካሙን ማን ያሳየናል?» ይላሉ፡፡ ያህዌ ሆይ፣ የፊትህን ብርሃን እኛ ላይ አብራ፡፡ +\v 7 ብዙ እህልና ወይን ካገኙ ሰዎች ይበልጥ አንተ ልቤን በታላቅ ሐሤት ሞልተኸዋል፡፡ +\v 8 በሰላም የምታኖረኝ አንተ ብቻ ስለሆንህ በሰላም እተኛለሁ አንቀላፋለሁም፡፡ + +\s5 +\c 5 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ ወደ አንተ ስጣራ ስማኝ መቃተቴንም አስብ፡፡ +\v 2 ንጉሤና አምላኬ ወደ አንተ እጸልያለሁና የልመናዬን ጽምፅ አድምጥ +\v 3 ያህዌ ሆይ በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ በማለዳ ልመናዬን ወደ አንተ አቀርባለሁ፤ እጠባበቃለሁም፡፡ + +\s5 +\v 4 በእርግጥ አንተ በክፋት ደስ የምትሰኝ አምላክ አይደለህም ክፉ ሰዎች ከአንተ አያድሩም፡፡ +\v 5 እብሪተኛ በፊትህ አይቆምም ዐመፃን የሚያደርጉትህን ሁሉ ጠላህ፡፡ +\v 6 ሐሰተኞችን ታጠፋለህ ደም የተጠሙትን አታላዮችን ያህዌ ይጸየፋል፡፡ + +\s5 +\v 7 እኔ ግን በኪዳናዊ ታማኝነትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ፤ በአክብሮት ፍርሃትም የተቀደሰ ማደሪያህ ውስጥ እሰግዳለሁ፡፡ +\v 8 ጌታ ሆይ፣ በጠላቶች ምክንያት በጽድቅህ ምራኝ መንገድህንም በፊቴ አቅና፡፡ + +\s5 +\v 9 በአፋቸው እውነት የለም ልባቸው ተንኰለኛ ነው፡፡ ጉሮሮአቸው እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፡፡ በአንደበታቸው ይሸነግላሉ፡፡ +\v 10 እግዚአብሔር ሆይ፣ የእጃቸውን ስጣቸው ተንኰላቸው መጥፊያቸው ይሁን! አንተ ላይ ዐምፀዋልና ከኃጢአታቸው ብዛት የተነሣ አስወግዳቸው፡፡ + +\s5 +\v 11 በአንተ የተማመኑ ሁሉ ደስ ይበላቸው አንተ ከለላ ሁነሃቸዋልና ለዘላለም ሐሤት ያድርጉ፡፡ ስምህን የሚወዱ በአንተ ደስ ይበላቸው +\v 12 ያህዌ ሆይ፣ አንተ ጻድቁን ትባርካለህ እንደ ጋሻ በሞገስ ትከልላቸዋለህ፡፡ + +\s5 +\c 6 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ በቁጣህ አትገሥጸኝ በመዐትህም አትቅጣኝ፡ +\v 2 ያህዌ ሆይ፣ ደካማ ስለሆንሁ ምሕረት አድርግልኝ፡፡ አምላኬ ሆይ፣ አጥንቶቼ ተናውጠዋልና፣ ፈውሰኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 ነፍሴም ታወካለች፤ ያህዌ ሆይ፣ ይህ እስከ መቼ ይቀጥላል? +\v 4 ወደ እኔ ተመለስ፤ አድነኝም፡፡ ከታማኝ ኪዳንህ የተነሣ አድነኝ +\v 5 በሞት የሚያስታውስህ የለም መቃብር ውስጥ ሆኖ፣ የሚያመሰግንህ ማን ነው? + +\s5 +\v 6 ከመቃተቴ የተነሣ ዝዬአለሁ ሌሊቱን ሁሉ በልቅሶ አልጋዬን በእንባ አርሳለሁ መኝታዬንም በእንባ አረጥባለሁ፡፡ +\v 7 ከሐዘን የተነሣ ዐይኖቼ ፈዘዙ፤ ከባላጋራዎቼ የተነሣ ደከሙ፡፡ + +\s5 +\v 8 እናንት ዐመፃን የምታደርጉ ሁሉ ከእኔ ራቁ ያህዌ የለቅሶዬን ድምፅ ሰምቷልና +\v 9 እንዲምረኝ ወደ እርሱ ያቀረብኩትን ልመና አድምጧል፤ ያህዌ ጸሎቴን ተቀብሏል፡፡ +\v 10 ጠላቶቼ ሁሉ ይፈሩ፤ እጅግም ይታወኩ ወደ ኋላ ይመለሳሉ፤ በድንገትም ይዋረዳሉ፡፡ + +\s5 +\c 7 +\p +\v 1 ያህዌ አምላኬ ሆይ፣ አንተ መጠጊያዬ ነህ! ከሚያሳድዱኝ ሁሉ አድነኝ ታደገኝም +\v 2 አለበለዚያ እንደ አንበሳ ይዘነጣጥሉኛል የሚያድነኝ በሌለበት ሁኔታ ያደቁኛል፡፡ + +\s5 +\v 3 አምላኬ ያህዌ ሆይ፣ ጠላቶቼ አድርጓል የሚሉትን አላደረግሁም በእኔ ላይ ምንም በደል የለም፡፡ +\v 4 በጐ ለዋለልኝ ክፉ አልመለስሁም፡፡ጠላቶቼን በከንቱ አልጐዳሁም፡፡ + +\s5 +\v 5 የምናገረው እውነት ካልሆነ ጠላቴ አሳድዶ ይያዘኝ ሕይወቴን ከምድር ይቀላቅል ክብሬንም ከትቢያ ጋር ይደበልቅ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 6 ያህዌ ሆይ፣ በቁጣህ ተነሥ በጠላቶቼ ዛቻ ፍረድ አምላኬ ሆይ ንቃ ትእዛዝም አስተላልፍ፡፡ +\v 7 ሕዝቦችን ሁሉ በዙሪያህ ሰብስብ ከላይም ሆነህ ግዛቸው፡፡ + +\s5 +\v 8 ያህዌ በሕዝቦች ላይ ይፈርዳል ያህዌ ሆይ፣ እንደ ጽድቄ ፍረድልኝ ልዑል ሆይ፣ እንደ ንጽሕናዬ መልስልኝ፡፡ +\v 9 ልብንና አእምሮን የምትመረምር ጻድቅ አምላክ ሆይ፣ የክፉዎችን ዐመፅ አጥፉ፤ ጻድቃንን ግን አጽና፡፡ + +\s5 +\v 10 ጋሻዬ ልዑል እግዚአብሔር ነው፤ እርሱ ልበ ቅኖችን ያድናቸዋል፡፡ +\v 11 እግዚአብሔር ጻድቅ ዳኛ ነው፤ ቁጣውንም በየዕለቱ የሚገልጥ አምላክ ነው፡፡ + +\s5 +\v 12 ሰው በንስሐ የማይመለስ ከሆነ እግዚአብሔር ሰይፉን ይስላል፤ ለውጊያም ቀስቱን ይገትራል +\v 13 የሚገደሉ ጦር ዕቃዎቹን አዘጋጅቷል የሚንበለበሉትን ፍላጻዎቹንም አሰናድቶአል፡፡ + +\s5 +\v 14 ክፋትን ያረገዘ፣ ክፉ ዕቅዶችን የፀነሰና አጥፊ ሐሰቶችን የወለደ ሰውን አስቡ፡፡ +\v 15 ጥልቅ ጉድጓድ ይቆፍራል በቆፈረው ጉድጓድ እርሱ ይገባበታል፡፡ +\v 16 ለሌሎች ያዘጋጀው ክፉ ዕቅድ ወደ ራሱ ይመለሳል፤ ዐመፃውም በገዛ ዐናቱ ላይ ይወርዳል፡፡ + +\s5 +\v 17 ስለ ጽድቁ ያህዌን አመሰግናለሁ ለልዑል አምላክም እዘምራለሁ፡፡ + +\s5 +\c 8 +\p +\v 1 ክብርህን በላይ በሰማያት የምትገልጥ አንተ ጌታችን ያህዌ፣ ስምህ በምድር ሁሉ ምንኛ ገናና ነው፡፡ +\v 2 ከጠላትህ የተነሣ፤ ባላንጣንና ቂመኛን ጸጥ ለማሰኘት ከልጆችና ጡት ከሚጠቡ ሕፃናት አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ + +\s5 +\v 3 ጣቶችህ የሠሯቸው ሰማያትን፣ በየቦታቸው ያደርግሃቸው ጨረቃና ከዋክብትን ስመለከት +\v 4 በአሳብህ ስፍራ ትሰጠው ዘንድ ሰው ምንድነው? ትጠነቀቅለትስ ዘንድ የሰው ልጅ ምንድነው? +\v 5 ከመላእከት በጥቂት አሳነሰኸው የክብርና የሞገስ ዘውድ አቀዳጀኸው፡፡ + +\s5 +\v 6 በእጆችህ ሥራ ሁሉ ላይ ሾምኸው ሁሉንም ከእግሮቹ በታች አደረግህለት +\v 7 በጐችና በሬዎችን፣ የዱር አራዊትን፣ +\v 8 የሰማይ ወፎችን፣ የባሕር ዓሦችን ባሕር ውስጥ የሚርመሰመሱትን ሁሉ አስገዛህለት፡፡ + +\s5 +\v 9 ጌታችን ያህዌ፣ ስምህ በምድር ሁሉ ላይ ምንኛ ገነነ! + +\s5 +\c 9 +\p +\v 1 በፍጹም ልቤ ያህዌን አመሰግናለሁ ስለ ድንቅ ሥራዎችህም እናገራለሁ፡፡ +\v 2 በአንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አደርጋለሁ ልዑል ሆይ፣ ለስምህ እዘምራለሁ! + +\s5 +\v 3 ጠላቶቼ ወደ ኋላ በተመለሱ ጊዜ ተሰነካክለው በፊትህ ይጠፋሉ፡፡ +\v 4 በዙፋንህ ላይ ተቀምጠህ ጻድቅ ፈራጅ ነህ! የእኔን ጉዳይም ትፈርድልኛለህ፡፡ + +\s5 +\v 5 ሕዝቦችን ገሠጽህ ክፉዎችን አጠፋህ ስማቸውን ከዘላለም እስከ ዘላለም ደመሰስህ፡፡ +\v 6 ጠላቶች ለዘላለም ጠፍተዋል ከተሞቻቸውንም ገለባበጥሃቸው መታሰቢያቸውንም አጠፋህ፡፡ + +\s5 +\v 7 እግዚአብሔር ግን ለዘላለም ዙፋኑ ላይ ነው ዙፋኑንም ለፍርድ አጽንቶአል፡፡ +\v 8 ዓለምን በጽድቅ ይዳኛል ለሕዝቦችም በፍትሕ ይፈርዳል፡፡ + +\s5 +\v 9 ያህዌ ለተጨቆኑት ዐምባ ነው፡፡ በመከራም ጊዜ መጠጊያ ይሆናቸዋል፡፡ +\v 10 ስምህን የሚያውቁ በአንተ ይታመናሉ አንተ ያህዌ፣ የሚፈልጉህን አትተዋቸውም፡፡ + +\s5 +\v 11 በጽዮን ለሚገዛ ለያህዌ ምስጋና ዘምሩ ድንቅ ሥራውን ለሕዝቦች ተናገሩ፡፡ +\v 12 ደም ተበቃዩ አስቦአቸዋልና የጭቁኖችን ጩኸት አልዘነጋም፡፡ + +\s5 +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ ማረኝ በሚጠሉኝ የደረሰብኝን ጭቆና ተመልከት አንተ ከሞት አፋፍ ነጥቀህ አድነኝ፡፡ +\v 14 ይህን ብታደርግልኝ፣ በጽዮን አደባባይ ምስጋናህን ሁሉ ለሕዝብ እናገራለሁ በማዳንህም ደስ እሰኛለሁ! + +\s5 +\v 15 ሕዝቦች ባዘጋጁት አዘቅት ሰጠሙ እግሮቻቸውም በሰወሩት ወጥመድ ተያዙ፡፡ +\v 16 እግዚአብሔር በእውነተኛ ፍርዱ ታወቀ ክፉዎችም በእጃቸው ሥራ ተጠመዱ፡፡ + +\s5 +\v 17 ክፉዎች ተመልሰው ወደ ሲኦል ይወርዳሉ፡፡ እግዚአብሔርን የሚዘነጉ ሰዎች ሁሉ ፍጻሜ ይኸው ነው፡፡ +\v 18 ችግረኞች መቼም ቢሆን አይዘነጉም የድኾችም ተስፋ ከንቱ ሆኖ አይቀርም፡፡ + +\s5 +\v 19 ያህዌ ሆይ ተነሥ፣ ሰውም አያይል ሕዝቦችም በፊት ይፈረድባቸው፡፡ +\v 20 ያህዌ ሆይ፣ አስደንግጣቸው ሕዝቦች ሰዎች ብቻ መሆናቸውን ይወቁ፡፡ ሴላ + +\s5 +\c 10 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ለምን ርቀህ ቆምህ? በመከራ ጊዜ ለምን ራስህን ሰወርህ? +\v 2 በእብሪት ተነሳሥተው ክፉዎች ጭቁኖችን ያሳድዳሉ እባክህ ክፉዎች ባጠመዱት ወጥመድ ይጠመዱ፡፡ +\v 3 ክፉ ሰው በልቡ ምኞት ይኩራራል ስግብግቡን ይባርካል፤ ያህዌን ይሰድባል፡፡ + +\s5 +\v 4 ክፉ ሰው በራሱ ይመካል፤ እግዚአብሔርንም አይፈልግም፡፡ ስለ እርሱ ምንም ደንታ ስለሌለው ስለ እግዚአብሔር አያስብም፡፡ +\v 5 ነገሩ ዘወትር ለእርሱ የተሳካ ነው የእግዚአብሔርን ፍርድ ግን ሊረዳ አይችልም፡፡ በጠላቶቹ ላይ ይሳለቃል፡፡ + +\s5 +\v 6 በልቡም፣ «በፍጹም አልወድቅም ከትውልድ እስከ ትውልድ መከራ አያገኘኝም» ይላል፡፡ +\v 7 አፉ መርገምን፣ ሸፍጥንና ግፍን የተሞላ ነው፤ በምላሱ ይጐዳል፤ ይገድላልም፡፡ + +\s5 +\v 8 መንደሮች አጠገብ አድፍጦ ይጠብቃል በሰዋራ ቦታ ንጹሐንን ይገድላል ዐይኖቹም ምስኪኖች ላይ ያነጣጥራሉ፡፡ +\v 9 ደን ውስጥ እንዳለ አንበሳ በስውር ያደባል ረዳት የሌለውን ለመያዝ ያሸምቃል፡፡ መረቡን ዘርግቶ ጭቁኖችን ያጠምዳል፡፡ +\v 10 እርሱ መትቶ ይጥላቸዋል፤ ረዳት የሌላቸው ደካሞች ምስኪኖችም የእርሱ ሰለባ ሆነው ይወድቃሉ፡፡ + +\s5 +\v 11 በልቡም፣ «እግዚአብሔር ረስቶአል እንዳያይም ፊቱን ሸፍኖአል» ይላል፡፡ +\v 12 ያህዌ ሆይ፣ ተነሥ! አምላክ ሆይ ኃያል ክንድህ ይነሣ! የተጨቆኑትን ችላ አትበላቸው፡፡ + +\s5 +\v 13 ክፉ ሰው ለምን እግዚአብሔርን ይንቃል? በልቡም ለምን፣ «እግዚአብሔር አይቀጣኝም» ይላል? +\v 14 አንተ ግን መከራንና ሐዘንን ታያለህ ምስኪኑም ራሱን በአንተ ላይ ይጥላል፤ ለድኻ አደጉም አንተ ረዳቱ ነህ፡፡ + +\s5 +\v 15 የክፉና የበደለኛውን ክንድ ስበር አንተ እንደማታገኘው አስቦ ነበር የእጁንም ሰጠው፡፡ +\v 16 ያህዌ ከዘላለም እስከ ዘላለም ንጉሥ ነው ሕዝቦችም ከምድሩ ይወገዳሉ፡፡ + +\s5 +\v 17 ያህዌ የጭቁኖቹን ጩኸት ሰምቷል ልባቸውን ታበረታለህ፤ ጸሎታቸውንም ትሰማለህ +\v 18 ከእንግዲህ ማንም በምድር ላይ ሽብር እንዳያደርግ አንተ አባት ለሌላቸውና ለጭቁኖች መከታ ሆንህላቸው፡፡ + +\s5 +\c 11 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ አንተን መጠጊያ አደረግሁ ታዲያ፣ ነፍሴ፣ «እንደ ወፍ ወደ ተራሮች ብረሪ» እንዴት ትሏታላችሁ? +\v 2 ደግሞም ለምን እንዲህ ትሉኛላችሁ? ልበ ቅኖችን በጨለማ ለመግደል ክፉዎች ቀስታቸውን ገትረዋል፤ ፍላጻቸውንም በአውታሩ ላይ ደግነዋል፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ አንተን መጠጊያ አደረግሁ ታዲያ፣ ነፍሴ፣ «እንደ ወፍ ወደ ተራሮች ብረሪ» እንዴት ትሏታላችሁ? ደግሞም ለምን እንዲህ ትሉኛላችሁ? +\v 4 ልበ ቅኖችን በጨለማ ለመግደል ክፉዎች ቀስታቸውን ገትረዋል፤ ፍላጻቸውንም በአውታሩ ላይ ደግነዋል፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ ጻድቁንና ኃጢአተኛውን ይመለከታል ዐመፅን ማድረግ የሚወዱትን ግን ይጠላቸዋል፡፡ +\v 6 እርሱ በክፉዎች ላይ የእሳት ፍምና ዲን ያዘንባል፤ የሚለበልብ ዐውሎ ነፋስም የእነርሱ ዕጣ ፈንታ ነው፡፡ +\v 7 ያህዌ ጻድቅ ስለ ሆነ የጽድቅን ሥራ ይወዳል፤ ቅኖችም ፊቱን ያያሉ፡፡ + +\s5 +\c 12 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ደግ ሰው የለምና አንተው እርዳኝ ከሰው ዘር መካከል አንድ ታማኝ አይገኝም፡፡ + +\s5 +\v 2 እያንዳንዱ ሰው ለባልንጀራው ባዶ ቃላት ይናገራል በሽንገላ ከንፈርና በሁለት ልብ ይናገራል፡፡ +\v 3 ሸንጋይ ከናፍርቶችንና በትምክህት የሚናገሩ አንደበቶችን ያህዌ ያጥፋ፡፡ +\v 4 እነዚህም፣ «በአንደበታችን እንበረታለን የምንናገረውንስ ማን ማስተባበል ይችላል?» የሚሉ ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 5 «ስለ ድኾች መከራ፣ ስለ ችግረኞች ጩኸት ያህዌ አሁን እነሣለሁ፤ የናፈቁትንም ሰላም እሰጣቸዋለሁ» ይላል፡፡ + +\s5 +\v 6 የያህዌ ቃሎች የነጹ ቃሎች ናቸው በእሳት ምድጃ ሰባት ጊዜ እንደ ነጠረ ብር የጠሩ ናቸው፡፡ +\v 7 ያህዌ ሆይ፣ አንተ ትጠብቀናለህ ከዚህ ዐመፀኛ ትውልድ ለዘላለም ጻድቃንን ትጠብቃለህ፡፡ +\v 8 በሰው ልጆች መካከል ክፋት በገነነበት ጊዜ ዐመፀኞች እንዳሻቸው በየቦታው ይዘራሉ፡፡ + +\s5 +\c 13 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ እስከ መቼ ድረስ ለዘላለሙ ትረሳኛለህ? ፊትህን ከእኔ የምትሰውረውስ እስከመቼ ድረስ ነው? +\v 2 በስጋት የምኖረው ልቤስ ቀኑን ሙሉ የሚያዝነው እስከ መቼ ነው? ጠላቴ እኔ ላይ የሚያይለው እስከ መቼ ነው? + +\s5 +\v 3 ያህዌ አምላኬ ሆይ፣ ወደ እኔ ተመልከት መልስልኝም! +\v 4 የሞት እንቅልፍ እንዳይወስደኝ ዐይኖቼን አብራ፡፡ ጠላቴ፣ «አሸነፍሁት» እንዳይል ባላጋራዎቼም በውድቀቴ ደስ እንዳይላቸው ርዳኝ፡፡ + +\s5 +\v 5 እኔ ግን ወሰን በሌለው ፍቅርህ እተማመናለሁ ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል፡፡ +\v 6 ቸርነቱ በዝቶልኛልና ለያህዌ እዘምራለሁ፡፡ + +\s5 +\c 14 +\p +\v 1 ሞኝ በልቡ፣ «እግዚአብሔር የለም» ይላል፡፡ ብልሹዎች ናቸው፤ አስጸያፊ ተግባርም ይፈጽማሉ፡፡ መልካም የሚያደርግ አንድም የለም፡፡ + +\s5 +\v 2 የሚያስተውል፣ እርሱንም የሚፈልግ መኖሩን ለማየት ያህዌ ከሰማይ ወደ ምድር ተመለከተ፡፡ +\v 3 ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤ ሁሉም ብልሹዎች ሆነዋል ከእነርሱ አንድ እንኳ መልካም የሚያደርግ የለም፡፡ + +\s5 +\v 4 እነዚያ ዐመፃ የሚያደርጉ ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉ፣ የያህዌን ስም የማይጠሩ ሰዎች ዕውቀት የላቸውምን? + +\s5 +\v 5 እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና እነርሱ በፍርሃት ተርበደበዱ! +\v 6 ምንም እንኳ ያህዌ መጠጊያው ቢሆንም እናንተ ግን ድኻውን ማዋረድ ትፈልጋላችሁ፡፡ + +\s5 +\v 7 ያህዌ ሕዝቡን ከምርኮ ሲመለስ ለእስራኤል መዳን ከጽዮን ይመጣል ያኔ ያዕቆብ ደስ ይለዋል እስራኤልም ሐሤት ያደርጋል፡፡ + +\s5 +\c 15 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ በድንኳንህ ውስጥ የሚያድር ማን ነው? በተቀደሰው ኮረብታህስ የሚኖር ማን ነው? +\v 2 አካሄዱ ንጹሕ የሆነ፣ ጽድቅን የሚያደርግ ከልቡ እውነትን የሚናገር፤ + +\s5 +\v 3 በአንደበቱ የማይሸነግል ሌሎች ሰዎችን የማይጐዳ፤ በጐረቤቱ ላይ አሉባልታ የማያሰራጭ + +\s5 +\v 4 ነውረኛውን የሚንቅ፣ ያህዌን የሚፈሩትን ግን የሚያከብር፡፡ ዋጋ ቢያስከፍለው እንኳ የገባውን ቃል የሚፈጽም +\v 5 ገንዘቡን በወለድ የማያበድር ንጹሕ ሰው ላይ ለመመስከር ጉቦ የማይበላ፤ እነዚህን የሚያደርግ ከቶውንም አይናወጥም፡፡ + +\s5 +\c 16 +\p +\v 1 በአንተ ተማምኛለሁና ያህዌ ሆይ ጠብቀኝ፡፡ +\v 2 ያህዌን፣ «አንተ ጌታዬ ነህ፤ ከአንተ ውጪ መልካም ነገር የለኝም» አልሁት፡፡ +\v 3 በምድር የሚኖሩ ቅዱሳን የተከበሩ ናቸው፤ በእነርሱም ደስ ይለኛል፡፡ + +\s5 +\v 4 ሌሎች አማልክትን የሚከተሉ መከራቸው ይበዛል እኔ ግን ለአማልክቶቻቸው የደም ቁርባን አላፈስም፤ ስማቸውንም በአፌ አልጠራም፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ የርስት ድርሻዬና ጽዋዬ ነው፤ ፍጻሜዬም በአንተ እጅ ነው፡፡ +\v 6 መለኪያ ገመድ ባማረ ስፍራ ተጥሎልኛል በእርግጥም የተዋበች ርስት አግኝቻለሁ፡፡ + +\s5 +\v 7 የሚመክረኝን ያህዌን እባርካለሁ፤ ሌሊት እንኳ ልቦናዬ ያስተምረኛል፡፡ +\v 8 ሁልጊዜ እግዚአብሔርን አስቀድማለሁ፤ እርሱ በቀኜ ስለሆነ አልናወጥም! + +\s5 +\v 9 ስለዚህ ልቤን ደስ አለው፤ ክብሬም ሐሤት አደረገ፡፡ በእርግጥ ያለ ስጋት እኖራለሁ፡፡ +\v 10 ምክንያቱም አንተ ነፍሴን በሲኦል አትተዋትም ታማኝህ መበስበስ እንዲደርስበት አታደርግም፡፡ + +\s5 +\v 11 የሕይወትን መንገድ ታሳየኛለህ በአንተ ዘንድ የደስታ ሙላት፣ በቀኝህም የዘላለም ፍስሐ አለ፡፡ + +\s5 +\c 17 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ትክክለኛ ፍርድ ለማግኘት የማቀርበውን ጸሎት ስማ ጩኸቴንም አድምጥ፡፡ ከሐሰተኛ ከንፈር ያልወጣውን ጸሎቴን አድምጥ፡፡ +\v 2 ጽድቄ ከአንተ ዘንድ ይምጣ፤ ዐይኖችህም ፍትሕን ይመልከቱ፡፡ + +\s5 +\v 3 ልቤን ብትመረምር፣ በሌሊትም ብትጐበኘኝ፣ ብትፈትነኝም ከእኔ ዘንድ ክፋት አታገኝም፤ አንደበቴም አይስትም፡፡ + +\s5 +\v 4 የሰው ልጆችን ተግባር በተመለከተ አንተ በተናገርኸው ቃል መሠረት ከዐመፀኞች መንገድ ራሴን ጠብቄአለሁ፡፡ +\v 5 አረማመዱ በመንገድህ ጸንቶአል እግሮቼም አልተንሸራተቱም፡፡ + +\s5 +\v 6 ያህዌ ሆይ፣ ስለምትመልስልኝ ወደ አንተ እጣራለሁ፤ ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል፤ ጸሎቴንም ስማ፡፡ +\v 7 የሚተማመኑብህን በቀኝህ ከጠላቶቻቸው የምታድናቸው አንተ ታማኝትህን ድንቅ አድርገህ ግለጠው፡፡ + +\s5 +\v 8 እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤ በክንፎችህ ጥላ ሥር ሰውረኝ፡፡ +\v 9 ከሚያስጨንቁኝ፣ ከከበቡኝም አደገኛ ጠላቶቼ ጋርደኝ፡፡ +\v 10 እነርሱ ማንንም አይምሩም፤ አንደበታቸው ትዕቢትን ይናገራል፡፡ + +\s5 +\v 11 ጠላቶቼ አስጨነቁኝ፤ ከበባም አደረጉብኝ መሬት ላይ ሊዘርሩኝም አፈጠጡብኝ፡፡ +\v 12 እነርሱ ለንጥቂያ እንደሚጓጓ፣ አድፍጦም እንደሚጠብቅ ደቦል አንበሳ ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ ተነሣና አጥቃቸው፤ በአፍጢማቸው ድፋቸው! በሰይፍህ ከክፉዎች አድነኝ፡፡ +\v 14 ያህዌ ሆይ፣ እንዲህ ካሉ ሰዎች፣ ብልጽግናቸው በዚህ ሕይወት ብቻ ከሆነ ከዚህ ዓለም ሰዎች በቀኝህ አድነኝ፡፡ የአንተ የሆነ ሰዎችን ሆድ በመልካም ነገር ትሞላለህ እነርሱም ብዙ ልጆች ይኖሩዋቸዋል፤ ሀብታቸውንም ለልጆቻቸው ያወርሳሉ፡፡ + +\s5 +\v 15 እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ ስነቃም ክብርህን ዐይቼ እረካለሁ፡፡ + +\s5 +\c 18 +\p +\v 1 ጉልበት የሆንኸኝ ያህዌ እወድሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 2 ያህዌ ዐለቴ፣ መጠጊያዬና ታዳጊዬ ነው፡፡ እርሱ አምላኬ የምሸሸግበት ዐለቴ፣ ጋሻዬ፣ የድነቴ ቀንድና ዐምባዬ ነው፡፡ +\v 3 ምስጋና የሚገባውን ያህዌን እጠራለሁ፤ ከጠላቶቼም እድናለሁ፡፡ + +\s5 +\v 4 የሞት ገመድ አነቀኝ፤ የጥፋት ጐርፍም አጥለቀለቀኝ፡፡ +\v 5 የሲኦል ማሰሪያ ተጠመጠመብኝ የሞት ወጥመድም ተጠመደብኝ፡፡ + +\s5 +\v 6 በጨነቀኝ ጊዜ ያህዌን ጠራሁት፤ እንዲረዳኝም ወደ አምላኬ ጮኽሁ፤ ከመቅደሱ ድምፄን ሰማ፤ ጩኸቴም ከፊቱ ደረሰ፤ ወደ ጆሮውም ገባ፡፡ + +\s5 +\v 7 ምድር ተንቀጠቀጠች ተናወጠችም፤ የተራሮችም መሠረት ተናጋ፤ ጌታ እግዚአብሔር ተቆጥቶአልና ተንቀጠቀጡ፡፡ +\v 8 ከአፍንጫው ጢስ፣ ከአፉም የሚባላ እሳት ወጣ፤ የፍም ነበልባል ከእርሱ ፈለቀ፡፡ + +\s5 +\v 9 ሰማያትን ከፍቶ ወረደ፤ ከእግሮቹም በታች ድቅድቅ ጨለማ ነበረ፡፡ +\v 10 በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ፤ በነፋስም ክንፍ መጠቀ፡፡ + +\s5 +\v 11 ጨለማን እንደ ድንኳን፣ ዝናብ አዘል ጥቁር ደመናን በዙሪያው አደረገ፡፡ +\v 12 በፊቱ ካለው መብረቅ የተነሣ የበረዶ ድንጋይና የእሳት ፍም ወጣ፡፡ + +\s5 +\v 13 ያህዌ ከሰማያት አንጐደጐደ! የልዑልም ድምፅ አስተጋባ፡፡ +\v 14 ቀስቱን አስፈንጥሮ ጠላቶቹን በተናቸው፤ መብረቅ አዥጐድጉዶ አሳደዳቸው፡፡ + +\s5 +\v 15 ያህዌ ሆይ፣ ከቁጣህ የተነሣ፣ ከአፍንጫህም እስትንፋስ የተነሣ፣ የባሕር ወለል ታዬ የዓለምም መሠረት ተገለጠ፡፡ + +\s5 +\v 16 ከላይ እጁን ዘርግቶ ያዘኝ፤ ከጥልቅ ውሃም ስቦ አወጣኝ፡፡ +\v 17 ከኃያላን ጠላቶቼ፣ ከሚጠሉኝ ከዐቅሜ በላይ ከሆኑ ባላንጣዎቼ ታደገኝ፡፡ + +\s5 +\v 18 በመከራዬ ቀን መጡብኝ፤ ያህዌ ግን ድጋፍ ሆነኝ፡፡ +\v 19 በጣም ሰፊ ወደ ሆነ ቦታ አወጣኝ፤ ወዶኛልና አዳነኝ፡፡ + +\s5 +\v 20 ያህዌ እንደ ጽድቄ ከፍሎኛል፤ እጆቼ ንጹሕ ስለ ነበሩ ታድጐኛል፡፡ +\v 21 የያህዌን መንገድ ጠብቄአለሁና፤ በዐመፅ ተነሣሥቼ ከእርሱ ዘወር አላልሁም፡፡ + +\s5 +\v 22 ሕጐቹ ሁሉ በፊቴ ናቸው፤ ሥርዐቱንም ከፊቴ አላራቅሁም፡፡ +\v 23 በእርሱ ፊት ንጹሕ ነበርሁ፤ ከኃጢአትም ራሴን ጠብቄአለሁ፡፡ +\v 24 ያህዌ እንደ ጽድቄ መጠን፤ በዐይኖቹ ፊት ንጹሕ እንደ ነበሩት እጆቼ መጠን ከፍሎኛል፡፡ + +\s5 +\v 25 አንተ ታማኝ ለሆኑት ታማኝ ነህ እውነተኞች ለሆኑት እውነተኛ ነህ +\v 26 ለንጹሖች ንጹሕ ነህ፡፡ ለጠማሞች ግን ጠማማ ትሆንባቸዋለህ፡፡ + +\s5 +\v 27 አንተ ትሑታንን ታድናለህ ትዕቢተኛውን ዐይን ግን ታዋርዳለህ፡፡ +\v 28 አንተ መብራቴን ታበራለህ፤ አምላኬ ያህዌ ጨለማዬን ብርሃን ታደርገዋለህ፡፡ +\v 29 በአንተ ጉልበት በሰራዊት እረማመዳለሁ፤ በአምላኬም ኃይል ቅጥሩን እዘላለሁ፡፡ + +\s5 +\v 30 የእግዚአብሔር መንገድ ፍጹም ነው፤ የያህዌ ቃል የነጠረ ነው። መጠጊያ ለሚያደርጉት ሁሉ እርሱ ጋሻ ነው። +\v 31 ከእግዚአብሔር በቀር ማን አምላክ አለ? ከአምላካችንስ በቀር ዐምባ ማን ነው? +\v 32 ኅይልን የሚያስታጥቀኝ፣ መንገዴንም የሚያቃና እግዚአብሔር ነው። + +\s5 +\v 33 እርሱ እግሮቼን እንደ ብሖር እግሮች ያጠነክራል፣ በከፍታዎችም ላይ ያቆመኛል፡፡ +\v 34 እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናቸዋል የናስ ቀስቶች መሳብ እንዲችሉ ክንዶቼን ያበረታል፡፡ + +\s5 +\v 35 የማዳን ጋሻህን ሰጠኸኝ፤ ቀኝ እጅህ ደግፎኛል፤ ሞገስህም ታላቅ አድርጐኛል፡፡ +\v 36 እግሮቼ እንዳይንሸራተቱ ከበታቼ ያለውን ቦታ አሰፋህልኝ፡፡ + +\s5 +\v 37 ጠላቶቼን አሳድጄ እይዛቸዋለሁ፤ እስኪጠፉ ድረስ ወደ ኃላ አልልም፡፡ +\v 38 እንዳያንሰራሩ አድርጌ አደቀቅኋቸው ከእግሬም ሥር ወደቁ፡፡ +\v 39 አንተ ለጦርነት ኃይልን አስታጠቅኸኝ፤ በእኔ ላይ የተነሡትንም ከበታቼ አደረግህልኝ፡፡ + +\s5 +\v 40 ጠላቴቼ ወደ ኋላ እንዲሸሹ አደረግህ የሚጠሉኝንም አጠፋኋቸው፡፡ +\v 41 ለእርዳታ ጮኹ፤ ግን ማንም አላዳናቸውም ወደ ያህዌ ጮኹ፤ እርሱ ግን አልመለሰላቸውም፡፡ +\v 42 ነፋስ ጠርጐ እንደሚወስደው ትቢያ አደቀቅኋቸው መንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ ረጋገጥኋቸው፡፡ + +\s5 +\v 43 ከሕዝብ ክርክር ታደገኸኝ፤ መንግሥታት ላይ መሪ አደረግኸኝ፤ የማላውቀውም ሕዝብ ያገለግለኛል፡፡ +\v 44 ዝናዬን እንደ ሰሙ ታዘዙልኝ፤ ባዕዳንም በፊቴ ራሳቸውን ዝቅ አደረጉ፡፡ +\v 45 ባዕዳን በፍርሃት ተዋጡ እየተንቀጠቀጡም ከምሽጋቸው ወጥተው መጡ፡፡ + +\s5 +\v 46 ያህዌ ሕያው ነው፤ ዐለት የሆነልኝ ይባረክ የድነቴ አምላክ ከፍ ከፍ ይበል፡፡ +\v 47 እርሱ ጠላቶቼን ይበቀልልኛል፤ ሕዝቦችን ከእግሬ ሥር የሚያስገዛልኝም እርሱ ነው፡፡ + +\s5 +\v 48 ከጠላቶቼም የሚታደገኝ እርሱ ነው! በእርግጥም አንተ ከተነሡብኝ በላይ ከፍ አደረግኸኝ! ከጨካኞችም አዳንኸኝ፡፡ +\v 49 ያህዌ ሆይ፣ ስለዚህ ለአንተ ውዳሴ እሰጣለሁ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤ ለስምህም እዘምራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 50 እግዚአብሔር ለንጉሡ ታላቅ ድል ይሰጠዋል ለቀባው ለዳዊትና ለዘሮቹም ለዘላለም ታማኝነቱን ይገልጣል፡፡ + +\s5 +\c 19 +\p +\v 1 ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤ የሰማይ ጠፈርም የእጁን ሥራ ያውጃል። +\v 2 አንዱ ቀን ለሌላው ቀን ቃል ይናገራል፤ አንዱም ሌሊት ለሌላው ሌሊት ዕውቀትን ይገልጣል፡፡ +\v 3 ንግግር የለም፤ ቃልም የለም፤ ድምፃቸውም አልተሰማም፡፡ + +\s5 +\v 4 ያም ሆኖ ቃላቸው ወደ ምድር ሁሉ ወጣ፣ ንግግራቸውም ወደ ዓለም ዳርቻ ወጣ፡፡ በመካከላቸውም ለፀሐይ ድንኳኑን ተከለ +\v 5 ፀሐይ ከእልፍኙ እንደሚወጣ ሙሽራ ይወጣል ወደ ግቡም እንደሚሮጥ ብርቱ ሰው ደስ ይለዋል፡፡ +\v 6 ፀሐይ ከአንዱ አድማስ ሰማይን አቋርጦ ወደ ሌላው አድማስ ይወጣል፤ ከሙቀቱም የሚሰወር የለም፡፡ + +\s5 +\v 7 የያህዌ ሕግ ፍጹም ነው፤ ነፍስን መልሶ ያለመልማል፤ የያህዌ ምስክር የታመነ ነው፤ ዐላዋቂውን ጥበበኛ ያደርጋል። +\v 8 የያህዌ ሕግ ትክክል ነው፤ ልብን ደስ ያሰኛል፡፡ የያህዌ ትእዛዝ ንጹሕ ነው፤ ዐይንንም ያበራል፡፡ + +\s5 +\v 9 ያህዌን መፍራት ንጹሕ ነው፤ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል፡፡ የያህዌ ፍርድ የታመነ ነው፤ ሁለንተናውም ጽድቅ ነው፡፡ +\v 10 ከወርቅ ይልቅ የከበረ፤ እጅግ ከጠራ ወርቅም የበለጠ ነው፡፡ ከማር ይልቅ ይጣፍጣል፤ ከማር ወለላም ይበልጥ ይጥማል፡፡ + +\s5 +\v 11 እንዲሁም አገልጋይህ በእርሱ ይመከራል፤ ሕግህን በመጠበቁም ወሮታ አለው፡፡ +\v 12 ስሕተቱን ሁሉ ማን ማስተዋል ይችላል? ከተሰወረ ኃጢአት አንጻኝ፡፡ + +\s5 +\v 13 ባርያህን ከድፍረት ኃጢአት ጠብቅ ያኔ ፍጹም እሆናለሁ ከታላቅ በደልም እነጻለሁ፡፡ +\v 14 ዐለቴና አዳኜ ያህዌ ሆይ፣ የአፌ ቃልና የልቤም ሐሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን፡፡ + +\s5 +\c 20 +\p +\v 1 በመከራ ቀን ያህዌ ይስማህ የያዕቆብም አምላክ ይጠብቅህ፡፡ +\v 2 ከመቅደሱ ረድኤት ይላክልህ ከጽዮንም ደግፎ ይያዝህ + +\s5 +\v 3 መባህን ሁሉ ያስብልህ የሚቃጠል መሥዋዕትህን ይቀበልልህ፡፡ +\v 4 የልብህን መሻት ይስጥህ ዕቅድህንም ሁሉ ያሳካልህ፡፡ + +\s5 +\v 5 በአንተ ደስ ይለናል በአምላካችንም ስም ዐርማችን ከፍ ከፍ እናደርጋለን፡፡ ያህዌ የለመንኸውን ሁሉ ይፈጽምልህ፡፡ +\v 6 ያህዌ የቀባውን እንደሚያድን አሁን ዐወቅሁ፤ ማዳን በሚችለው ቀኝ እጁ ከተቀደሰው ሰማይ ይመልስለታል፡፡ + +\s5 +\v 7 አንዳንዶች በሰረገላ ሌሎች በፈረስ ይታመናሉ እኛ ግን የያህዌን ስም እንጠራለን፡፡ +\v 8 እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ እኛ ግን ተነሣን፤ ቀጥ ብለንም ቆምን! + +\s5 +\v 9 ያህዌ ሆይ፣ ንጉሡን አድን ስንጠራህ እኛንም ሰማን፡፡ + +\s5 +\c 21 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ንጉሥ በኃይልህ ደስ ይለዋል! በምትሰጠውም ድል እጅግ ሐሤት ያደርጋል፡፡ +\v 2 የልቡን መሻት ሰጠኸው፤ የለመንህንም አልከለከልኸውም፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 3 ብዙ በረከት ሰጠኸው፤ በራሱ ላይ የንጹሕ ወርቅ ዘውድ አደረግህለት፡፡ +\v 4 ሕይወትን ለመነህ አንተም ረጅም ዘመንን ለዘላለም ሰጠኸው + +\s5 +\v 5 ከሰጠኸው ድል የተነሣ ክብሩ እጅግ በዛ ክብርንና ሞገስንም አጐናጸፍኸው፡፡ +\v 6 ዘላለማዊ በረከት ሰጠኸው በፊትህ ባለው ፍስሐም ደስ አሰኘኸው፡፡ + +\s5 +\v 7 ንጉሡ በያህዌ ተማምኖአልና ከልዑል ታማኝነት የተነሣ ከቶውንም አይናወጥም፡፡ +\v 8 እጅህ ጠላቶችህን ትይዛቸዋለች ቀኝ እጅህም የሚጠሉህን ሁሉ ታገኛቸዋለች፡፡ + +\s5 +\v 9 በቁጣህ ቀን እሳት በሚንቀለቀልበት ምድጃ ታቃጥላቸዋለህ፤ ያህዌ በመዓቱ ይፈጃቸዋል፤ እሳትም ይበላቸዋል፡፡ +\v 10 ትውልዳቸውን ከምድር ላይ ታጠፋለህ ዘራቸውንም ከሰዎች መካከል ለይተህ ትደመስሳለህ፡፡ + +\s5 +\v 11 በአንተ ላይ ክፋት ቢያስቡም፣ ሤራ ቢያውጠነጥኑም፣ አይሳካላቸውም፡፡ +\v 12 በመጡበት ትመልሳቸዋለህና ቀስትህንም በእነርሱ ላይ ታነጣጥራለህ፡፡ + +\s5 +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ በብርታትህ ከፍ ከፍ በል እኛም ኃይልህን እንዘምራለን፤ እንወድሳለንም፡፡ + +\s5 +\c 22 +\p +\v 1 አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? እኔን ለማዳን፣ ከመቃተቴም ቃል ለምን ራቅህ? +\v 2 አምላኬ ሆይ፣ በቀን ወደ አንተ እጮኻለሁ፣ አንተ ግን አልመለሰህልኝም በሌሊት እንኳ አላረፍሁም፡፡ + +\s5 +\v 3 አንተ ቅዱስ ነህ በእስራኤል ምስጋና ውስጥ እንደ ንጉሥ ትቀመጣለህ፡፡ +\v 4 አባቶቻችን በአንተ ተማመኑ፣ በአንተ ተማመኑ አንተም ታደግሃቸው፡፡ +\v 5 ወደ አንተ ጮኹ፤ እነርሱም ዳኑ በአንተ ተማመኑ፤ እነርሱም አላፈሩም፡፡ + +\s5 +\v 6 እኔ ግን ትል እንጂ፣ ሰው አይደለሁም ለሰዎች ማላገጫ፣ በሕዝብም ዘንድ የተናቅሁ ነኝ፡፡ +\v 7 የሚያዩኝ ሁሉ ይሣለቁብኛል ራሳቸውንም እየነቀነቁ ያፌዙብኛል፡፡ +\v 8 «በያህዌ ተማምኖአል፤ ያህዌ ያድነው፤ በእርሱ ደስ ተሰኝቶበታልና እስቲ ይታደገው» ይላሉ፡፡ + +\s5 +\v 9 አንተ ከእናቴ ማሕፀን አወጣኸኝ በእናቴም ጡት ሳለሁ በአንተ እንድታመን አደረግኸኝ፡፡ +\v 10 ከማሕፀን ጀምሮ በአንተ ተጣልሁ በእናቴ ማሕፀን ከነበርኩበት ጊዜ ጀምሮ አንተ አምላኬ ነህ! + +\s5 +\v 11 መከራ እየተቃረበ ነው የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ፡፡ +\v 12 ብዙ ኮርማዎች ከበቡኝ ኃይለኛ የባሳን ኮርማዎች ዙሪያዬን ቆመዋል፡፡ +\v 13 እንደሚያገሣና እንደሚቦጫጭቅ አንበሳ አፋቸውን ከፈቱብኝ፡፡ + +\s5 +\v 14 እንደ ውሃ ፈሰሰሁ አጥንቶቼም ሁሉ ከመጋጠሚያቸው ወለቁ ልቤ እንደ ሰም ሆነ በውስጤም ቀጠለ፡፡ +\v 15 ጉልበቴ እንደ ሸክላ ደረቀ ምላሴም ከላንቃዬ ጋር ተጣበቀ፡፡ እንደ ሞተ ሰው ትቢያ ላይ አደረግኸኝ፡፡ + +\s5 +\v 16 ውሾች ከበቡኝ የክፉዎች ስብስብ በዙሪያዬ ሰፈሩ፤ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩ +\v 17 ዐጥንቶቼን ሁሉ አንድ አንድ መቁጠር እችላለሁ እነርሱም አፍጥጠው ይመለከቱኛል፡፡ + +\s5 +\v 18 ልብሶቼን ተከፋፈሉ በእጄ ጠባቤም ዕጣ ተጣጣሉ፡፡ +\v 19 ያህዌ ሆይ፣ ከእኔ አትራቅ ብርታቴ ሆይ፣ እባክህ እኔን ለመርዳት ፍጠን! + +\s5 +\v 20 ነፍሴን ከሰይፍ ታደጋት ውድ ሕይወቴንም ከክፉ ውሾች አድናት፡፡ +\v 21 ከአንበሳ አፍ አድነኝ፣ ከተዋጊ ጐሽ ቀንዶችም ታደገኝ፡፡ + +\s5 +\v 22 ስምህን ለወንድሞቼ እናገራለሁ፤ በጉባኤም መካከል አመሰግንሃለሁ፡፡ +\v 23 እናንት ያህዌን የምትፈሩ አመስግኑት፡፡ እናንት የያዕቆብ ዘሮች ሁሉ አክብሩት! እናንት የእስራኤል ልጆች ሁሉ እርሱን ፍሩት! + +\s5 +\v 24 ጭንቀት የደረሰበትን ሰው አልናቀም፤ መከራ ላይ ያለውን አልተጸየፈም፤ ነገር ግን የድረሱልኝ ጩኸቱን ሰማው፡፡ +\v 25 ስለ ሠራኸው መልካም ሥራ፣ ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበት ስፍራ አመሰግንሃለሁ፤ በሚፈሩህ ሰዎችም ፊት ስእለቴን እፈጽማለሁ፡፡ + +\s5 +\v 26 ችግረኞች ይበላሉ፤ ይጠግባሉም ያህዌን የሚፈልጉም ያመሰግኑታል፡፡ ልባችሁ ለዘላለም ሕያው ይሁን፡፡ +\v 27 የምድር ሕዝቦች ሁሉ ያስታውሳሉ ወደ ያህዌም ይመለሳሉ፤ የምድር ወገኖች ሁሉ በፊትህ ወድቀው ይሰግዳሉ፡፡ + +\s5 +\v 28 መንግሥት የያህዌ ነውና ሕዝቦችንም የሚገዛ እርሱ ነው፡፡ +\v 29 የምድር ከበርቴዎች ሁሉ ይበላሉ፤ እርሱንም ያመልካሉ በሕይወት ማቆየት የማይችሉ ወደ አፈር ተመላሽ የሆኑ ሰዎች ሁሉ በፊቱ ይንበረከካሉ፡፡ + +\s5 +\v 30 የሚመጣው ትውልድ ያገለግለዋል ለቀጣዩ ትውልድም ስለ ጌታ ይነግረዋል +\v 31 የጽድቅ ሥራውን በማወጅ ገና ላልተወለደ ሕዝብ ጽድቁን፣ እርሱ ያደረገውንም ይነግራሉ፡፡ + +\s5 +\c 23 +\p +\v 1 ያህዌ እረኛዬ ነው፤ ምንም አላጣም፡፡ +\v 2 በለመለመ መስክ ያሳድረኛል ፀጥ ባለ ውሃ ዘንድ ይመራኛል፡፡ + +\s5 +\v 3 ነፍሴን ይመልሳታል፤ ያድሳታል፡፡ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ ይመራኛል፡፡ + +\s5 +\v 4 በጨለማው የሞት ሸለቆ ውስጥ እንኳ ባልፍ አንተ ከእኔ ጋር ስለ ሆንህ ጉዳት ይደርስብኛል ብዬ አልፈራም፡፡ + +\s5 +\v 5 በጠላቶቼ ፊት ለፊት በፊቴ ገበታ አዘጋጀህልኝ ራሴን በዘይት ቀባህ ጽዋዬ ሞልቶ ተርፏል፡፡ + +\s5 +\v 6 በሕይወት ዘመኔ ሁሉ ደግነትና ፍቅር ዘወትር ከእኔ ጋር ይሆናሉ፤ በያህዌም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ፡፡ + +\s5 +\c 24 +\p +\v 1 ምድርና በእርሷ ያለው ሁሉ፣ ዓለምና በውስጧ የሚኖር ሁሉ የያህዌ ነው፡፡ +\v 2 እርሱ ባሕር ላይ መሥርቶአታልና በውሆችም ላይ አጽንቶአታል፡፡ + +\s5 +\v 3 ወደ ያህዌ ተራራ ማን ይወጣል? በተቀደሰ ስፍራውስ ማን ይቆማል? +\v 4 ንጹሕ እጅና ንጹሕ ልብ ያለው፣ ነፍሱን ለሐሰት ያላስገዛ በሐሰት የማይምል፣ + +\s5 +\v 5 እርሱ ከያህዌ ዘንድ በረከትን፣ ከመድኃኒቱም አምላክ ጽድቅን ይቀበላል፡፡ +\v 6 እርሱን የሚፈልግ ትውልድ የያዕቆብ አምላክን ፊት የሚፈልግ እንዲህ ያለ ነው፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 7 እናንተ ደጆች ራሳችሁን ቀና አድርጉ እናንተ የዘላለም በሮች የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ! +\v 8 ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው? ብርቱና ኃያል የሆነው ያህዌ፣ በጦርነት አሸናፊ የሆነው ያህዌ ነው፡፡ + +\s5 +\v 9 እናንተ ደጆች ራሳችሁን ቀና አድርጉ እናንተ የዘላለም በሮች የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ! +\v 10 ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው? የሰራዊት ጌታ ያህዌ እርሱ የክብር ንጉሥ ነው፡፡ ሴላ + +\s5 +\c 25 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ነፍሴን ወደ አንተ አነሣለሁ! +\v 2 አምላኬ ሆይ፣ በአንተ እታመናለሁ፡፡ እባክህ አታሳፍረኝ፤ አታዋርደኝ ጠላቶቼም በእኔ ላይ ደስ እንዲላቸው አታድርግ፡፡ +\v 3 አንተን ተስፋ የሚያደርጉ ከቶ አያፍሩም፤ እንዲያው ያለ ምክንያት የሚያታልሉ ግን ያፍራሉ፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌ ሆይ፣ አካሄድህን አሳውቀኝ መንገድህንም አስተምረኝ፡፡ +\v 5 በእውነትህ ምራኝ አስተምረኝም፤ አንተ የድነቴ አምላክ ነህና ቀኑን ሙሉ በአንተ ታመንሁ፡፡ + +\s5 +\v 6 ያህዌ ሆይ፣ ከጥንት ጀምሮ የነበሩ ምሕረትህንና ፍቅርህን አስብ፡፡ +\v 7 የልጅነቴን ኃጢአት፣ መተላለፌንም አታስብብኝ፤ ያህዌ ሆይ፣ እንደ ቸርነትህ ብዛት እንደ ምሕረትህም መጠን አስበኝ፡፡ + +\s5 +\v 8 ያህዌ መልካም ቅን ነው፤ ስለዚህ ኃጢአተኞችን መንገድን ያስተምራቸዋል፡፡ +\v 9 ትሑታንን በትክክለኛው መንገድ ይመራቸዋል መንገዱንም ያስተምራቸዋል + +\s5 +\v 10 ኪዳኑንና ሥርዐቱን ለሚጠብቁ የያህዌ መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ነው፡፡ +\v 11 ያህዌ ሆይ፣ ኃጢአቴ እጅግ ብዙ ነውና ስለ ስምህ ይቅር በለኝ + +\s5 +\v 12 ያህዌን የሚፈራ ሰው ማን ነው ጌታ በመረጠው መንገድ ያስተምረዋል፡፡ +\v 13 ዘመኑን በተድላ ደስታ ያሳልፋል ዘሮቹም ምድርን ይወርሳሉ፡፡ + +\s5 +\v 14 ያህዌ ለሚታዘዙት ሁሉ ወዳጃቸው ነው ለእነርሱ የገባውንም ኪዳን ያጸናል፡፡ +\v 15 ዐይኖቼ ዘወትር ወደ ያህዌ ናቸው እግሮቼን ከወጥመድ የሚያላቅቃቸው እርሱ ነው፡፡ +\v 16 እኔ ብቸኛና ምስኪን ነኝና ወደ እኔ ተመለስ ማረኝም፡፡ + +\s5 +\v 17 የልቤ ሐዘን በዝቶአል ከጭንቀቴ አወጣኝ፡፡ +\v 18 መከራዬንና ጭንቀቴን ተመልከት ኃጢአቴን ሁሉ ይቅር በል፡፡ +\v 19 ጠላቶቼ እንዴት እንደ በዙ እይ፤ እንዴት አምርረው እንደሚጠሉኝ ተመልከት፡፡ + +\s5 +\v 20 ነፍሴን ጠብቃት፤ ታደገኝም በአንተ ተማምኛለሁና አልዋረድ፤ አልፈር፡፡ +\v 21 አንተን ተስፋ አድርጌአለሁና ታማኝነትና ቅንነት ይጠብቁኝ + +\s5 +\v 22 ያህዌ ሆይ፣ እስራኤልን ከመከራው ሁሉ አድነው፡፡ + +\s5 +\c 26 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ያለ ነቀፋ ተመላልሻለሁና አንተው ፍረደኝ፤ ያለ ማወላውል በያህዌ ተማምኛለሁ፡፡ +\v 2 ያህዌ ሆይ፣ ፈትነኝ መርምረኝም የልቤንና የውስጤን ንጽሕና ፈትን! +\v 3 የኪዳን ታማኝነትህ ዘወትር በፊቴ ነው በታማኝነትህም ተመላለስሁ፡፡ + +\s5 +\v 4 ከአታላይ ሰዎች ጋር አልተባበርሁም ከማይታመኑ ሰዎችም ጋር አልተቀላቀልሁም፡፡ +\v 5 የክፉዎችን ኅብረት ጠላሁ ከዐመፀኞችም ጋር አልተቀመጥሁም፡፡ + +\s5 +\v 6 እጆቼን በየዋህነት እታጠባለሁ ያህዌ ሆይ፣ መሠዊያህንም እዞራለሁ +\v 7 የምስጋናህን መዝሙር እየዘመርሁ ድንቅ ሥራዎችህን ሁሉ አወራለሁ፡፡ +\v 8 ያህዌ ሆይ፣ የምትኖርበትን ቤት፣ የክብርን ማደሪያ ቦታ ወደድሁ፡፡ + +\s5 +\v 9 ነፍሴን ከኃጢአተኞች ጋር፣ ሕይወቴንም ደም ከተጠሙ ጋር አታጥፉ +\v 10 በእነርሱ እጅ የተንኰል ዕቅድ አለ ቀኝ እጃቸውም ጉቦ ያጋብሳል፡፡ + +\s5 +\v 11 እኔ ግን በታማኝነት እጓዛለሁ አድነኝ፤ ምሕረትም አድርግልኝ፡፡ +\v 12 እግሮቼ በተስተካከለ ምድር ላይ ቆመዋል በጉባኤ ፊት ያህዌን እባርካለሁ፡፡ + +\s5 +\c 27 +\p +\v 1 ያህዌ ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማን ነው? ያህዌ የሕይወቴ መታመኛዋ ነው የሚያስደነግጠኝ ማን ነው? + +\s5 +\v 2 ክፉ አድራጊዎች ሥጋዬን ለመብላት በቀረቡኝ ጊዜ፣ ባላጋራዎቼና ጠላቶቼ ተሰነካክለው ወደቁ፡፡ +\v 3 ሰራዊት ቢከብበኝ እንኳ፣ ልቤ አይፈራም ጦርነት ቢነሣብኝ እንኳ ልበ ሙሉ ነኝ፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌን አንዲት ነገር ለመንሁት፣ እርሷንም እሻለሁ፤ ያም በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በያህዌ ቤት እንድኖር፣ የመቅደሱን ውበት እንዳይና መቅደሱ ውስጥ አሰላስል ዘንድ ነው፡፡ + +\s5 +\v 5 በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ይሰውረኛናል በዐለትም ላይ ያቆመኛል፡፡ +\v 6 ያኔ በዙሪያዬ ባሉ ጠላቶቼ ላይ ራሴ ከፍ ከፍ ይላል በድንኳኑም የደስታ መሥዋዕት እሠዋለሁ ለያህዌ እቀኛለሁ፤ እዘምርለታለሁም፡፡ + +\s5 +\v 7 ያህዌ ሆይ፣ ወደ አንተ ስጮኽ ድምፄን ስማ ማረኝ መልስልኝም፡፡ +\v 8 «ፊቴን ፈልጉ» ባልህ ጊዜ ልቤ፣ «የያህዌን ፊት እፈልጋለሁ» አለች፡፡ + +\s5 +\v 9 ፊትህን ከእኔ አትሰውር ተቆጥተህም ባርያህን ገሸሽ አታድርገው! መቼም አንተ ረዳቴ ነህና የመድኃኒቴ አምላክ ሆይ፣ አትተወኝ፣ አትጣለኝም +\v 10 አባትና እናቴ ቢተውኝ እንኳ ያህዌ ይቀበለኛል፡፡ + +\s5 +\v 11 ያህዌ ሆይ መንገድህን አስተምረኝ ስለ ጠላቶቼም በቀናች መንገድ ምራኝ፡፡ +\v 12 ሐሰተኛ ምስክሮች ተነሥተውብኛልና ጠላቶቼ እንደ ፈለጉ እንዲያደርጉብኝ አትተወኝ፡፡ እነርሱ ዐመፃን ይረጫሉ! + +\s5 +\v 13 በሕያዋን ምድር የያህዌን መልካምነት እንደማይ ባላምን ኖሮ ምን እሆን ነበር? +\v 14 እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ አይዞህ በርታ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ + +\s5 +\c 28 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፤ ወደ አንተ እጣራለሁ፤ ዐለቴ ሆይ፣ ችላ አትበለኝ፡፡ አንተ ዝም ካልኸኝ ወደ መቃብር ከሚወርዱ ጋር እሆናለሁ፡፡ +\v 2 እንድትረዳኝ ወደ አንተ በጮኽኩ ጊዜ እጆቼን ወደ ቅዱስ ማደሪያህ በዘረጋሁ ጊዜ የልመኛዬን ቃል ስማ፡፡ + +\s5 +\v 3 ከዐመፀኞች ጋር፣ ክፋትን ከሚያደርጉ ጋር፣ በልባቸው ክፉ ሐሳብ እያለ ከባልንጀራቸው ጋር በሰላም ከሚናገሩ ጋር ጐትተህ አትውሰደኝ፡፡ +\v 4 የእጃቸውን ስጣቸው፣ እንደ ዐመፃቸውም ክፈላቸው እንደ ክፉ ተግባራቸው መልስቸው፡፡ +\v 5 ለያህዌ ሥራ ግድ ስለሌላቸው፣ ለእጆቹም ተግባር ስፍራ ስላልሰጡ እርሱ ያፈርሳቸዋል፤ መልሶም አይሠራቸውም፡፡ + +\s5 +\v 6 የልመናዬን ቃል ሰምቶአልና ያህዌ ይባረክ፡፡ +\v 7 ያህዌ ብርታቴና ጋሻዬ ነው ልቤ በእርሱ ይተማመናል፤ እርሱም ረዳኝ፡፡ ስለዚህ ልቤ ሐሤት አደረገ፤ በዝማሬም አመሰግነዋለሁ፡፡ +\v 8 ያህዌ የሕዝቡ ብርታታቸው ነው ለቀባውም የመዳን ዐምባ ነው፡፡ + +\s5 +\v 9 ሕዝብህን አድንን ርስትህንም ባርክ እረኛ ሁናቸው፤ ለዘላለሙም ተንከባከባቸው፡፡ + +\s5 +\c 29 +\p +\v 1 እናንተ የእግዚአብሔር ልጆች ለያህዌ ምስጋና ስጡ ስለ ክብሩና ስለ ብርታቱ ለያህዌ ምስጋና ስጡ፡፡ +\v 2 ለስሙ የሚገባውን ክብር ለያህዌ ስጡ በቅድስናው ውበት ለያህዌ ስገዱ + +\s5 +\v 3 የያህዌ ድምፅ በውሆች ላይ ያስተጋባል የክብር አምላክ ያንጐዳጉዳል ያህዌ በብዙ ውሆች ላይ ድምፁን ያሰማል፡፡ +\v 4 የያህዌ ድምፅ ኃያል ነው የያህዌ ድምፅ ባለ ግርማ ነው፡፡ +\v 5 የያህዌ ድምፅ የሊባኖስን ዝግባ ይሰብራል + +\s5 +\v 6 ሊባኖን እንደ ጥጃ፣ ስርዮንን እንደ ኮርማ ያዘልላል፡፡ +\v 7 የያህዌ ድምፅ የእሳት ነበልባል ይረጫል +\v 8 የያህዌ ድምፅ ምድረ በዳውን ያናውጣል የያህዌ ድምፅ የቃዴስን ምድረ በዳ ያናውጣል፡፡ + +\s5 +\v 9 የያህዌ ድምፅ ወርካዎችን ይወዘውዛል ጫካዎችን ይመነጥራል፡፡ ሁሉም በእርሱ ቤተ መቅደስ፣ «ክብር!» ይላል፡፡ +\v 10 ያህዌ በጐርፍ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶ ተቀምጧል ያህዌ ለዘላለም ይነግሣል፡፡ + +\s5 +\v 11 ያህዌ ለሕዝቡ ብርታት ይሰጣል ያህዌ ሕዝቡን በሰላም ይባርካል፡፡ + +\s5 +\c 30 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ አንተ አንሥተኸኛልና ጠላቶቼም በእኔ ላይ ደስ እንዲላቸው አላደረግህምና ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፡፡ +\v 2 ያህዌ ሆይ፣ እንድትረዳኝ ወደ አንተ ጮኽሁ አንተም ፈውሰኸኝ፡፡ +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ ነፍሴን ከሲኦል አወጣሃት ወደ መቃብር ከመውረድም አዳንኸኝ፡፡ + +\s5 +\v 4 እናንት የእርሱ ታማኝ ሕዝቦች ለያህዌ የምስጋና መዝሙር አቅርቡ፤ ቅድስናውን ስታስታውሱ፣ ውዳሴ ስጡ፡፡ +\v 5 ቁጣው ለአጭር ጊዜ ነው ሞገሱ ግን ለዕድሜ ልክ ነው፡፡ ሌሊት ሲለቀስ አድሮ ማለዳ ደስታ ይሆናል፡፡ + +\s5 +\v 6 በልበ ሙሉነት «አልናወጥም!» አልሁ፡፡ +\v 7 ያህዌ ሆይ በሞገስህ እንደ ተራራ ብርቱ አደረግኸኝ ፊትህን ስትሰውር ግን ውስጤ ታወከ፡፡ +\v 8 ያህዌ፣ ወደ አንተ ጮኽሁ፤ ከጌታም ዘንድ ሞገስ ፈለግሁ፡፡ + +\s5 +\v 9 እኔ ብሞት፣ ወደ መቃብርም ብወርድ ምን ጥቅም አለው? አፈር ያመሰግንሃልን? ታማኝነትህንስ ይናገራልን? +\v 10 ያህዌ ሆይ፣ ስማኝ ማረኝም፣ ያህዌ ረዳት ሁነኝ፡፡ + +\s5 +\v 11 ዋይታዬን ወደ ሽብሸባ ለወጥህልኝ ማቄን አስወግደህ ደስታን አለበስከኝ፡፡ +\v 12 እንግዲህ፣ ነፍሴ ታመስግንህ፤ ዝምም አትበል፡፡ አምላኬ ያህዌ ሆይ፣ ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፡፡ + +\s5 +\c 31 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ አንተን ተማጽኛለሁና እፍረት ከቶ አይድረስብኝ፤ በጽድቅህም ታደገኝ፡፡ +\v 2 ጌታ ሆይ፣ አድምጠኝ ፈጥነህም ታደገኝ የመማጸኛ ዐለት፣ የመዳኛም ምሽግ ሁነኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 አንተ ዐለቴና ዐምባዬ ነህ ስለ ስምህ ስትል ምራኝ መንገዱንም አሳየኝ፡፡ +\v 4 አንተ መታመኛዬ ነህና በስውር ከተዘረጋብኝ ወጥመድ አውጣኝ፡፡ + +\s5 +\v 5 መንፈሴን በእጅህ ዐደራ እሰጣለሁ የእውነት አምላክ ያህዌ ሆይ፣ ተቤዠኝ፡፡ +\v 6 ከንቱ ጣዖታትን የሚያገለግሉትን ጠላሁ እኔ ግን በያህዌ እታመናለሁ፡፡ +\v 7 መከራዬን አይተሃልና የነፍሴን ጭንቀት ዐውቀሃልና እኔ በኪዳን ታማኝነትህ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አድርጋለሁ፡፡ + +\s5 +\v 8 በጠላቴ እጅ አሳልፈህ አልሰጠኸኝም እግሮቼን ሰፊ ቦታ ላይ አቆምሃቸው፡፡ +\v 9 ያህዌ ሆይ፣ ጭንቀት ውስጥ ነኝና ማረኝ ዐይኖቼ በሐዘን ደክመዋል፤ ነፍስና ሥጋዬም ዝለዋል፡፡ + +\s5 +\v 10 ሕይወቴ በጭንቀት ዕድሜዬም በመቃተት አለቀ፡፡ ከኃጢአቴ የተነሣ ጉልበቴ ከዳኝ ዐጥንቴም ደቀቀ፡፡ +\v 11 ከጠላቶቼ ሁሉ የተነሣ ለጐረቤቶቼ መዘባበቻ ለሚያውቁኝ ሰዎች መሳለቂያ ሆኛለሁ መንገድ ላይ የሚያገኙኝም ይሸሹኛል፡፡ + +\s5 +\v 12 ማንም እንደማያስበው እንደ ሞተ ሰው ተረሳሁ እንደ ተሰበረ የሸክላ ዕቃም ተቆጠርሁ፡፡ +\v 13 የብዙዎችን ሹክሹክታ ሰምቻለሁ በዙሪያዬም የሽብር ወሬ አለ በእኔ ላይ ባሤሩ ጊዜ ሕይወቴን ለማጥፋት ዶለቱ፡፡ + +\s5 +\v 14 እኔ ግን ያህዌ ሆይ፣ በአንተ እተማመናለሁ «አንተ አምላኬ ነህ» አልሁ፡፡ +\v 15 ዘመኔ ሁሉ በእጅህ ነው፡፡ ከጠላቶቼና ከሚያሳድዱኝ ሰዎች እጅ አድነኝ፡፡ +\v 16 ፊትህን ባርያህ ላይ አብራ፡ በኪዳን ታማኝነትህ አድነኝ፡፡ + +\s5 +\v 17 ያህዌ ሆይ፣ አንተን ጠርቻለሁና ለእፍረትና ለውርደት አትዳርገኝ፡፡ ክፉዎች ግን ይፈሩ፤ ይዋረዱ ሲኦል ገብተው ጸጥ ይበሉ፡፡ +\v 18 ጻድቁ ላይ በእብሪት የሚናገሩ ትዕቢትና ንቀትን የተሞሉ ከንፈሮች ድዳ ይሁኑ፡፡ + +\s5 +\v 19 ለሚፈሩህ የሰወርኸው፣ በአንተም ለሚታመኑ በሰው ልጆች ሁሉ ፊት የምታደርገው እንዴት ታላቅ ነው! +\v 20 ከሰዎች ሤራ በማደሪያህ ውስጥ ትሸሽጋቸዋለህ፡፡ + +\s5 +\v 21 በተከበበች ከተማ ለእኔ ድንቅ ታማኝነቱን የገለጠ ያህዌ ይባረክ፡፡ +\v 22 እኔ ግን ባለ ማስተዋል፣ «ከእንግዲህ ከዐይንህ ፊት ተወግጃለሁ» ብዬ ነበር፤ ሆኖም፣ አንተ እንድትረዳኝ ስጮኽ ሰማኸኝ፡፡ + +\s5 +\v 23 እናንተ ታማኝ ተከታዮቹ ሁሉ ያህዌን ወደዱት ያህዌ ታማኞችን ይጠብቃል ለእብሪተኞች ግን የእጃቸውን ይሰጣቸዋል፡፡ +\v 24 እግዚአብሔርን ተስፋ የምታደርጉ ሁሉ በርቱ ልባችሁም ይጽና፡፡ + +\s5 +\c 32 +\p +\v 1 መተላለፉ ይቅር የተባለለት ኃጢአቱም የተሸፈነለት ሰው ቡሩክ ነው፡፡ +\v 2 ያህዌ በደሉን የማይቆጥርበት በመንፈሱም ሽንገላ የሌለበት ሰው ቡሩክ ነው፡፡ + +\s5 +\v 3 ቀኑን ሙሉ በመቃተቴ ዝም ባልሁ ጊዜ፣ አጥንቶቼ ተበላሹ፡፡ +\v 4 ቀኑን ሙሉ እጅህ ከብዳኛለች ብርታቴም የበጋ ትኩሳት እንደ መታው ነገር ከውስጤ ተሟጠጠ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 5 በዚያን ጊዜ ኃጢአቴን ለአንተ ተናዘዝሁ በደሌንም ከአንተ አልሰወርሁም ደግሞም፣ «መተላለፌን ለያህዌ እናዘዛለሁ» አልሁ አንተም የኃጢአቴን በደል ይቅር አልህ፡፡ ሴላ +\v 6 ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው በጭንቅ ጊዜ ወደ አንተ ይጸልይ ብርቱ ጐርፍ ሞልቶ ቢያጥለቀቅ እንኳ፣ ወደ እነዚህ ሰዎች አይቀርብም፡፡ + +\s5 +\v 7 አንተ መሸሸጊያዬ ነህ፤ ከመከራም ታወጣኛለህ፡፡ በድል ዝማሬ ትከበኛለህ፡፡ ሴላ +\v 8 አስተምርሃለሁ፤ በምትሄድበት መንገድ እመራሃለሁ እመክርሃለሁ ዐይኔንም አንተ ላይ አደርጋለሁ፡፡ + +\s5 +\v 9 ወደምትፈልጉት ቦታ እንዲሄዱላችሁ በልጓምና በልባብ እንደሚገሩት ማስተዋል እንደሌለው ፈረስና በቅሎ አትሁኑ፡፡ +\v 10 የክፉዎች ሐዘን ይበዛል በያህዌ የሚታመነውን ግን የእርሱ ኪዳን ታማኝነት ይከብበዋል፡፡ + +\s5 +\v 11 ጻድቃን ሆይ፣ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ ልበ ቅኖች ሆይ፣ እልል በሉ፡፡ + +\s5 +\c 33 +\p +\v 1 ጻድቃን ሆይ፣ በያህዌ ደስ ይበላችሁ ቅኖች ሊያመሰግኑት ይገባል፡፡ +\v 2 ያህዌን በመሰንቆ አመስግት ዐሥር አውታር ባለው በገና ዘምሩለት፡፡ +\v 3 አዲስ ዝማሬ አቅርቡለት ባማረ ቅኝት በገና ደርድሩ፤ እልልም በሉ፡፡ + +\s5 +\v 4 የያህዌ ቃል እውነት ነው ሥራውም ሁሉ የታመነ ነው፡፡ +\v 5 እርሱ ጽድቅንና ፍትሕን ይወዳል ምድር በያህዌ ኪዳን ታማኝት ተሞልታለች፡፡ +\v 6 ያህዌ ሰማያትን በቃሉ የሰማይ ሰራዊትን በአፉ እስትንፋስ ፈጠረ፡፡ + +\s5 +\v 7 የባሕርን ውሆች እንደ ክምር ቀላዩንም በመከማቻ ስፍራ አኖረ፡፡ +\v 8 ምድር ሁሉ ያህዌን ትፍራው በዓለም ያሉ ሁሉ በፊቱ ይንቀጥቀጥ፡፡ +\v 9 እርሱ ተናግሮአልና ሆኑ፤ እርሱ አዞአልና በስፍራቸው ጸኑ፡፡ + +\s5 +\v 10 ያህዌ የሕዝቦችን ምክክር ያጨናግፋል ዕቅዳቸውንም ከንቱ ያደርጋል፡፡ +\v 11 የያህዌ ዕቅድ ግን ለዘላለም ይኖራል የልቡም ሐሳቡም ለትውልድ ሁሉ ነው፡፡ +\v 12 ያህዌ አምላኩ የሆነለት፣ ርስቱ እንዲሆን የመረጠውም ሕዝብ ቡሩክ ነው፡፡ + +\s5 +\v 13 ያህዌ ከሰማይ ይመለከታል የሰው ልጆችንም ሁሉ ያያል፡፡ +\v 14 ከማደሪያው ሆኖ፣ በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ይመለከታል፡፡ +\v 15 የሁሉንም ልብ የሠራ እርሱ ነው የሚያደርጉትንም ሁሉ ይመለከታል፡፡ + +\s5 +\v 16 ንጉሥ በሰራዊቱ ብዛት አይድንም፤ ጀግናም በኃይሉ ብርታት አያመልጥም፡፡ +\v 17 በፈረስ ድል አደርጋለሁ ማለት ከንቱ ተስፋ ነው፤ በብርቱ ጉልበቱም ማንም አይድንም + +\s5 +\v 18 እነሆ፣ የያህዌ ዐይኖች በሚፈሩት ላይ ናቸው፤ በኪዳን ታማኝነቱ በሚታመኑት ላይ አትኩረዋል፡፡ +\v 19 ይህም የሚሆነው ከሞት ሊያድናቸውና ከራብ ዘመንም ሊጠብቃቸው ነው፡፡ + +\s5 +\v 20 ያህዌን በተስፋ እንጠብቃለን እርሱ ረድኤታችንና ጋሻችን ነው፡፡ +\v 21 በቅዱስ ስሙ ተማምነናልና ልባችን በእርሱ ደስ ይለዋል፡፡ + +\s5 +\v 22 ያህዌ ሆይ፣ ተስፋችንን አንተ ላይ አድርገናልና ምሕረትህ በእኛ ላይ ይሁን፡፡ + +\s5 +\c 34 +\p +\v 1 ያህዌን ሁልጊዜ አመሰግናለሁ ምስጋናውም ዘወትር በአፌ ነው፡፡ + +\s5 +\v 2 ያህዌን አመሰግናለሁ! ትሑታን ይህን ሰምተው ደስ ይበላቸው፡፡ +\v 3 ያህዌን ከእኔ ጋር አመስግኑት በአንድነት ስሙን ከፍ ከፍ እናድርግ፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌን ፈለግሁ እርሱም መለሰልኝ ከፍርሃቴም ሁሉ አዳነኝ፡፡ +\v 5 ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ ፊታቸውም በፍጹም አያፍርም፡፡ +\v 6 ይህ ችግረኛ ጮኸ እግዚአብሔርም ሰማው ከመከራውም ሁሉ አዳነው፡፡ + +\s5 +\v 7 የያህዌ መልአክ በሚፈሩት ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸዋልም፡፡ +\v 8 ያህዌ መልካም መሆኑን ቀምሳችሁ እዩ፡፡ በእርሱ የተማመነ ሰው ቡሩክ ነው፡፡ +\v 9 እናንተ ቅዱሳን ያህዌን ፍሩ እርሱን የሚፈሩ አንዳች አያጡምና፡፡ + +\s5 +\v 10 አንበሶች ሊያጡ ሊራቡም ይችላሉ ያህዌን የሚሹ ግን መልካም ነገር አይጐድልባቸውም፡፡ +\v 11 ልጆቼ ሆይ፣ ኑ ስሙኝ ያህዌን መፍራት አስተምራችኋለሁ፡፡ + +\s5 +\v 12 ሕይወትን የሚወድ፣ መልካም ነገርን ለማየት ረጅም ዕድሜ የሚፈልግ ማነው? +\v 13 እንግዲያስ አንደበትህን ከክፉ ከልክል ከንፈርህንም ከውሸት ጠብቅ፡፡ +\v 14 ከክፉ ሽሽ፤ መልካሙንም አድርግ ሰላምን ፈልጋት ደግሞም ተከተላት፡፡ + +\s5 +\v 15 የያህዌ ዐይኖች ጻድቃን ላይ ናቸው፡፡ ጆሮዎቹም ለጩኸታቸው ተከፍተዋል፡፡ +\v 16 መታሰቢያቸውን ከምድር ላይ ለማጥፋት የያህዌ ፊት ክፉ በሚያደርጉ ላይ ነው። +\v 17 ጻድቃን ወደ ያህዌ ይጮኻሉ እርሱም ይሰማቸዋል፤ ከመከራቸውም ሁሉ ያድናቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 18 ያህዌ ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው መንፈሳቸው የደቀቀውንም ያድናቸዋል፡፡ +\v 19 የጻድቅ መከራው ብዙ ነው ያህዌ ግን ከሁሉም ያድነዋል፡፡ +\v 20 ዐጥንቶቹን ሁሉ ይጠብቃል ከእነርሱ አንዱ እንኳ አይሰበርም፡፡ + +\s5 +\v 21 ኃጢአተኛን ክፋት ይገድለዋል ጻድቃንን የሚጠሉ ይፈርድባቸዋል፡፡ +\v 22 ያህዌ የባርያዎቹን ነፍስ ይታደጋል እርሱንም መጠጊያ ያደረገ አይፈረድበትም፡፡ + +\s5 +\c 35 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ የሚቃወሙኝን ተቃወማቸው፤ የሚዋጉኝንም ተዋጋቸው፡፡ +\v 2 ትልቁንና ትንሹን ጋሻ ያዝ እኔንም ለመርዳት ተነሥ፡፡ +\v 3 በሚያሳድዱኝ ላይ ጦርና ሰይፍህን ምዘዝና ነፍሴን «እኔ አዳኝሽ ነኝ» በላት፡፡ + +\s5 +\v 4 ሕይወቴን የሚፈልጓት ይፈሩ ይዋረዱም እኔን ለመጉዳት የሚያደቡ አፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ፤ ግራ ይጋቡ፡፡ +\v 5 በነፋስ ፊት እንዳለ እብቅ ይሁኑ የያህዌም መልአክ ያሳድዳቸው፡፡ +\v 6 መንገዳቸው ጨለማና ድጥ ይሁን የያህዌ መልአክ ያባርራቸው፡፡ + +\s5 +\v 7 ያለ ምክንያት ወጥመድ ዘርግተውብኛል ያለ ምክንያት ሕይወቴን ለማጥፋት ጉድጓድ ቆፍረዋል፡፡ +\v 8 ጥፋት በድንገት ይምጣባቸው የዘረጉት ወጥመድ ይያዛቸው ጉድጓድ ውስጥ ወድቀው ይጥፉ፡፡ + +\s5 +\v 9 እኔ ግን በያህዌ ደስ ይለኛል በማዳኑም ሐሤት አደርጋለሁ፡፡ +\v 10 ዐጥንቶቼ ሁሉ፣ «ያህዌ ሆይ፣ ድኻውን ከእርሱ ከሚበረቱ፣ ችግረናውንና ምስኪኑን ከቀማኞች እጅ የሚያድን እንደ አንተ ያለ ማን ነው?» እለዋለሁ፡፡ + +\s5 +\v 11 ሐሰተኛ ምስክሮች ተነሥተውብኛል በሐሰትም ይከስሱኛል፡፡ +\v 12 እኔን ብቸኛ አድርገው በመልካም ፈንታ ክፉ መለሱልኝ፡፡ + +\s5 +\v 13 እኔ ግን እነርሱ በታመሙ ጊዜ ማቅ ለበስሁ፤ ለእነርሱ ጾምሁ፤ አንገቴን ደፋሁ፡፡ +\v 14 ለወንድሙ እንደሚያለቅስ ሰው አዘንሁ ለእናቱ ልጅ እንደሚያዝን ሰው ሆንሁ፡፡ + +\s5 +\v 15 እኔ በተሰናከልሁ ጊዜ ደስ ብሎአቸው ተሰበሰቡ ግፈኞች በድንገት ተሰበሰቡብኝ ያለ ዕረፍትም ቦጫጨቁኝ፡፡ +\v 16 እንደ ምናምንቴዎች አፌዙብኝ ጥርሳቸውንም አፋጩብኝ፡፡ + +\s5 +\v 17 ጌታ ሆይ፣ እስከ መቼ ዝም ብለህ ታያለህ? ነፍሴን በእነርሱ ከመጠቃት ሕይወቴንም ከአንበሶች አድናት፡፡ +\v 18 በታላቅ ጉባኤ መካከል አመሰግንሃለሁ ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበትም እወድስሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 19 ያለ ምክንያት የሚጠሉኝ ጠላቶቼ በእኔ ላይ ደስ እንዲላቸው፣ ተንኰላቸውንም እንዲፈጽሙብኝ አታድርግ፡፡ +\v 20 የሰላም ቃል ከአፋቸው አይወጣም ነገር ግን በምድሪቱ በጸጥታ በሚኖሩት ላይ ተንኮል ይሸርባሉ፡፡ + +\s5 +\v 21 አፋቸውን አስፍተው በመክፈት፣ «እሰይ! እሰይ! በዐይናችን አየነው» አሉ፡፡ +\v 22 ያህዌ ሆይ፣ ይህን አይተሃልና ዝም አትበል ጌታ ሆይ፣ ለእኔም አትራቅ፡፡ +\v 23 አምላኬ ጌታዬ፣ ለእኔ ለመሟገት ተነሥ ልትከራከርልኝም ተንቀሳቀስ፤ + +\s5 +\v 24 ያህዌ ሆይ፣ በጽድቅህ ፍረድልኝ በእኔም ላይ ደስ አይበላቸው፡፡ +\v 25 በልባቸው፣ «እሰይ፣ ያሰብነው ተሳካ» አይበሉ፤ «ዋጥ አደረግነውም» አይበሉ፡፡ +\v 26 በጭንቀቴ ደስ የሚላቸው ይፈሩ፤ ግራም ይጋቡ፡፡ በእኔ ላይ የሚያፌዙ፤ እፍረትና ውርደት ይልበሱ፡፡ + +\s5 +\v 27 ፍትሕ ማግኘቴን የሚፈልጉ እልል ይበሉ ሐሤትም ያድርጉ፣ ዘወትርም፣ «የባርያው ሰላም ደስ የሚለው ያህዌ ይመስገን» ይበሉ፡፡ +\v 28 ያኔ የአንተን ጽድቅ እናገራለሁ ቀኑን ሙሉ አመሰግንሃለሁ፡፡ + +\s5 +\c 36 +\p +\v 1 ክፉ ሰው በልቡ፣ ክፋትን ያስባል በዐይኖቹም ፊት እግዚአብሔርን መፍራት የለም፡፡ +\v 2 በደሉ ግልጽ ወጥቶ እንዳይጠላ እያሰበ ራሱን ይሸነግላል፡፡ + +\s5 +\v 3 ንግግሩ ተንኰልንና ሐሰትን የተሞላ ነው፤ አስተዋይ መሆንንና መልካም ማድረግን አይፈልግም፡፡ +\v 4 በመኝታው ላይ ክፋት ያውጠነጥናል ራሱን ወደ ክፉ መንገድ ይመራል ክፉውንም ነገር አያርቅም፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ ሆይ፣ ታማኝነትህ እስከ ሰማይ እውነተኛነትህም እስከ ደመናት ይደርሳል፡፡ +\v 6 ጽድቅህ እንደ እግዚአብሔር ተራራ ነው ፍርድህም እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ ያህዌ ሆይ፣ አንተ ሰውንም እንስሳንም ትጠብቃለህ፡፡ + +\s5 +\v 7 እግዚአብሔር ሆይ፣ ታማኝነትህ እንዴት ክቡር ነው! የሰው ልጆች ሁሉ በክንፎችህ ጥላ ሥር መጠጊያ ያገኛሉ፡፡ +\v 8 ከቤትህ ሲሳይ ተመግበው ይጠግባሉ፤ ከበረከትህም ወንዝ ይጠጣሉ፡፡ +\v 9 በአንተ ዘንድ የሕይወት ምንጭ አለ በአንተ ብርሃን ብርሃን እናያለን፡፡ + +\s5 +\v 10 ለሚያውቁህ ምሕረትህ፣ ልባቸውም ለቀና ጽድቅህ አይቋረጥባቸው፡፡ +\v 11 የእብሪተኛ እግር አይቅረበኝ የክፉ ሰው እጅም አያሳድደኝ፡፡ +\v 12 ክፉ አድራጊዎች እንዴት እንደ ወደቁ መነሣትም እንደማይችሉ ተመልከት፡፡ + +\s5 +\c 37 +\p +\v 1 በክፉዎች ምክንያት አትበሳጭ ኃጢአት በሚሠሩም አትቅና፤ +\v 2 እንደ ሣር ቶሎ ይደርቃሉና እንደ ለመለመ ቅጠልም ይጠወልጋሉ፡፡ + +\s5 +\v 3 በያህዌ ተማመን፤ መልካምንም አድርግ በምድሪቱ ተቀመጥ፤ ታምነህም ተሰማራ፡፡ +\v 4 በያህዌ ደስ ይበልህ የልብህንም ፍላጐት ይሰጥሃል፡፡ + +\s5 +\v 5 መንገድህን ለያህዌ አደራ ስጥ በእርሱ ታመን እርሱም ያከናውንልሃል፡፡ +\v 6 ጽድቅህን እንደ ብርሃን ያንተንም ንጽሕና እንደ ቀትር ፀሐይ ያበራዋል፡፡ + +\s5 +\v 7 በያህዌ ፊት ጸጥ በል፤ በትዕግሥትም ተጠባበቀው፡፡ ነገር በተሳካለት፣ ክፋትንም በሚሸርብ ሰው አትቅና + +\s5 +\v 8 አትቆጣ፤ ተስፋም አትቁረጥ መከራን ከማብዛቱ ውጪ ምንም ስለማይጠቅምህ አትከፋ፡፡ +\v 9 ክፉ አድራጊዎች ይጠፋሉ ያህዌን የሚጠባበቁ ግን ምድሪቱን ይወርሳሉ፡፡ +\v 10 ብዙም ሳይቆይ ክፉ ሰው ይጠፋል ብትፈልግም ቦታውን አታገኘውም፡፡ + +\s5 +\v 11 ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ በታላቅ ሰላምም ደስ ይላቸዋል፡፡ +\v 12 ክፉዎች ጻድቃን ላይ ያሤራሉ ጥርሳቸውንም ያፋጩባቸዋል፡፡ +\v 13 መጥፊያ ቀናቸው እንደ ደረሰ ስለሚያውቅ ጌታ ይስቅባቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 14 ድኾችንና ችግረኞችን ለመጣል ልበ ቅኖችንም ለመግደል ክፉዎች ሰይፋቸውን መዘዙ፤ ቀስታቸውንም ገተሩ፡፡ +\v 15 ሰይፋቸው የገዛ ልባቸውን ይወጋል ቀስታቸውም ይሰበራል፡፡ + +\s5 +\v 16 ከክፉ ሰው ብዙ ሀብት ይልቅ፣ የጻድቅ ጥቂት ሀብት ይበልጣል፡፡ +\v 17 የክፉዎች ክንድ ይሰበራልና ያህዌ ግን ጻድቃንን ይደግፋቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 18 ያህዌ ያለ ነቀፋ የሚመላለሱትን ዕለት ዕለት ይጠብቃቸዋል፡፡ ርስታቸውም ለዘላለም ይኖራል፡፡ +\v 19 በክፉ ቀን አያፍሩም በራብ ዘመንም የሚበሉትን አያጡም፡፡ + +\s5 +\v 20 ክፉዎች ግን ይጠፋሉ የያህዌ ጠላቶች እንደ መስክ ውበት ይሆናሉ፡፡ እንደ ጢስም በንነው ይጠፋሉ፡፡ +\v 21 ኃጢአተኛ ይበደራል፣ ግን መልሶ አይከፍልም ጻድቅ ግን በልግስና ይሰጣል፡፡ + +\s5 +\v 22 እግዚአብሔር የባረካቸው ምድርን ይወርሳሉ እርሱ የረገማቸው ግን ይጠፋሉ፡፡ +\v 23 የሰውን አካሄድ የሚያጸና ያህዌ ነው በመንገዱም ደስ ይለዋል፡፡ +\v 24 ያህዌ በእጁ ደግፎ ስለሚይዘው ቢሰናከል እንኳ አይወድቅም፡፡ + +\s5 +\v 25 ጐልማሳ ነበርሁ፤ አሁን አርጅቻለሁ ጻድቅ ሲጣል፣ ዘሩም እንጀራ ስለምን አላየሁም፡፡ +\v 26 ጻድቅ ሁልጊዜ በልግሥና ይሰጣል፣ ደግሞም ያበድራል ልጆቹም የተባረኩ ይሆናሉ፡፡ +\v 27 ከክፉ ራቅ መልሙንም አድርግ ለዘላለምም በሰላም ትኖራለህ፡፡ + +\s5 +\v 28 ያህዌ ፍትሕ ይወዳልና ታማኞቹንም በፍጹም አይጥልም፤ ለዘላለምም ይጠብቃቸዋል፡፡ የኃጢአተኛው ዘር ግን ይጠፋል፡፡ +\v 29 ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ በእርሷም ለዘላለም ይኖራሉ፡፡ +\v 30 የጻድቅ አፍ ጥበብን ይናገራል አንደበቱም ፍትሕን ያወራል፡፡ + +\s5 +\v 31 የአምላኩ ሕግ ልቡ ውስጥ ነው አካሄዱም አይሰናከልም፡፡ +\v 32 ኃጢአተኛው ጻድቅን ይመለከተዋል ሊገድለውም ይፈልጋል፡፡ +\v 33 እግዚአብሔር ግን በእጁ አይጥለውም ፍርድ ፊት ሲቀርቡም አይረታም፡፡ + +\s5 +\v 34 ያህዌን ደጅ ጥና፤ መንገዱንም ጠብቅ እርሱም ምድርን እንድትወርስ ከፍ ከፍ ያደርግሃል፡፡ ክፉዎች ሲጠፋ ታያለህ፡፡ + +\s5 +\v 35 ክፉና ጨካኙን ሰው ምቹ መሬት ላይ እንዳለ ዛፍ ለምልሞ አየሁት +\v 36 ተመልሼ ስመጣ ግን በቦታው አልበረም፤ ፈለግሁ ላገኘው ግን አልቻልሁም፡፡ + +\s5 +\v 37 ጻድቅን ሰው ተመልከት ቅን የሆነውንም ሰው እይ የሰላም ሰው ተስፋ አለውና፡፡ +\v 38 ኃጠአተኞች ግን ፈጽሞ ይደመስሳሉ ዘራቸውም ይወገዳል፡፡ + +\s5 +\v 39 የጻድቃን ድነት ከያህዌ ዘንድ ነው በመከራም ጊዜ ይጠብቃቸዋል፡፡ +\v 40 ያህዌ ይረዳቸዋል፤ ደግሞም ይታደጋቸዋል፡፡ ከክፉዎች እጅ ነጥቆ ያወጣቸዋል እርሱን መጠጊያ አድርገዋልና ያድናቸዋል፡፡ + +\s5 +\c 38 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ በቁጣህ አትገሥጸኝ በመዓትህም አትቅጣኝ፡፡ +\v 2 ፍላጻዎችህ ወግተውኛልና እጅህ ተጭናኛለች፡፡ + +\s5 +\v 3 ከቁጣህ የተነሣ መላው አካሌ ታመመ ከኃጢአቴ የተነሣም ዐጥንቶቼ ጤና የላቸውም፡፡ +\v 4 በደሌ ውጦኛል እንደ ከባድ ሸክምም ተጭኖኛል፡፡ + +\s5 +\v 5 በሞኝነት ካደረግሁት የተነሣ ቁስሌ መገለ፤ ሸተተም፡፡ +\v 6 ጐበጥሁ፤ በየቀኑም እያጐነበስኩ ሄድሁ ቀኑን ሙሉ በትካዜ ዋልሁ፡፡ + +\s5 +\v 7 ውስጤ እንደ እሳት ይቃጠላል ሥጋዬም ጤና የለውም፡፡ +\v 8 እንደ ዲዳ ሆንሁ፤ ፈጽሞም ደቀቅሁ ከልቤ ምሬት የተነሣ እቃትታለሁ፡፡ + +\s5 +\v 9 ጌታ ሆይ፣ የጥልቅ ልቤን ናፍቆት አንተ ታውቃለህ መቃተቴም ከአንተ የተሰወረ አይደለም፡፡ +\v 10 ልቤ በኃይል ይመታል፤ ጉልበት ከድቶኛል የዐይኔም ብርሃን ፈዝዞአል፡፡ + +\s5 +\v 11 ካለሁበት ሁኔታ የተነሣ፣ ወዳጆቼም ባልንጀሮቼም ሸሹኝ ጐረቤቶቼም ርቀው ቆሙ፡፡ +\v 12 ሕይወቴን ማጥፋት የሚወዱ ወጥመድ ዘረጉብኝ ሊጐዱኝ የሚፈልጉም በዛቻ ተናገሩኝ፤ በእኔም ላይ ቀኑን ሙሉ ያሤራሉ፡፡ + +\s5 +\v 13 እኔ ግን እንደማይሰማ ደንቆሮ ምንም መናገር እንደማይችል ዲዳ ሰው ሆንሁ፡፡ +\v 14 ጆሮው እንደማይሰማ አንደበቱም መልስ መስጠት እንደማይችል ሰው ሆንሁ፡፡ + +\s5 +\v 15 ያህዌ ሆይ፣ በፍጹም ልቤ አንተን እጠብቃለሁ ጌታ ሆይ፣ አንተ መልስ ትሰጠኛለህ፡፡ +\v 16 ይህን የምለው ጠላቶቼ በእኔ ላይ ደስ እንዳይላቸው ነው፤ እግሬ ቢንሸራተት ክፉ ነገር ያደርጉብኛል፡፡ + +\s5 +\v 17 ልወድቅ ተቃርቤአለሁ ሕመሜም ፋታ አልሰጠኝም፡፡ +\v 18 በደሌን እናዘዛለሁ ኃጢአቴም አስጨንቆኛል፡፡ + +\s5 +\v 19 ጠላቶቼ እጅግ ብዙ ናቸው ያለ ምክንያት የሚጠሉንም በዝተዋል፡፡ +\v 20 በመልካም ፈንታ ክፉ መለሱልኝ መልሙን እየተከተልሁ ቢሆንም፣ እነርሱ ግን እኔ ላይ የሐሰት ክስ ደረደሩ፡፡ + +\s5 +\v 21 ያህዌ ሆይ፣ አትተወኝ አምላኬ ሆይ፣ ከእኔ አትራቅ +\v 22 ጌታ መድኃኒቴ እኔን ለመርዳት ፍጠን፡፡ + +\s5 +\c 39 +\p +\v 1 እኔ፣ «በአንደበቴ እንዳልበድል ለምናገረው እጠነቀቃለሁ፣ በክፉዎችም ፊት እስካለሁ ድረስ፣ በአፌ ልጓም አደርጋለሁ» አልሁ፡፡ + +\s5 +\v 2 አንድ ቃል እንኳ ሳልናገር ዝም አልሁ ለመልካም ነገር እንኳ አፌን ዘጋሁ፤ ያም ሆኖ ጭንቀቴ ባሰ፡፡ +\v 3 ልቤ በውስጤ ጋለ ስለ እነዚህ ነገሮች ሳስብ እንደ እሳት ነደደ፡፡ ከዚያም መናገር ጀመርሁ፡፡ + +\s5 +\v 4 «ያህዌ ሆይ፣ የሕይወቴ መጨረሻ መቼ እንደ ሆነና የዕድሜዬን ልክ አሳውቀኝ አላፊ ጠፊ መሆኔን አሳየኝ፡፡ +\v 5 እነሆ፣ ዘመኔን በስንዝር ለክተህ አኖርህ ዕድሜዬም በፊትህ እንደ ኢምንት ነው፡፡ በእርግጥ የሰው ሁሉ ሕይወት ጥላ ነው፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 6 በእርግጥ ሰው ሁሉ እንደ ጥላ ይመላለሳል፡፡ ለማን እንደሚሆን ሳያውቅ ሀብት ንብረት ያከማቻል፡፡ +\v 7 ጌታ ሆይ፣ አሁንስ ማንን ልጠብቅ? ተስፋዬ አንተ ብቻ ነህ፡፡ + +\s5 +\v 8 ከኃጢአቴ አድነኝ የሞኞች መዘባበቻ አታድርገኝ፡፡ +\v 9 ይህን ያደረግህ አንተ ነህና ዝም እላለሁ አፌንም አልከፍትም፡፡ + +\s5 +\v 10 ክንድህን አንሣልኝ ከእጅህ ምት የተነሣ ዝዬአለሁ፡፡ +\v 11 ሰውን በኃጢአቱ ትገሥጸዋለህ፤ ትቀጣዋለህም የሚወደውንም ነገር እንደ ብል ታጠፋበታለህ፡፡ በእርግጥ ሰው ሁሉ ተን ነው፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 12 ያህዌ ሆይ፣ ጸሎቴን ስማ፤ ጩኸቴንም አድምጥ ለቅሶየንም ቸል አትበል፡፡ በአንተ ፊት እንደ መጻተኛ ነኝና እንደ አባቶቼም እንግዳ ነኝ፡፡ +\v 13 ከመሞቴ በፊት ዳግመኛ ደስ እንዲለኝ ዐይንህን ከላዬ አንሣ፡፡ + +\s5 +\c 40 +\p +\v 1 በትዕግሥት ያህዌን ደጅ ጠናሁት እርሱም ዘንበል አለልኝ፤ ጩኸቴንም ሰማኝ፡፡ +\v 2 ከአደገኛ ጉድጓድ፣ ከሚያዘቅጥም ጭቃ አወጣኝ፤ እግሮቼን፣ በዐለት ላይ አቆመ አካሄዴንም አጸና፡፡ + +\s5 +\v 3 ለአምላካችን ምስጋና አዲስ መዝሙር በአፌ አኖረ፡፡ ብዙዎች ዐይተው ያከብሩታል፤ በያህዌም ይታመናሉ፡፡ +\v 4 ያህዌን መታመኛው ያደረገ ወደ ትዕቢተኛው የማይመለከት የሐሰት አማልክት ወደሚከተሉት የሚያይ ቡሩክ ነው፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ አምላኬ ሆይ፣ ያደረግኸው ድንቅ ነገር ብዙ ነው ለእኛ ያለህም ሐሳብ ከቁጥር በላይ ነው፤ ላወራው ልናገረው ብል ስፍር ቁጥር አይኖረውም፡፡ +\v 6 መሥዋዕትንና መባን አልፈለግህም ጆሮዎቼን ግን ከፈትህ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትንና የኃጢአት መሥዋዕትን አልጠየቅህም፡፡ + +\s5 +\v 7 እኔም እንዲህ አልሁ፣ «እነሆ፣ መጥቻለሁ በመጽሐፍ ጥቅልል ስለ እኔ ተጽፎአል፤ +\v 8 አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ ሕግህም ልቤ ውስጥ ነው፡፡ +\v 9 በታላቅ ጉባኤ ውስጥ ጽድቅህን ዐወጅሁ ያህዌ ሆይ፣ ይህን ከማድረግ ወደ ኋላ አለማለቴንም አንተ ታውቃለህ፡፡ + +\s5 +\v 10 ጽድቅህን በልቤ ውስጥ አልሸሸግሁም፤ ታማኝነትህንና ማዳንህን ተናገርሁ ምሕረትህንና እውነትህን ከታላቅ ጉባኤ አልደበቅሁም፡፡ +\v 11 ያህዌ ሆይ ምሕረትህን አትንፈገኝ ቸርነትህና ታማኝነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ፡፡ + +\s5 +\v 12 ስፍር ቁጥር የሌለው ችግር ከብቦኛል የኃጢአቴ ብዛት ስለ ያዘኝ ማየት ተስኖኛል፤ ከራሴ ጠጉር ይልቅ በዝቶአል፤ ልቤም ከድቶኛል፡፡ +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ እኔን ለማዳን ፈቃድህ ይሁን እኔን ለመርዳትም ፍጠን፡፡ + +\s5 +\v 14 ነፍሴን ለመንጠቅ የሚፈልጉ ይፈሩ፤ ይዋረዱም፡፡ ጉዳቴን የሚሹ ተዋርደው በመጡበት ይመለሱ፡፡ +\v 15 በእኔ ላይ፣ «እሰይ! እሰይ!» የሚሉ በራሳቸው እፍረት ይደንግጡ + +\s5 +\v 16 አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ደስ ይበላቸው ሐሤትም ያድርጉ፤ ማዳንህን የሚወዱ ዘወትር፣ «ያህዌ ከፍ ከፍ ይበል» ይበሉ፡፡ +\v 17 እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ ጌታ ግን ያስብልኛል፡፡ አንተ ረዳቴ ነህ እኔን ለማዳን ፍጠን አምላኬ ሆይ አትዘግይ፡፡ + +\s5 +\c 41 +\p +\v 1 ለድኾች የሚያስብ ቡሩክ ነው እርሱንም በመከራ ቀን ያህዌ ያድነዋል፡፡ +\v 2 ያህዌ ይጠብቀዋል፤ በሕይወትም ያኖረዋል በምድርም ላይ ይባርከዋል ለጠላቶቹ ምኞትም አሳልፎ አይሰጠውም፡፡ +\v 3 ታሞ በተኛበት አልጋ ያህዌ ይንከባከበዋል በበሽታውም ጊዜ መኝታውን ያነጥፍለታል፡፡ + +\s5 +\v 4 እኔም፣ «ያህዌ ሆይ፣ ማረኝ! በአንተ ላይ ኃጢአት አድርጌአለሁና ፈውሰኝ» አልሁ፡፡ +\v 5 «የሚሞተው መቼ ነው፤ ስሙ የሚደመሰሰውስ መቼ ነው?» እያሉ ጠላቶቼ እኔ ላይ ክፉ ይናገራሉ፡፡ +\v 6 ሊጠይቀኝ ቢመጣ እንኳ በልቡ ስድብ እያመቀ ከአንገት በላይ ይናገራል ወጥቶም ወሬ ይነዛል፡፡ + +\s5 +\v 7 ጠላቶቼ ሁሉ ተባብረው እኔ ላይ ያሾኮሽካሉ የክፋ ነገርም በላዬ ያውጠነጥናሉ +\v 8 «ክፉ ደዌ ይዞታል፤ አልጋ ላይ ወድቋል ከእንግዲህ ከተኛበት አይነሣም» ይላሉ። +\v 9 እንጀራዬን ተካፍሎ የበላ የተማመንሁበት የቅርብ ወዳጄ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣ፡፡ + +\s5 +\v 10 አንተ ግን ያህዌ ሆይ ማረኝ፤ የእጃቸውን እንድሰጣቸውም አስነሣኝ፡፡ +\v 11 ጠላቴ በእኔ ላይ ድል አላገኘምና እንደ ወደድከኝ በዚህ ዐወቅሁ፡፡ +\v 12 ስለ ቅንነቴ እኔን ትረዳኛለህ በፊትህም ለዘላለም ታኖረኛለህ፡፡ + +\s5 +\v 13 የእስራኤል አምላክ ያህዌ ከዘላለም እስከ ዘለላለም ይመስገን፡፡ አሜን አሜን፡፡ + +\s5 +\c 42 +\p +\v 1 ዋላ የምንጭ ውሃ እንደሚናፍቅ አምላኬ ሆይ፣ እኔም እግዚአብሔርን ተጠማሁ፡፡ +\v 2 መቼ ደርሼ ነው የአምላክን ፊት የማየው? + +\s5 +\v 3 ጠላቶቼ ዘወትር፣ «አምላክህ የት አለ?» ስለሚሉኝ እንባዬ ቀንና ሌሊት ምግቤ ሆነ፡፡ +\v 4 ነፍሴ በውስጤ እየፈሰሰች እነዚህን ነገሮች አስታውሳለሁ፣ ታላቅ ሕዝብ ወደ እግዚአብሔር ቤት እየመራሁ በአእላፍ ሕዝብ መካከል በእልልታና በምስጋና መዝሙር እንዴት ከሕዝቡ ጋር እሄድ እንደ ነበር ትዝ አለኝ፡፡ + +\s5 +\v 5 ነፍሴ ሆይ፣ ለምን ታዝኛለሽ? በውስጤስ ለምን ትታወኪያለሽ? የመድኃኒቴን አምላክ ዳግመኛ እንዳመሰግነው እግዚአብሔርን ተስፋሽ አድርጊ፡፡ +\v 6 አምላኬ ሆይ፣ ነፍሴ በውስጤ አዝናለች ስለዚህ በዮርዳኖስ ምድር፣ ከአርሞንኤም ተራራ ጫፍ በሚዛር ተራራ አስብሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 7 በፏፏቴህ ድምፅ ጥልቁ ጥልቁን ይጠራል ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በእኔ ላይ አለፈ፡፡ +\v 8 ያም ሆኖ፣ ያህዌ ምሕረቱን በቀን ያዛል በሌሊትም ዝማሬው በእኔ ዘንድ አለ ይህም ለሕይወቴ አምላክ የማቀርበው ጸሎት ነው፡፡ + +\s5 +\v 9 እግዚአብሔር ዐለቴን፣ «ለምን ረሳኸኝ? ጠላቴ ከደረሰብኝ ጭንቀት የተነሣ ለምን በሐዘን እመላለሳለሁ?» እለዋለሁ፡፡ +\v 10 ጠላቶቼ ቀኑን ሙሉ፣ «አምክህ የት አለ?» እያሉ የሚያደርሱብን ፌዝ ዐጥንቶቼ ውስጥ እንደ ሰይፍ ሆነ፡፡ + +\s5 +\v 11 ነፍሴ ሆይ፣ ለምን ታዝኛለሽ? ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ? የመድኃኒቴን አምላክ ዳግመኛ እንዳመሰግነው እግዚአብሔርን ተስፋሽ አድርጊ፡፡ + +\s5 +\c 43 +\p +\v 1 አምላክ ሆይ፣ ፍረድልኝ ከጽድቅ ከራቀ ሕዝብ ጋር ተሟገትልኝ፡፡ +\v 2 አምላክ ሆይ፣ አንተ ብርታቴ ነህ ለምን ተውኸኝ? ጠላት እያስጨነቀኝ ለምን በሐዘን እመላለሳለሁ? + +\s5 +\v 3 ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እኔንም ይምሩኝ፡፡ ወደ ቅዱስ ኮረብታህና ወደ ማደሪያህ ያድርሱኝ፡፡ +\v 4 እኔም ወደ እግዚአብሔር መሠዊያ እሄዳለሁ ፍጹም ደስታዬ ወደ ሆነው አምላኬ አቀናለሁ፡፡ እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፣ በበገና አመሰግንሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 5 ነፍሴ ሆይ፣ ለምን ታዝኛለሽ? ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ? የመድኃኒቴን አምላክ ዳግመኛ እንዳመሰግነው እግዚአብሔርን ተስፋሽ አድርጊ፡፡ + +\s5 +\c 44 +\p +\v 1 አምላክ ሆይ፣ በጆሮአችን ሰምተናል በቀድሞ ዘመን እነርሱ በነበሩበት ዘመን ያደረግኸውን አባቶቻችን ነግረውናል፡፡ +\v 2 ሕዝቦችን በእጅህ አሳድዶህ አስወጣህ የእኛን ሕዝብ ግን ተከልህ ሕዝቦችን አደቀቅህ የእኛ ሕዝብ ግን በምድሩ እንዲኖር አደረግህ፡፡ + +\s5 +\v 3 ምድሪቱን የወረሳት በሰይፋቸው አልነበረም፣ ያዳናቸውም የገዛ ክንዳቸው አልነበረም አንተ ወደድሃቸውና ቀኝ እጅህ፣ ክንድህና የፊትህ ብርሃን ይህን አደረገ፡፡ +\v 4 እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ ንጉሤ ነህ ያዕቆብ ድል እንዲያገኝ የወሰንህ አንተ ነህ፡፡ + +\s5 +\v 5 በአንተ ርዳታ ጠላቶቻችንን ድል እንነሣለን በስምህም ተቃዋሚዎቻችንን እንረግጣለን፡፡ +\v 6 በቀስቴ አልተማመንምና ሰይፌም አያድነኝም፡፡ + +\s5 +\v 7 አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው፡፡ +\v 8 ዘወትር በእግዚአብሔር እንመካለን ለዘላለምም ስምህን እንወድሳለን፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 9 አሁን ግን ትተኸናል ለውርደትም ዳርገኸናል ከሰራዊታችንም ጋር አትወጣም፡፡ +\v 10 ከጠላት ፊት እንድንሸሽ አደረግህ ባላንጣዎቻችንም ዘረፉን፡፡ +\v 11 እንደሚታረዱ በጐች አደረግኸን በሕዝቦችም መካከል በተንኸን፡፡ + +\s5 +\v 12 ሕዝብህን በርካሽ ዋጋ ሸጥኸው ከሽያጩም ያተረፍኸው የለም፡፡ +\v 13 ለጐረቤቶቻችን ማፈሪያ በዙሪያችን ላሉትም መሣቂያና መዘባበቻ አደረግኸን፡፡ +\v 14 በሕዝቦች ዘንድ ስድብ፣ በሰዎችም መካከል ራስ የሚነቀነቅብን አደረግኸን፡፡ + +\s5 +\v 15 ውርደቴ ዘወትር በፊቴ ነው ፊቴም እፍረትን ተከናንቦአል፡፡ +\v 16 ይህም ከዘላፊውና ከተሳዳቢው ድምፅ የተነሣ ከጠላትና ከተበቃይ የተነሣ ነው፡፡ +\v 17 ይህ ሁሉ ቢደርስብንም፣ አንተን ግን አልረሳንም ለኪዳንህ ታማኝ መሆንንም አልተውንም፡፡ + +\s5 +\v 18 ልባችን ከአንተ አልተመለሰም ርምጃችንም ከመንገድህ ወደ ኋላ አላለም፡፡ +\v 19 አንተ ግን ተኩላዎች በሚውሉበት ቦታ ሰባብረህ ጣልኸን፤ በሞት ጥላም ሸፈንኸን፡፡ +\v 20 የአምካችንን ስም ረስተን፣ እጆቻችንን ለባዕድ አማልክት ዘርግተን ቢሆን ኖሮ፣ +\v 21 እግዚአብሔር ይህን ማወቅ ይሣነዋልን? እርሱ የሰውን ልብ ምስጢር የሚረዳ ነውና፡፡ +\v 22 ያም ሆኖ፣ ቀኑን ሙሉ ስለ አንተ እንገደላለን እንደሚታረዱ በጐችም ተቆጠርን፡፡ + +\s5 +\v 23 ጌታ ሆይ ንቃ፣ ለምንስ ትተኛለህ? ተነሥ፣ ለዘላለምም አትተወን፡፡ +\v 24 ፊትህን ለምን ከእኛ ትሰውራለህ? መከራና ጭንቀታችን ለምን ችላ ትላለህ? + +\s5 +\v 25 እስከ ምድር ትቢያ ድረስ ወርደናል አካላችን ከምድር ጋር ተጣብቆአል፡፡ +\v 26 እኛን ለመርዳት ተነሥ ስለ ኪዳን ታማኝነትህ ስትል ተቤዠን፡፡ + +\s5 +\c 45 +\p +\v 1 ልቤ መልካም ሐሳብ አፈለቀ ለንጉሡ የተቀኘሁትን ቅኔ አሰማለሁ አንደበቴ እንደ መልካም ጸሐፊ ብዕር ነው፡፡ +\v 2 አንተ ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ውብ ነህ ከከንፈሮችህ ጸጋ ይፈስሳል፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ባርኮሃል፡፡ + +\s5 +\v 3 ኃያል ሆይ፣ ሰይፍህን በወገብህ ታጠቅ ግርማ ሞገስንም ተላበስ +\v 4 ስለ እውነት ስለ ፍትሕ ግርማን ተጐናጽፈህ ድል ለማድረግ ገሥግሥ ቀን እጅህ ድንቅ ነገር ታሳይ፡፡ + +\s5 +\v 5 ፍላጻዎችን የሾሉ ናቸው ሕዝቦች ከእግርህ በታች ይወድቃሉ፡፡ ፍላጻዎችህ የንጉሡ ጠላቶችን ልብ ይወጋል፡፡ +\v 6 አምላክ ሆይ፣ ዙፋንህ የዘላለም ዙፋን ነው በትረ መንግሥትህም የፍትሕ በትረ መንግሥት ነው፡፡ +\v 7 ጽድቅን ወደድህ፤ ዐመፃንም ጠላህ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ ከባልንጀሮችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ፡፡ + +\s5 +\v 8 ልብስህ ሁሉ ከከርቤ፣ ከእሬትና ከብርጉድ በተቀመመ ሽቱ ያውዳል፤ በዝሆን ጥርስ ከተዋቡ ቤተ መንግሥቶች የሚወጣ የበገናና የመሰንቆ ድምፅ ደስ ያሰኝሃል፡፡ +\v 9 በቤተ መንግሥትህ ከሚገኙ ወይዛዝርት መካከል፤ የነገሥታት ልጆች ይገኛሉ፤ ንግሥቲቱም በንጹሕ ወርቅ ያሸበረቀ ጌጤኛ ልብስ ተጐናጽፋ በቀኝህ በኩል ትቆማለች፡፡ + +\s5 +\v 10 ልጄ ሆይ፣ አድምጪ አስተውይ፣ ጆሮሽንም አዘንብይ ሕዝብሽንና የአባትሽን ቤት እርሺ፡፡ +\v 11 ንጉሥ በውበትሽ ተማርኮአል እርሱ ጌታሽ ነውና አክብሪው፡፡ + +\s5 +\v 12 የጢሮስ ሴት ልጅ ስጦታ ይዛ ትመጣለች፤ ሀብታሞች ደጅ ይጠኑሻል፡፡ +\v 13 በቤተ መንግሥት ያለችው ልዕልት አጊጣለች ልብሷም በወርቅ አሸብርቋል፡፡ + +\s5 +\v 14 ጌጠኛ ልብሷን ለብሳ ወደ ንጉሡ ትገባለች፤ ደናግል ጓደኞቿም አጅበዋት ወደ አንተ ይመጣሉ፡፡ +\v 15 በደስታና በሐሤትም አብረው ወደ ንጉሡ ቤት ይገባሉ፡፡ + +\s5 +\v 16 ወንዶች ልጆችህ በአባቶችህ እግር ይተካሉ በምድር ሁሉ ላይ ገዦች አድርገህ ትሾማቸዋለህ፡፡ +\v 17 ስምህን በትውልድ ሁሉ ዘንድ ለመታሰቢያ አደርጋለሁ ስለዚህ ሕዝቦች ከዘላለም እስከ ዘላለም ይወድሱሃል፡፡ + +\s5 +\c 46 +\p +\v 1 እግዚአብሔር መጠጊያችንና ኃይላችን፣ በመከራም ቀን ረዳታችን ነው፡፡ +\v 2 ስለዚህ ምድር ብትናወጥ ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ ቢወሰዱ፣ አንፈራም፡፡ +\v 3 ውሆች ቢያስገመግሙ፣ ዐረፋ ቢደፍቁም፣ ከውሃው ሙላት የተነሣ ተራሮች ቢንቀጠቀጡም አንደነግጥም፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 4 የእግዚአብሔርን ከተማ የልዑልንም የተቀደሰ ማደሪያ ደስ የሚያሰኙ ወራጅ ወንዞች አሉ፡፡ +\v 5 እግዚአብሔር በመካከሏ ነውና አትናወጥም ጠዋት በማለዳ እግዚአብሔር ይረዳታል፡፡ + +\s5 +\v 6 ሕዝቦች በዐመፅ ተነሡ፤ መንግሥታት ወደቁ ድምፁን ከፍ አድርጐ አሰማ ምድርም ቀለጠች፡፡ +\v 7 የሰራዊት ጌታ ያህዌ ከእኛ ጋር ነው የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 8 ኑ የእግዚአብሔርን ሥራ በምድር ላይ የደረሰውን ጥፋት ተመልከቱ፡፡ +\v 9 ከምድር ዳር እስከ ዳርቻ ጦርነትን ያስወግዳል ቀስትን ይሰብራል፤ ጦርንም ያነክታል ጋሻዎችንም በእሳት ያቃጥላል፡፡ + +\s5 +\v 10 ጸጥ በሉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ በሕዝቦች ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ፡፡ +\v 11 የሰራዊት አምላክ ያህዌ ከእኛ ጋር ነው፤ የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው፡፡ ሴላ + +\s5 +\c 47 +\p +\v 1 ሕዝቦች ሁሉ እጆቻችሁን አጨብጭቡ ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር እልል በሉ፡፡ +\v 2 በምድር ሁሉ ላይ ታላቅ ንጉሥ የሆነው ልዑል ያህዌ እጅግ አስፈሪ ነው፡፡ + +\s5 +\v 3 ሕዝቦችን ከእኛ በታች አደረገ፣ መንግሥታትንም ከእግራችን ሥር አስገዛልን፡፡ +\v 4 ለሚወደው ለያዕቆብ ክብር የሆነችውን ርስታችንን እርሱ መረጠልን፡፡ +\v 5 እግዚአብሔር በእልልታ፣ ያህዌም በመለከት ድምፅ ዐረገ + +\s5 +\v 6 ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ ዘምሩ ለንጉሣችን ዘምሩ +\v 7 እግዚአብሔር የምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና ስለዚህ በማስተዋል ዘምሩለት፡፡ + +\s5 +\v 8 እግዚአብሔር በሕዝቦች ሁሉ ነግሦአል እግዚአብሔር በተቀደሰ ዙፋኑ ላይ ተቀምጧል፡፡ +\v 9 ከአብርሃም አምላክ ሕዝብ ጋር የሕዝቦች መኳንንት ተሰበሰቡ የምድር ነገሥታት የእግዚአብሔር ናቸውና እርሱ እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡ + +\s5 +\c 48 +\p +\v 1 ያህዌ ታላቅ ነው፣ በአምላካችን ከተማ በተቀደሰ ተራራው ላይ ከፍ ያለ ምስጋና ሊቀርብለት ይገባል፡፡ +\v 2 የምድር ሁሉ ደስታ የሆነው በሰሜን በኩል በርቀት የሚታየው በከፍታ ላይ አምሮ የደመቀው የጽዮን ተራራ የታላቁ ንጉሥ ከተማ ነው፡፡ +\v 3 እግዚአብሔር በቤተ መንግሥት ውስጥ ሆኖ ብርቱ ምሽጓ መሆኑን አስመስክሮአል፡፡ + +\s5 +\v 4 እነሆ፣ ነገሥታት ተባብረው መጡ በአንድነትም ገሠገሡ፡፡ +\v 5 ዐይተው ተደነቁ ደንግጠውም ፈረጠጡ፡፡ +\v 6 በዚያ ፍርሃትና ድንጋጤ ያዛቸው ምጥ እንደያዛት ሴት ብርክ ያዛቸው፡፡ + +\s5 +\v 7 የምሥራቅ ነፋስ የተርሴስን መርከብ እንደሚሰባብር አንተ አንበረከክሃቸው +\v 8 በጆሮአችን እንደ ሰማን በሰራዊት አምላክ ከተማ በአምላካችን ያህዌ ከተማ በዐይናችን አየን፡፡ + +\s5 +\v 9 አምላክ ሆይ፣ በቤተ መቅደስ ውስጥ ሆነን ታማኝነትህን እናስባለን፡፡ +\v 10 እግዚአብሔር ሆይ፣ እንደ ስምህ ምስጋናህም እስከ ምድር ዳርቻ ነው፤ ቀኝ እጅህም ጽድቅን የተሞላች ናት፡፡ + +\s5 +\v 11 ስለ ጽድቅህ የጽዮን ተራራ ደስ ይበላት የይሁዳም ልጅ ሐሤት ታድርግ፡፡ + +\s5 +\v 12 በጽዮን ተራራ፣ በዙሪያዋም ተመላለሱ፣ ማማዎቿን ቁጠሩ፤ +\v 13 ለሚቀጥለው ትውልድ ትናገሩ ዘንድ ጠንካራ ቅጥሮቿን አስተውሉ ምሽጐችዋንም ተመልከቱ፡፡ + +\s5 +\v 14 ይህ አምላክ ከዘላለም እስከ ዘላለም አምላካችን ነው፤ እስከ መጨረሻው መሪያዎችንም እርሱ ነው፡፡ + +\s5 +\c 49 +\p +\v 1 ሕዝቦች ሁሉ ይህን ስሙ በዓለም የምትኖሩ ሁሉ ይህን አድምጡ፡፡ +\v 2 ዝቅተኞችና ከፍተኞች ሀብታሞችና ድኾች ይህን በአንድነት አድምጡ፡፡ + +\s5 +\v 3 አፌ ጥበብን ይናገራል የልቤ ሐሳብም ማስተዋልን ይሰጣል፡፡ +\v 4 ጆሮዬን ወደ ምሳሌ አዘነብላለሁ በበገናም የምሳሌዎቹን ትርጒም እገልጣለሁ፡፡ +\v 5 ክፉ ቀን ሲመጣና አታላዮች ሲከብቡኝ ለምን እፈራለሁ? + +\s5 +\v 6 በሀብታቸው የሚመኩትንና በብልጽግናቸው የሚተማመኑትን ለምን እፈራለሁ? +\v 7 ማንም ወንድሙን መቤዠት ለእርሱም ቤዛ የሚሆነውን ዋጋ ለእግዚአብሔር መክፈል አይችልም፡፡ +\v 8 የነፍስ ቤዛ ውድ ነውና በቂ ዋጋ ሊገኝለት አይችልም፡፡ + +\s5 +\v 9 እንዳይሞትና ወደ መቃብር እንዳይወርድ ማንም ለዘላለም መኖር አይችልም፡፡ +\v 10 ሰዎች ሁሉ ይሞታሉ፤ ጠቢባን እንኳ ከሞኞችና ከሞኞች እኩል በአንድት ይጠፋሉ ሀብታቸውንም ለሌላው ጥለው ይሄዳሉ፡፡ + +\s5 +\v 11 እነርሱ የሚያስቡት ቤተ ሰባቸው ለዘላለም እንደሚኖር፣ መኖሪያ ስፍራቸውም ለትውልድ ዘመን እንደማይጠፋ በመሆኑ መሬቶቻቸውን በስማቸው ይሰይማሉ፡፡ + +\s5 +\v 12 ግን ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም አሁን ታይተው በኃላ እንደሚጠፉ እንስሳት ይመስላል፡፡ +\v 13 ይህ የምኞት ዕድል ፈንታ የእነርሱንም አባባል የሚከተሉ ሰዎች መጨረሻ ግብ ነው፡፡ + +\s5 +\v 14 እንደ በጐች ለሞት የተመደቡ ናቸው እረኛቸውም ሞት ነው በማለዳ ቅኖች ይገዟቸዋል፤ መኖሪያ ቦታ አጥቶ አካላቸው ሲኦል ውስጥ ይፈራርሳል፡፡ +\v 15 እግዚአብሔር ግን ሕይወቴን ከሲኦል ኃይል ይቤዣል፤ እርሱም ይቀበለኛል፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 16 ሰው ባለጠጋ ቢሆን፣ የቤቱም ክብር ቢበዛለት አትፍራ፡፡ +\v 17 በሚሞትበት ጊዜ ምንም ይዞ አይሄድም ክብሩም አብሮት አይወርድም፡፡ + +\s5 +\v 18 ሰው በሕይወቱ ዘመን ቢደሰትም፣ ሁሉም ነገር ስለ ተሳካለት ቢመሰገንም፣ +\v 19 በሞት ተለይቶ ከእንግዲህ ብርሃን ወደሚያይበት ወደ አባቶች ትውልድ ይሄዳል፡፡ +\v 20 ሁሉም ነገር እያለው ማስተዋል የጐደለው ሰው ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል፡፡ + +\s5 +\c 50 +\p +\v 1 ኃያሉ አምላክ ያህዌ ተናገረ ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያዋ ድረስ ምድርን ተናገረ፡፡ +\v 2 ፍጹም ውብ ከሆነችው ከጽዮን እግዚአብሔር አበራ፡፡ + +\s5 +\v 3 አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም የሚባላ እሳት በፊቱ ነው ኃይለኛ ዐውሎ ነፋስም በዙሪያው ነው፡፡ +\v 4 ሕዝቡ ላይ ይፈርድ ዘንድ በላይ ያሉ ሰማያትንና ምድርን፣ «በመሥዋዕት ከእኔ ጋር ኪዳን የገቡትን +\v 5 ቅዱሳኔን ሁሉ ወደ እኔ ሰብስቡ» ብሎ ይጣራል፡፡ + +\s5 +\v 6 ሰማያት ጽድቁን ያውጃሉ፡፡ እግዚአብሔርን ራሱ ፈራጅ ነው፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 7 «ሕዝቤ ሆይ፣ ስማኝ ልንገርህ እስራኤል ሆይ፣ በአንተ ላይ ልመስክር፤ አምላክህ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፡፡ +\v 8 ስለ መሥዋዕትህ አልነቅፍህም የሚቃጠል መሥዋዕትህ ሁልጊዜ በፊቴ ነው፡፡ + +\s5 +\v 9 ከበረትህ ኮርማዎችን፣ ከጉሮኖህም አውራ ፍየሎችን አልወስድም +\v 10 የዱር አራዊት ሁሉ፣ በሺ ተራሮች ያለው እንስሳ ሁሉ የእኔ ነውና፡፡ +\v 11 በየተራሮች ያሉ ወፎችን ሁሉ ዐውቃለሁ፡፡ በመስክ የሚገኙ እንስሶች ሁሉ የእኔ ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 12 ብራብ እንኳ ለአንተ አልናገርም ዓለምና በውስጧ ያለው ሁሉ የእኔ ነውና፡፡ +\v 13 የኮርማዎችን ሥጋ እበላለሁን? ወይስ የፍየሎችን ደም እጠጣለሁን? + +\s5 +\v 14 የምስጋና መሥዋዕት ለእግዚአብሔር አቅርብ፤ ስእለትህንም ለልዑል አምላክ ክፈል፡፡ +\v 15 በመከራ ቀን ጥራኝ እኔ እታደግሃለሁ፤ አንተም ታከብረኛለህ፡፡ + +\s5 +\v 16 ዐመፀኛውን እግዚአብሔር እንዲህ ይለዋል ሕጌን ለማነብነብ፣ ኪዳኔንም በአፍህ ለመናገር ምን መብት አለህ? +\v 17 ትምህርቴን ጠልተሃል፤ ቃሌንም ወደ ኃላህ ጥለሃል፡፡ + +\s5 +\v 18 ሌባውን ባየህ ጊዜ ከእርሱ ጋር ሮጥህ፣ ዕድል ፈንታህንም ከአመንዝሮች ጋር አደረግህ፡፡ +\v 19 አፍህን ለክፋት፣ አንደበትህንም ሽንገላ ለመናገር አዋልህ፡፡ +\v 20 ተቀምጠህ ወንድምህን አማኸው የእናትህንም ልጅ ስም አጠፋህ፡፡ + +\s5 +\v 21 ይህን ሁሉ ስታደርግ ዝም አልሁህ ስለዚህ እኔም እንዳንተው የሆንሁ መሰለህ፡፡ አሁን ግን ፊት ለፊት ነገርህን ገልጩ እገሥጽሃለሁ፡፡ +\v 22 እናንት እግዚአብሔርን የምትረሱ ይህን አስተውሉ፤ አለበለዚያ ብትንትናችሁን አወጣለሁ! የሚያስጥላችሁም የለም! + +\s5 +\v 23 የምስጋና መሥዋዕት የሚያቀርብልኝ ያከብረኛል፤ መንገዱን ቀና ለሚያደርግ የእግዚአብሔር ማዳን አሳየዋለሁ፡፡ + +\s5 +\c 51 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ፤ እንደ ርኅራኄም ብዛት መተላለፌን ደምስስ፡፡ +\v 2 በደሌን ፈጽሞ እጠብልኝ ከኃጢአቴም አንጻኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 መተላለፌን ዐውቃለሁና ኃጢአቴም ዘወትር በፊቴ ነው፡፡ +\v 4 አንተን፣ በእርግጥ አንተን ብቻ በደልሁ ስትናገር ትክክል ነህ፤ ስትፈርድም ትክክል ነህ፡፡ + +\s5 +\v 5 ስወለድ ጀምሮ በደለኛ ነህ ገና እናቴም ስትወልደኝ ኃጢአተኛ ነኝ፡፡ +\v 6 እነሆ፣ አንተ ልቤ ውስጥ እውነትን ትሻለህ ስለዚህ ጥልቅ ጥበብን በውስጤ አስተምረኝ፡፡ + +\s5 +\v 7 በሂሶጵ እርጨኝ እኔም እነጻለሁ፡፡ እጠበኝ፤ ከበረዶም ይልቅ እነጻለሁ፡፡ +\v 8 ያደቀቅሃቸው አጥንቶቼ ደስ እንዲላቸው ደስታንና ሐሤትን አሰማኝ፡፡ +\v 9 ፊትህን ከኃጢአቴ መልስ፣ በደሌን ሁሉ ደምስስልኝ፡፡ + +\s5 +\v 10 አምላኬ ሆይ፣ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ ቀና የሆነውንም መንፈስ በውስጤ አድስ +\v 11 ከፊትህ አትጣለኝ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ አትውሰድብኝ፡፡ + +\s5 +\v 12 የማዳንህን ደስታ መልስልኝ በእሺታ መንፈስም ደግፈኝ ያዘኝ፡፡ +\v 13 በዚያ ጊዜ፣ ለሕግ ተላላፊዎች መንገድህን አስተምራለሁ፡፡ ኃጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ፡፡ + +\s5 +\v 14 የድነቴ አምላክ ሆይ፣ ደም አፍሳሽነቴን ይቅር በል አንደበቴም በደስታ ስለ ጽድቅህ በእልልታ ይዘምራል፡፡ +\v 15 ጌታ ሆይ፣ ከንፈሮቼን ክፈት አፌም ምስጋናህን ያውጃል፡፡ +\v 16 መሥዋዕትን ብትወድ ኖሮ፣ እሰጥህ ነበር፤ የሚቃጠል መሥዋዕትም ደስ አያሰኝህም፡፡ + +\s5 +\v 17 የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው አንተ፣ የተሰበረውን የተዋረደውን መንፈስ አትንቅም፡፡ +\v 18 በበጐነትህ ለጽዮን መልካም አድርግ የኢየሩሳሌምንም ቅጥሮች ሥራ፡፡ +\v 19 በዚያ ጊዜ የጽድቅ መሥዋዕት፣ የሚቃጠል መሥዋዕትና ፈጽሞ የሚቃጠል መሥዋዕት ደስ ያሰኝሃል፡፡ እኛም በመሠዊያህ ላይ እንደ ገና ኮርማዎችን እናቀርባለን፡፡ + +\s5 +\c 52 +\p +\v 1 ኃያል ሆይ፣ ሁከት በመፍጠር ለምን ትኩራለህ? የእግዚአብሔር ኪዳን ታማኝነት ዕለት ዕለት ነው፡፡ +\v 2 አንደበትህ እንደ ሰላ ምላጭ ጥፋትን ያውጠነጥናል፡፡ + +\s5 +\v 3 ከመልካም ይልቅ ክፋትን፣ እውነትን ከመናገር ይልቅ ሐሰትን ወደድህ፡፡ + +\s5 +\v 4 አንተ አታላይ አንደበት ሆይ፣ ሌሎችን የሚያጠፋ ቃል ወደድህ፡፡ +\v 5 ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ያጠፋሃል ይነጥቅሃል፤ ከድንኳንህም መንጥቆ ያወጣሃል፤ ከሕያዋን ምድር ይነቅልሃል፡፡ + +\s5 +\v 6 ጻድቃን ይህን ዐይተው ይፈራሉ እንዲህ እያሉም ይሥቁበታል፤ +\v 7 «ተመልከቱ፣ እግዚአብሔርን መጠጊያ ያላደረገ፣ ነገር ግን በሀብቱ ብዛት የተመካ በክፋቱም የበረታ ያ ሰው እነሆ!» + +\s5 +\v 8 እኔ ግን በእግዚአብሔር ቤት እንደ ለመለመ የወይራ ዛፍ ነኝ፤ ከዘላለም እስከ ዘላለም፣ በእግዚአብሔር ምሕረት እታመናለሁ። +\v 9 ስላደረግኸው ነገር ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፤ ስምህ መልካም ነውና ስምህን ተስፋ አደርጋለሁ፤ በቅዱሳንም መካከል አመሰግንሃለሁ። + +\s5 +\c 53 +\p +\v 1 ሞኝ በልቡ፣ «እግዚአብሔር የለም» ይላል ብልሹዎች ናቸው፤ ጸያፍ ነገርም አድርገዋል መልካም የሚያደርግ አንድ እንኳ የለም፡፡ +\v 2 አስተዋዮችና እርሱን የሚፈልጉ ሰዎች ለማግኘት፣ እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ፡፡ +\v 3 ሁሉም ወደ ሌላ ዘወር ብለዋል፤ በአንድነትም ብልሹዎች ሆነዋል፡፡ መልካም የሚያደርግ አንድ እንኳ የለም፡፡ + +\s5 +\v 4 ክፉ አድራጊዎች ከቶ አያስተውሉምን እንጀራ እንደሚበላ ሰው ሕዝቤን የሚበሉ፣ እግዚአብሔርንም ጠርተው የማያውቁት ሰዎች አይማሩምን? +\v 5 ምንም የሚያስፈራ ነገር ሳይኖር እጅግ ፈሩ፤ የዘመቱብህን ሰዎች ዐጥንት እግዚአብሔር በተነ፤ እግዚአብሔር ስለ ናቃቸው እንዲህ ያሉ ሰዎች ያፍራሉ፡፡ + +\s5 +\v 6 ምነው ለእስራኤል የሚሆን መዳን ከጽዮን በመጣ እግዚአብሔር ሕዝቡን ከምርኮ በመለሰ ጊዜ ያዕቆብ ደስ ይለዋል፤ እስራኤልም ሐሤት ያደርጋል! + +\s5 +\c 54 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ በስምህ አድነኝ በኃይልህም ፍረድልኝ፡፡ +\v 2 እግዚአብሔር ሆይ፣ ጸሎቴን ስማልኝ የአፌንም ቃል አድምጥ፡፡ +\v 3 ባዕዳን ተነሥተውብኛልና ጨካኞችም ነፍሴን ይፈልጓታል እግዚአብሔርንም ከምንም አልቆጠሩትም፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 4 እነሆ እግዚአብሔር ረዳቴ ነው ጌታም ደግፎ ይይዘኛል፡፡ +\v 5 ክፋታቸውን በጠላቶቼ ላይ መልስባቸው በቃልህ ታማኝ ነህና አጥፋቸው፡፡ + +\s5 +\v 6 በበጐ ፈቃድ መሥዋዕት አቀርብልሃለሁ መልም ነውና ያህዌ ሆይ፣ ስምህን አመሰግናለሁ፡፡ +\v 7 ከመከራ ሁሉ ታድጐኛልና ዐይኔም የጠላቶቼን ውድቀት ለማየት በቅቶአል፡፡ + +\s5 +\c 55 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ጸሎቴን ስማ ልመናዬንም ቸል አትበል፡፡ +\v 2 ችግሬ ዕረፍት ነስቶኛልና ወደ እኔ ተመልከት መልስልኝም፡፡ +\v 3 ከጠላቶቼ ዛቻ የተነሣ፣ ፈርቼአለሁ፤ በክፉዎችም ጭቈና ደቅቄአለሁ፡፡ መከራ አምጥተውብኛል፤ በቁጣም ያሳድዱኛል፡፡ + +\s5 +\v 4 ልቤ በውስጤ ተሸበረብኝ የሞት ድንጋጤም መጣብኝ፡፡ +\v 5 ፍርሃትና እንቅጥቅጥ መጡብኝ ሽብርም በረታብኝ፡፡ + +\s5 +\v 6 እኔም እንዲህ አልሁ፣ «ምነው የርግብ ክንፍ በኖረኝ! በርሬ ሄጄ ዐርፍ ነበር፡፡ +\v 7 እነሆ፣ ኮብልዬ በራቅሁ ነበር በምድረ በዳ በሰነበትሁ ነበር፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 8 ከዐውሎ ነፋስና ከውሽንፍር ሸሽቼ ወደ መሸሽጊያ ፈጥኜ በደረስሁ ነበር፡፡» +\v 9 ግፍና ሁከት በከተማዪቱ ዐይቻለሁና ጌታ ሆይ ግራ አጋባቸው፤ ቋንቋቸውንም ደበላልቅ! + +\s5 +\v 10 ቀንና ሌሊት ቅጥሮቿን ይዞራሉ ተንኰልና መከራ በውስጧ አሉ፡፡ +\v 11 ዐመፃ በመካከልዋ ነው፤ ግፍና አታላይነት ከጐዳናዋ አይጠፋም፡፡ + +\s5 +\v 12 የሰደበኝ ጠላት አይደለም ያማ ቢሆን በታገሥኩ ነበር፤ የሚታበይብኝ፣ ራሱንም ቀና ቀና ያደረገብኝ ባላንጣ አይደለም፤ ያማ ቢሆን፣ ከእርሱ በተሸሸግሁ ነበር፡፡ +\v 13 ነገር ግን ያን ያደረግህ አንተ እኩያየ፣ ባልንጀራዬና የቅርብ ወዳጄ ነህ፡፡ +\v 14 ደስ የሚል ኅብረት በአንድነት ነበረን በሕዝቡ መካከል በእግዚአብሔር ቤት አብረን ተመላልሰን ነበር፡፡ + +\s5 +\v 15 በድንገት ሞት ይምጣባቸው ክፋት በመካከላቸው ናትና በሕይወታቸው እያሉ ወደ ሲኦል ይወረዱ፡፡ + +\s5 +\v 16 እኔ ግን እግዚአብሔርን እጣራለሁ ያህዌም ያድነኛል፡፡ +\v 17 በማታ፣ በጧትና በቀትር አቃሥታለሁ እቃትታለሁም እርሱም ድምፄን ይሰማል፡፡ +\v 18 ከእኔ ጋር የሚዋጉት ብዙ ናቸውና እርሱ፣ ከተከፈተብኝ ጦርነት በሰላም ይታደገኛል፡፡ + +\s5 +\v 19 ስለማይለወጡና አምኬንም ስለማይፈሩ ከዘላለም እስከ ዘላለም ዙፋኑ ላይ ያለው እግዚአብሔር ሰምቶ ያዋርዳቸዋል፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 20 ጓደኛዬ የምለው ሰው እጁን በወዳጆቹ ላይ ሰነዘረ፤ ቃል ኪዳኑንም አፈረሰ፡፡ +\v 21 አፉ ከቅቤ ይልቅ የለዘበ ነው በልቡ ግን ጦርነት አለ፤ ቃሉ ከዘይት ይልቅ የለሰለሰ ነው ሆኖም የተመዘዘ ሰይፍ ነው፡፡ + +\s5 +\v 22 የከበድህን ነገር በያህዌ ላይ ጣል እርሱ ደግፎ ይይዝሃል፤ የጻድቁን መናወጥ ከቶ አይፈቅድም፡፡ +\v 23 አንተ ግን እግዚአብሔር ሆይ፣ ዐመፀኞችን ወደ ጥፋት ጉድጓድ ታወርዳቸዋለህ ደም የተጠሙና አታላዮች የዕድሜያቸውን ግማሽ እንኳ አይኖሩም፡፡ እኔ ግን በአንተ እታመናለሁ፡፡ + +\s5 +\c 56 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ሰዎች ስለሚያጠቁኝና ጠላቶቼም ቀኑን ሙሉ ስለሚያሳድዱኝ ማረኝ፡፡ +\v 2 ጠላቶቼ ቀኑን ሙሉ በላዬ ቆሙ በእብሪት የሚዋጉኝ ብዙ ናቸውና፡፡ + +\s5 +\v 3 እኔ ግን ፍርሃት ሲይዘኝ እምነቴን አንተ ላይ አደርጋለሁ +\v 4 ቃሉን በማመሰግው አምላክ በእግዚአብሔር ታምኛሁና አልፈራም ከቶ ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል? + +\s5 +\v 5 ቀኑን ሙሉ ቃሌን ያጣምማሉ ሐሳባቸው ሁሉ እኔን መጉዳት ነው፡፡ +\v 6 ይዶልታሉ፤ ያደባሉ ሕይወቴ ላይ እንደሚያደቡት ሁሉ ርምጃዬንም ይከታተላሉ፡፡ + +\s5 +\v 7 አምላክ ሆይ፣ በምንም መንገድ እንዲያመልጡ አታድርጋቸው፤ በቁጣህ ሕዝቦችን አዋርዳቸው፡፡ +\v 8 የመንከራተት ቀኖቼን ቆጥረሃል እንባዎቼን በመያዣህ አኑረሃል፡፡ ሁሉስ በመጽሐፍህ ያለ አይደለምን? + +\s5 +\v 9 ወደ አንተ በተጣራሁ ቀን ጠላቶቼ ወደ ኋላቸው ይመለሳሉ፡፡ በዚህም እግዚአብሔር ከእኔ ጋር መሆኑን በእርግጥ ዐወቅሁ፡፡ +\v 10 ቃሉን በማመሰግነው አምላክ ቃሉን በማመመሰግነው ያህዌ +\v 11 በአምላክ ታምኛለሁና አልፈራም፤ ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል? + +\s5 +\v 12 አምላኬ ሆይ፣ የተሳልሁትን እፈጽማለሁ ለአንተም የምስጋና መሥዋዕት አቀርባለሁ፡፡ +\v 13 ነፍሴን ከሞት፣ እግሬን ከመሰናከል አድነሃልና በሕያዋን ብርሃን፣ በእግዚአብሔር ፊት እመላለሳለሁ፡፡ + +\s5 +\c 57 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ ማረኝ አቤቱ ማረኝ የመከራው ጊዜ እስኪያበቃ ድረስ አንተን መጠጊያ አድርጌአለሁና፡፡ ጥፋት እስኪያልፍ ድረስ በክንፎችህ እጠለላለሁ፡፡ + +\s5 +\v 2 ወደ ልዑል እግዚአብሔር የሚያስፈልገኝን ሁሉ ወደሚሰጠኝ አምላክ እጮኻለሁ፡፡ +\v 3 ከሰማይ ልኮ ያድነኛል የሚያስጨንቁኝንም ያዋርዳቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ፍቅሩንና ታማኝነቱን ይልካል፡፡ + +\s5 +\v 4 ነፍሴ በአንበሶች ተከባለች፣ ሊውጡኝ በተዘጋጁ መካከል ወድቄአለሁ፡፡ እነዚህ ሰዎች ጥርሳቸው ጦርና ፍላጻ ምሳቸውም የተሳለ ሰይፍ ነው፡፡ +\v 5 እግዚአብሔር ሆይ፣ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ይስፋፋ + +\s5 +\v 6 ለእግሬ ወጥመድ ዘረጉ፣ ነፍሴንም አጐበጡአት፤ መንገዴ ላይ ጉድጓድ ቆፈሩ፤ ነገር ግን ራሳቸው ገቡበት፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 7 ልቤ ጽኑ ነው፤ እግዚአብሔር ሆይ ልቤ ጽኑ ነው እቀኛለሁ፤ እዘምራለሁ፡፡ +\v 8 ነፍሴ ሆይ፣ ንቂ በገናና መሰንቆም ተነሡ እኔም በማለዳ እነሣለሁ፡፡ + +\s5 +\v 9 ጌታ ሆይ፣ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ በመንግሥታት መካከል ምስጋና እዘምራለሁ፡፡ +\v 10 ዘላለማዊ ፍቅርህ ከሰማያት በላይ ነው ታማኝነትህም እስከ ደመናት ይደርሳል፡፡ +\v 11 እግዚአብሔር ሆይ፣ ከሰማያት በላይ ከፍ በል ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ይስፋፋ፡፡ + +\s5 +\c 58 +\p +\v 1 እናንተ ገዢዎች እውነትን ትናገራላችሁ? እናንተ ሰዎች ቅን ፍርድ ትፈርዳላችሁ? +\v 2 የለም፤ በልባችሁ ክፋት ታውጠነጥናላችሁ በእጃችሁም በምድር ሁሉ ላይ በደል ትፈጽማላችሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 ክፉዎች በእናታቸው ማሕፀን እያሉ እንኳ ከመንገድ የወጡ ናቸው ሲወለዱ ጀምሮ የተሳሳቱና ውሸታሞች ናቸው፡፡ +\v 4 መርዛቸው እንደ እባብ መርዝ ነው +\v 5 የአስማተኛውን ቃል አልሰማ እንዳለች እፉኝት ጆሮአቸውን ደፍነዋል፡፡ + +\s5 +\v 6 እግዚአብሔር ሆይ፣ ጥርሳቸውን አፋቸው ውስጥ ስበር የአንበሶችንም መንጋጋ አውላልቅ፡፡ +\v 7 ፈስሶ እንደሚያልቅ ውሃ ይጥፉ የቀስታቸው ፍላጻ ዱልዱም ይሁን፡፡ +\v 8 እየሄደ ሟምቶ እንደሚጠፋ ቀንድ አውጣ፣ ፀሐይ እንደማያይም ጭንጋፍ ይሁኑ፡፡ + +\s5 +\v 9 የሚነደው እሾኽ እሳት ገና ድስታችሁን ሳያሞቀው እርጥቡንም ደረቁንም እኩል በዐውሎ ነፋስ ጠራርጐ ይወስዳቸዋል፡፡ +\v 10 ጻድቃን የእግዚአብሔርን በቀል ሲያዩ ደስ ይላቸዋል እግሩንም በግፈኞች ደም ይታጠባል፡፡ +\v 11 በዚህ ጊዜ ሰዎች፣ «በእርግጥ ለጻድቃን ዋጋ አላቸው፤ በእውነትም በምድር ላይ የሚፈርድ አምላክ አለ» ይላሉ፡፡ + +\s5 +\c 59 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ከጠላቶቼ አድነኝ በእኔ ላይ ከሚነሡ ሰዎችም ጠብቀኝ፡፡ +\v 2 ከክፉ አድራጊዎች ታደገኝ፣ ደም ከተጠሙ ሰዎችም አድነኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 ሕይወቴን ለማጥፋት አድብተዋልና ያህዌ ሆይ፣ ጨካኞች ያለ በደሌ፣ ያለ ኃጢአቴ በላዬ ተሰብስበው ዶለቱብኝ፡፡ +\v 4 ምንም በደል ባይኖርብኝም ተዘጋጅተው መጡብኝ፤ አንተ ግን ሁኔታዬን ተመልከት እኔን ለመርዳትም ተነሥ፡፡ + +\s5 +\v 5 የሰራዊት አምላክ የሆንህ ያህዌ አንተ የእስራኤልም አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝቦችን ለመቅጣት ተነሥ፣ ዐመፀኞችንም ያለ ምሕረት ቅጣቸው፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 6 እንደ ውሻ እያላዘኑ በምሽት ተመልሰው ይመጣሉ በከተማዪቱም ይራወጣሉ፡፡ +\v 7 ከአፋቸው የሚወጣውን ተመልከት ሰይፍ ከንፈራቸው ላይ አለ ደግሞም፣ «ማን ሊሰማን ይችላል?» ይላሉ፡፡ + +\s5 +\v 8 አንተ ያህዌ ግን ትሥቅባቸዋለህ ሕዝቦችን ሁሉ በንቀት ታያቸዋለህ፡፡ +\v 9 እግዚአብሔር ብርታቴ ሆይ አንተን እጠብቃለሁ፤ አምላኬ ሆይ አንተ መጠጊያዬ ነህና፡፡ + +\s5 +\v 10 እግዚአብሔር በምሕረቱ ይገናኘኛል አምላኬ የጠላቶቼን ውድቀት ያሳየኛል፡፡ +\v 11 እግዚአብሔር ጋሻችን ሆይ፣ ሕዝቤ እንዳይረሱ አትግደላቸው፤ በኃይልህ በትናቸው ዝቅ ዝቅም አድርጋቸው፡፡ + +\s5 +\v 12 ከአፋቸው ስለሚወጣው ኃጢአት ከከንፈራቸውም ስለሚሰነዘረው ቃል በትዕቢታቸው ይያዙ፡፡ ከአፋቸው ስለ ወጣው መርገምና ውሸት +\v 13 በቁጣ አጥፋቸው፤ ፈጽመህም አስወግዳቸው፡፡ እግዚአብሔር በያዕቆብና በምድር ዳርቻ ሁሉ ገዢ መሆኑን ይወቁ፡፡ + +\s5 +\v 14 እንደ ውሻ እያላዘኑ፣ በምሽት ተመልሰው ይመጣሉ፤ በከተማዪቱም ዙሪያ ይራወጣሉ፡፡ +\v 15 ምግብ ፍለጋ ይራወጣሉ፤ ካልጠገቡም ያላዝናሉ፡፡ + +\s5 +\v 16 እኔ ግን ስለ ኃይልህ እዘምራለሁ በማለዳም ስለ ዘላለማዊ ፍቅርህ እዘምራለሁ፡፡ አንተ መጠጊያዬ፣ በመከራዬም ቀን ዐምባዬ ነህና፡፡ +\v 17 ብርታቴ ሆይ፣ በዝማሬ አመሰግንሃለሁ፤ እግዚአብሔር መጠጊያዬ የምትወደኝም አምላኬ ነህና፡፡ + +\s5 +\c 60 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ጣልኸኝ፣ ሰባበርኸን፤ ተቆጣኸንም፤ አሁን ግን መልስህ አብጀኝ፡፡ + +\s5 +\v 2 ምድሪቱን አናወጥኃት፣ ፍርክስክስ አደረግኃት፤ ተንገዳግዳለችና ስብራቷን ጠግን፡፡ +\v 3 ሕዝብህን መከራውን አሳየኸው የሚያንገዳግድ ወይን ጠጅ እንድንጠጣም ሰጠኸን፡፡ + +\s5 +\v 4 ከጠላት ቀስት እንዲያመልጡ ለሚፈሩህ ምልክት አደረግህላቸው፡፡ ሴላ +\v 5 የምትወደው ሕዝብህ ከጉዳት እንዲድን በቀኝህ ታደገን፤ መልስም ስጠን፡፡ + +\s5 +\v 6 እግዚአብሔር በመቅደሱ ሆኖ እንዲህ አለ፣ «ሲኬምን እሸነሽናለሁ፤ የሱኮትንም ሸለቆ አከፋፍላለሁ፡፡ +\v 7 ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤ ኤፍሬም የራስ ቁሬ፣ ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው፡፡ + +\s5 +\v 8 ሞዓብ መታጠቢ ገንዳዬ ነው፤ በኤዶም ላይ ጫማየን እወረውራለሁ ፍልስጥኤማውያን ላይ በድል እልል እላለሁ፡፡ +\v 9 ወደ ተመሸገችው ከተማ ማን ያመጣኛል? ማንስ ወደ ኤዶም ይመራኛል? + +\s5 +\v 10 ነገር ግን እግዚአብሔር ሆይ፥ የጣልከን አንተ አይደለህምን? አምላክ ሆይ፥ ከሠራዊታችን ጋር አብረህ አልወጣህም +\v 11 በጠላቶቻችን ላይ ድልን ስጠን የሰው ድጋፍ ከንቱ ነውና። +\v 12 በእግዚአብሔር እርዳታ ድል እንቀዳጃለን እርሱ ጠላቶቻችንን ከእግሩ በታች ይረግጣቸዋል። + +\s5 +\c 61 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ጩኸቴን ስማ ጸሎቴንም አድምጥ፡፡ +\v 2 ልቤ በዛለ ጊዜ ከምድር ዳርቻዎች ወደ አንተ እጣራለሁ ከእኔ ይልቅ ከፍ ወዳለው ዐለት ምራኝ፡፡ +\v 3 አንተ መጠጊያዬ ከጠላትም የምከለልብህ ፅኑ ግንብ ሆነኸኛልና፡፡ + +\s5 +\v 4 በማደሪያህ ለዘላለም ልኑር በክንፎችህም ጥላ ልከለል፡፡ ሴላ +\v 5 እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ ስእለቴን ሰምተሃል ስምህን የሚያከብሩ ሰዎችን ርስት ለእኔ ሰጠህ፡፡ + +\s5 +\v 6 የንጉሡን ዕድሜ አርዝመው ዘመኑንም እስከ ብዙ ትውልዶች ድረስ ጨምርለት፡፡ +\v 7 ለዘላለም በእግዚአብሔር ፊት ይንገሥ፡፡ + +\s5 +\v 8 ስእለቴን በየቀኑ እንድፈጽም ለስምህ ለዘላለም የምስጋና መዝሙር አቀርባለሁ፡፡ + +\s5 +\c 62 +\p +\v 1 ድነቴ የሚመጣው ከእርሱ ስለሆነ እግዚአብሔርን ብቻ በጸጥታ እጠብቃለሁ፡፡ +\v 2 ዐለቴና መድኃኒቴ እርሱ ብቻ ነው መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ ከቶም አልናወጥም፡፡ + +\s5 +\v 3 ሰውን የምታጠቁት እስከ መቼ ነው? ይህን የዘመመ ግድግዳ የተንጋደደ ዐጥር ሁላችሁ ገፍታችሁ ልትጥሉት ትፈልጋላችሁ? +\v 4 እነርሱ የሚፈልጉት እርሱን ከክብሩ ለማዋረድ ስለሆነ በእርሱ ላይ ሐሰት መናገር ይወዳሉ፤ በአፋቸው ይመርቁታል፤ በልባቸው ግን ይረግሙታል፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 5 እግዚአብሔርን ብቻ በጸጥታ እጠብቃለሁ +\v 6 ዐለቴና መድኃኒቴ እርሱ ብቻ ነው፡፡ መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ ከቶም አልናወጥም፡፡ + +\s5 +\v 7 ድነቴና ክብሬ ከእግዚአብሔር ነው እርሱ መጠጊያ ዐምባዬና መሸሸጊያ ነው፡፡ +\v 8 ሰዎች ሆይ፣ ሁልጊዜ በእርሱ ታመኑ በፊቱም ልባችሁን አፍስሱ እግዚአብሔር ለእኛ መጠጊያችን ነውና፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 9 ከዝቅተኛ ወገን መወለድ ከንቱ ነው፣ ከከፍተኛ ወገን መወለድም ሐሰት ነው ሚዛን ላይ ከፍ ብለው ቢታዩም ሁሉም በአንድነት ከነፋስ የቀለሉ ናቸው፡፡ +\v 10 በዝርፊያ አትተማመኑ በቅሚያ በተገኘ ሀብትም ተስፋ አታድርጉ በዚህ አትበለጽጉምና ልባችሁ እነርሱ ላይ አታድርጉ፡፡ + +\s5 +\v 11 እግዚአብሔር አንዴ ተናገረ እኔም ይህን ሁለቴ ሰማሁ፡፡ ኃይል የእግዚአብሔር ነው፡፡ +\v 12 ጌታ ሆይ፣ የኪዳን ታማኝነት የአንተ ነው አንተ ለእያንዳንዱ፣ እንደ ሥራው ትከፍለዋለህ፡፡ + +\s5 +\c 63 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ አምላኬ ነህ! ከልቤ አንተን እሻለሁ ውሃ በሌለበት ደረቅና ጭው ያለ ምድረ በዳ ነፍሴ አንተን ተጠማች ሥጋዬም አንተን ናፈቀች፡፡ +\v 2 ስለዚህ መቅደስህ ውስጥ አየሁህ ኃይልህንና ክብርህንም ተመለከትሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 ታማኝነትህ ከሕይወት ይበልጣልና ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል፡፡ +\v 4 እንግዲህ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ በስምህም እጆቼን አነሣሁ፡፡ + +\s5 +\v 5 ሰው መልካም ምግብ በልቶ እንደሚጠግብ ነፍሴ በአንተ ትረካለች፤ ስለዚህ ደስ እያለኝ የምስጋና መዝሙር አቀርብልሃለሁ +\v 6 በመኝታዬ ሆኜ አስታውስሃለሁ፤ ሌሊቱን ሁሉ የአንተን ነገር አስባለሁ፡፡ + +\s5 +\v 7 አንተ ረዳቴ ነህና በክንፎችህ ጥላ ውስጥ ሐሤት አደርጋለሁ፡፡ +\v 8 ነፍሴ አንተን የሙጥኝ ብላለች ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች፡፡ + +\s5 +\v 9 ነፍሴን ማጥፋት የሚፈልጉ ግን ወደ ምድር ጥልቅ ይወርዳሉ፤ +\v 10 በሰይፍ ይገደላሉ ለቀበሮችም ምግብ ይሆናሉ፡፡ + +\s5 +\v 11 ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል በእግዚአብሔ ስም የሚምሉ ሁሉ ይከብራ የሐሰተኞች አንደበትም ትዘጋለች፡፡ + +\s5 +\c 64 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ድምፄን ስማ የብሶቴን ቃል አድምጥ፤ ከሚያስፈራ የጠላት ዛቻ ሕይወቴን አድናት +\v 2 ከክፉ አድራጊዎች ዐድማ ሰውረኝ ከዐመፀኞችም ሤራ አድነኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 እነርሱ ምላሳቸውን እንደ ሰይፍ ስለዋል መርዘኛ ቃላቸውንም እንደ ፍላጻ ያነጣጥራሉ +\v 4 ካሸመቁበት ቦታ ሆነው ንጹሑን ሰው ይነደፋታል ድንገት ይነድፉታል፤ አይፈሩምም፡፡ + +\s5 +\v 5 ክፉ ዕቅድ ለማውጣት እርስ በርስ ይመካከራሉ፤ ወጥመድ ለመዘርጋትም በምስጢር ይነጋገራሉ፤ «ማንስ ሊያድን ይችላል?» ይባባላሉ፡፡ +\v 6 እነርሱ ክፉ ዕቅድ አወጡ፤ በሐሳባቸውም፣ «በጥንቃቄ ዕቅድ አውጥተናል» ይላሉ፡፡ የሰው ሐሳብና ልብ በጣም ጥልቅ ነው፡፡ + +\s5 +\v 7 እግዚአብሔር ግን በፍላጻው ይነድፋቸዋል እነርሱም በድንገት ይቆስላሉ፡፡ +\v 8 በገዛ ምላሳቸው ያሰናክላቸዋል ጥፋትንም ያመጣባቸዋል የሚያዩአቸው ሁሉ በመገረም ራሳቸውን ይነቀንቃሉ፡፡ +\v 9 የሰው ልጆች ሁሉ ይፈራሉ የእግዚብሔር ያደረገውንም በይፋ ይናገራሉ፡፡ + +\s5 +\v 10 ጻድቅ በያህዌ ደስ ይለዋል፤ እርሱንም መጠጊያው ያደርጋል ልበ ቅኖችም ሁሉ በእርሱ ይመካሉ፡፡ + +\s5 +\c 65 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ በጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል፤ ለአንተ የተሳልነውንም እንፈጽማለን፡፡ +\v 2 ሥጋ ለባሽ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል፡፡ +\v 3 ኃጢአት በርትቶብን በነበረ ጊዜ አንተ መተላለፋችንን ይቅር አልህ፡፡ + +\s5 +\v 4 አንተ የመረጥኸው፣ በአደባባይህም እንዲኖር ወደ አንተ ያቀረብኸው ሰው ቡሩክ ነው፡፡ ከተቀደሰው መቅደስህ፣ ከቤትህም በረከት እንጠግባለን፡፡ + +\s5 +\v 5 የምድር ዳርቻዎችና ከባሕሩ ማዶ ርቀው ያሉ ሁሉ ተስፋ አዳኛችን እግዚአብሔር ሆይ፣ በጽድቅህ ድንቅ አሠራር መልስልን፡፡ + +\s5 +\v 6 በኃይልህ ተራሮችን አጽንተሃል ብርታትንም ታጥቀሃል፡፡ +\v 7 አንተ የባሕሮችን ማስገምገም የማዕበላቸውንም ጩኸት የሕዝቦችንም ውካታ ጸጥ ታሰኛለህ፡፡ + +\s5 +\v 8 ርቀው በምድር ዳርቻዎች ያሉ ካደረግኸው ድንቅ ሥራህ የተነሣ ይደነግጣሉ፡፡ ምሥራቅና ምዕራብ በደስታ እልል እንዲሉ ታደርጋቸዋለህ፡፡ +\v 9 ዝናብ በማዝነብ ምድርን ትጐበኛለህ፤ ፍሬያማ በማድረግም ታበለጽጋታለህ፡፡ ለሰው ልጆች እህልን ይሰጡ ዘንድ የእግዚአብሔር ወንዞች ውሃን የተሞሉ ናቸው፡፡ አንተ እንዲህ እንዲሆን ወስነሃል፡፡ + +\s5 +\v 10 ትልሟን ታረሰርሳለህ ወጣ ገባውን ታስተካክላለህ ዐፈሩን በካፊያ ታለሰልሳለህ ቡቃያዋንም ትባርካለህ፡፡ +\v 11 ለዓመቱ በጐነትህን ታቀዳጀዋለህ፤ ሰረገላህም በረከትን ሞልቶ ይፈስሳል፡፡ +\v 12 የምድረ በዳው ግጦሽ ቦታ እጅግ ለመለመ ኮረብቶችም ደስታን ለበሱ፡፡ + +\s5 +\v 13 መሰማሪያዎች መንጋ በመንጋ ሆኑ ሸለቆዎች በሰብል ተሞሉ እልል እያሉም ዘመሩ፡፡ + +\s5 +\c 66 +\p +\v 1 ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር እልል በሉ +\v 2 ለስሙ ክብር ዘምሩ ምስጋናውን አድምቁ፡፡ + +\s5 +\v 3 እግዚአብሔርን፣ «ሥራህ እንዴት ድንቅ ነው! ከኃይልህ ታላቅነት የተነሣ ጠላቶችህ ይገዙልሃል፡፡ +\v 4 ምድር ሁሉ ያመልክሃል በዝማሬም ያመሰግኑሃል ለስምህም ይዘምራሉ» ባሉት፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 5 ኑ የእግዚአብሔርን ሥራ እዩ ለሰው ልጆ ያደረገውስ አስፈሪ ነው፡፡ +\v 6 ባሕሩን ደረቅ ምድር አደረገው ወንዙን በእግር ተሻገሩ እኛም እርሱ ባደረገው ነገር ደስ ብሎናል፡፡ +\v 7 በኃይሉ ለዘላለም ይነግሣል ዐይኖቹ ሕዝቦችን ይመለከታሉ፡፡ እንግዲህ ዐመፀኞች ቀና ቀና አይበሉ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 8 ሕዝቦች ሁሉ እግዚአብሔርን ባርኩ የምስጋናውንም ድምፅ አሰሙ፡፡ +\v 9 በሕያዋን መካከል አኑሮናል እግራችን እንዲንሸራተት አልፈቀደም፡፡ + +\s5 +\v 10 እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ ፈተንኸን ብር እንደሚፈተን እኛን ፈተንኸን +\v 11 ወደ ወጥመድ አገባኸን በጀርባችንም ከባድ ሸክም ጫንህብን፡፡ +\v 12 ሰዎች ራሳችን ላይ እንዲፈነጩ አደረግህ በእሳትና በውሃ መካከል አለፍን የኃላ ኃላ ግን ወደ ሰፊ ስፍራ አመጣኸን፡፡ + +\s5 +\v 13 የሚቃጠል መሥዋዕት ይዤ ወደ ቤትህ እመጣለሁ ስእለቴንም ለአንተ እከፍላለሁ፡፡ +\v 14 ይህም መከራ በደረሰብኝ ጊዜ ከአፌ የወጣ፣ በከንፈሮቼም የተናገርሁት ስእለት ነው፡፡ +\v 15 የሰቡ እንስሶችን የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጌ፣ እንዲሁም መዓዛው ደስ የሚያሰኝ የአውራ በግ መሥዋዕት አቀርብልሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 16 እናንት እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሁሉ ኑና ስሙ፣ ለነፍሴ ያደረገላትን እነግራችኃለሁ፡፡ +\v 17 በአፌ ወደ እርሱ ጮኽሁ፤ በአንደበቴ አመሰገንሁት፡፡ +\v 18 በውስጤ ኃጢአት ይዤ ቢሆን ኖሮ ጌታ አይሰማኝም ነበር፡፡ + +\s5 +\v 19 አሁን ግን እግዚአብሔር በእርግጥ ሰምቶኛል ጸሎቴንም አድምጦአል፡፡ +\v 20 ጸሎቴን ያልናቀ ምሕረቱንም ከእኔ ያላራቀ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ + +\s5 +\c 67 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ይማረን ይባርከንም ፊቱንም በላያችን ያብራ፡፡ ሴላ +\v 2 መንገድህ በምድር ላይ ማዳንህም በሕዝቦች ሁሉ መካከል ይታወቅ ዘንድ፡፡ + +\s5 +\v 3 እግዚአብሔር ሆይ፣ ሕዝቦች ያመስግኑህ ሰዎች ሁሉ ምስጋና ያቅርቡልህ፡፡ +\v 4 አንተ ለሕዝቦች ቅን ስለምትፈርድላቸው የምድር ሕዝቦችን ስለምትመራ ሕዝቦች ሁሉ ደስ ይበላቸው በእልልታም ይዘምሩ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 5 እግዚአብሔር ሆይ፣ ሕዝቦች ያመስግኑህ ሰዎች ሁሉ ምስጋና ያቅርቡልህ፡፡ +\v 6 ምድር ፍሬዋን ሰጠች አምላካችን እግዚአብሔር ባርኮናል፡፡ + +\s5 +\v 7 እግዚአብሔር ባርኮናል የምድር ዳርቻዎች ሁሉ እርሱን ያከብሩታል፡፡ + +\s5 +\c 68 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ይነሣ የሚጠሉትም ከፊቱ ይበተኑ፡፡ +\v 2 ጢስ እንደሚበንን፣ እንዲሁ አብንናቸው፤ ሰም በእሳት ፊት እንደሚቀልጥ እንዲሁ ክፉች ከእግዚአብሔር ፊት ይጥፉ፡፡ +\v 3 ጻድቃን ግን ደስ ይበላቸው በእግዚአብሔርም ፊት ሐሤት ያድርጉ ደስታንና ሐሤትን ይሞሉ፡፡ + +\s5 +\v 4 ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ለስሙም የምስጋና መዝሙር አቅርቡ በደመናት ላይ የሚሄደውን ከፍ አድርጉት፡፡ ስሙ ያህዌ ነው! በፊቱም ሐሤት አድርጉ፡፡ +\v 5 በተቀደሰ ማደሪያው ያለው አምላክ አባት ለሌላቸው አባት ነው፡፡ ለመበለቶችም ዳኛ ነው፡፡ +\v 6 እግዚአብሔር ብቸኞች በቤተ ሰብ መካከል ያኖራቸዋል፤ እስረኞችን ነጻ አውጥቶ ያስፈነድቃቸዋል፤ ክፉዎች ግን በምድረ በዳ ይኖራሉ፡፡ + +\s5 +\v 7 እግዚአብሔር ሆይ፣ በሕዝብህ ፊት ባለፍህ ጊዜ በምድረ በዳ በተጓዝህ ጊዜ፣ +\v 8 በሲና አምላክ በእግዚአብሔር ፊት ምድር ተንቀጠቀጠች ሰማያትም ዶፍ አወረዱ፡፡ + +\s5 +\v 9 እግዚአብሔር ሆይ፣ በቂ ዝናብ አዘነብህ ደርቆ የነበረውን ርስትህን አረሰረስህ፡፡ +\v 10 ሕዝብህ መኖሪያው አደረጋት፤ እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ ከመልካምነትህ ለድኾች ሰጠህ፡፡ + +\s5 +\v 11 እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ቃሉን ሰጠ ቃሉን የሚያውጁትም ብዙ ሰራዊት ናቸው፡፡ +\v 12-13 የሰራዊት ነገሥታት ፈጥነው ወደ ኋላ ሸሹ፤ በሰፈር የቀሩ ሴቶችም ምርኮ ተከፋፈሉ በበጐች በረት መካከል ብትገኙ እንኳ በቅጠልያ ወርቅ እንደ ተለበጡ ላባዎች ናችሁ፡፡ + +\s5 +\v 14 ሁሉን ቻዩ በዚያ የነበሩትን ነገሥታት በበተነ ጊዜ፣ ከሰልሞን ተራራ እንደሚወርድ በረዶ አደረጋቸው፡፡ +\v 15 አንተ ብርቱ የባሰን ተራራ ሆይ፤ እናንት ባለ ብዙ ጫፍ ተራሮች ሆይ፣ እግዚአብሔር ሊኖርበት የመረጠውን ተራራ፣ በእርግጥ እግዚአብሔር ለዘላለም +\v 16 የሚኖርበትን ተራራ ለምን በምቀኝነት ትመለከቱታላችሁ? + +\s5 +\v 17 የእግዚአብሔር ሰረገላዎች እልፍ አእላፍ ነቸው ሺህ ጊዜም ሺህ ናቸው ጌታ በተቀደሰው ቦታ በሲና በመካከላቸው ነው፡፡ +\v 18 ወደ ላይ ዐረግህ፣ ምርኮን አጋበስህ እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ በዚያ ትኖር ዘንድ ከአንተ ጋር ከተዋጉት እንኳ ሳይቀር፣ ከሰዎች ስጦታን ተቀበልህ፡፡ + +\s5 +\v 19 በየዕለቱ ሸክማችንን የሚሸከምልን መድኃኒታችን የሆነው እግዚአብሔር ይባረክ፡፡ ሴላ +\v 20 አምላካችን የሚያድን አምላክ ነው ከሞት ሊታደገን የሚቻለው ጌታ ያህዌ ነው፡፡ +\v 21 እግዚአብሔር የጠላቶችን ራስ በኃጢአታቸውም የሚጸኑትን ሰዎች ጠጉራም ዐናት ይፈነክታል፡፡ + +\s5 +\v 22 ጌታ እንዲህ አለ፤ «ጠላቶቼን ከባሳን መልሼ አመጣቸዋለሁ፤ ከባሕርም ጥልቅ አውጥቼ አመጣቸዋለሁ፤ +\v 23 እግርህ በጠላትህ ደም እንዲጠልቅ የውሻህም ምላሽ ከጠላትህ ድርሻውን እንዲያገኝ ነው፡፡» + +\s5 +\v 24 አምላክ ሆይ፣ የክብር አካሄድህን፣ አምላኬና ንጉሤ ወደ ቤተ መቅደሱ የሚያደርገውን የክብር አካሄድ አዩ፡፡ +\v 25 የሚጫወቱ ከኋላ ሆነው ሲሄዱ መዘምራን ከፊት፤ መሣሪያ መካከላቸው ከበሮ የሚመቱ ደናግል ነበሩ፡፡ + +\s5 +\v 26 እግዚአብሔርን በጉባኤ አመስግኑት በእውነት የእስራኤል ዘር የሆናችሁ ያህዌን አመስግኑት፡፡ +\v 27 በመጀመሪያ በቁጥር ታናሽ የሆነው የብንያም ነገድ ታየ ቀጥሎም የይሁዳ መሪዎችና ሰራዊቶቻቸው ታዩ፤ በመጨረሻም የዛብሎንና የንፍታሌም መሪዎች ተከተሉ፡፡ + +\s5 +\v 28 እግዚአብሔር ሆይ፣ በቀድሞ ዘመን እንደዳረግኸው ኃይልህን ግለጥ +\v 29 ነገሥታት ስጦታቸውን ከሚያመጡልህ በኢየሩሳሌም ካለው ቤተ መቅደስህ ኃይልህን ግለጥ፡፡ + +\s5 +\v 30 በሸምበቆ መካከል ያሉትን አራዊት ገሥጽ ኮርማዎችና ጥጆች የመሳሰሉትን መንግሥታት ገሥጸቸው፡፡ አዋርዳቸው ስጦታዎች እንዲመጡልህም አድርጋቸው ጦርነትን የሚወዱ ሕዝቦችንም በትናችው፡፡ +\v 31 መሳፍንት ከግብጽ ይመጣሉ፤ ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች፡፡ + +\s5 +\v 32 እናንት የምድር መንግሥታት ለያህዌ የምስጋና መዝሙር አቅርቡ፡፡ ሴላ +\v 33 ከጥንት ጀምሮ ከነበሩት ሰማያት በላይ ለሚራመደው በኃያል ድምፁ ለሚያስገመግመው ዘምሩ፡፡ + +\s5 +\v 34 ግርማው በእስራኤል ላይ ኃይሉም በሰማያት ላይ ስለሆነ የእግዚአብሔርን ኃይል ዐውጁ፡፡ +\v 35 እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ በመቅደስህ ድንቅ ነህ፤ የእስራኤል አምላክ ለሕዝቡ ኃይልና ብርታት ይሰጣል፡፡ እግዚአብሔር ይባረክ! + +\s5 +\c 69 +\p +\v 1 የውሃ ሙላት እስከ አንገቴ ደርሶአልና አምላክ ሆይ አድነኝ፡፡ +\v 2 መቆሚያ ስላጣሁ በጥልቁ ረግረግ ውሃ ለመስጠም ተቃርቤአለሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 ብዙ ከመጮኼ የተነሣ ዛልሁ ጉሮሮየም ደረቀ፤ አምላኬን በመጠባበቅ ዐይኖቼ ፈዘዙ፡፡ +\v 4 ያለ ምክንያት የሚጠሉኝ ከራስ ጠጉሬ ይልቅ በዝተዋል፤ ብዙ ጠላቶቼ እኔን ማጥፋት ይፈልጋሉ ያልሰረቅሁን ነገር መልሰህ አምጣ ተባልሁ፡፡ + +\s5 +\v 5 እግዚአብሔር ሆይ አንተ ሞኝነቴን ታውቃለህ ኃጢአቴም ከአንተ የተሰወረ አይደለም፡፡ +\v 6 የሰራዊት ጌታ ያህዌ ሆይ፣ አንተን ተስፋ የሚያደርጉ በእኔ ምክንያት አይፈሩ፡፡ የእስራኤል አምላክ ሆይ፣ አንተን አጥብቀው የሚሹህ በእኔ ምክንያት አይዋረዱ፡፡ + +\s5 +\v 7 ስለ አንተ ስድብን ታግሼአለሁ እፍረትም ፊቴን ሸፍኖአል፡፡ +\v 8 ለወንድሞቼ እንደ እንግዳ ለእናቴም ልጆች እንደ ባዕድ ሆንሁባቸው፡፡ +\v 9 የቤትህ ቅናት በላችኝ ለአንተ የተሰነዘረው ስድብ እኔ ላይ ዐረፈ፡፡ + +\s5 +\v 10 በምጾምበት ጊዜ በጣም አለቀስሁ እነርሱም ሰደቡኝ፡፡ +\v 11 ማቅ በለበስሁ ጊዜ መተረቻ አደረጉኝ፡፡ +\v 12 በከተማው ቅጥር ለሚቀመጡ የመነጋገሪያ ርእስ ለሰካራሞችም መዝፈኛ ሆንሁ፡፡ + +\s5 +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ እኔ ግን በወደድኸው ሰዓት ወደ አንተ እጸልያለሁ፡፡ በታላቅ ምሕረትህ፣ በማዳንህም ርግጠኝነት መልስልኝ፡፡ +\v 14 ከረግረግ አውጣኝ እንድሰጥምም አትተወኝ፡፡ ከጥልቁ ውሃ ከእነዚያ ከሚጠሉኝም ታደገኝ፡፡ +\v 15 ጐርፍ አያጥለቅልቀኝ ጥልቁ ውሃም አይዋጠኝ ጉድጓዱም ተደርምሶ አይዘጋብኝ፡፡ + +\s5 +\v 16 ያህዌ ሆይ፣ የኪዳንህ ታማኝነት በጐ ናትና ስማኝ እንደ ምሕረትህም ብዛት መልስልኝ +\v 17 ከባርያህ ፊትህን አትሰውር ተጨንቄአለሁና ፈጥነህ መልስልኝ፡፡ + +\s5 +\v 18 ወደ እኔ ቀርበህ አድነኝ ስለ ጠላቶቼም ተቤዠኝ፡፡ +\v 19 የደረሰብኝን ስድብ፣ እፍረትና ውርደት ታውቃለህ ጠላቶቼንም አንድ በአንድ ታውቃቸዋለህ፡፡ + +\s5 +\v 20 ስድብ ልቤን ሰብሮታልና ተስፋ ቆረጥሁ፡፡ የሚያዝንልኝ ፈለግሁ ማንም አልነበረም የሚያጽናናኝም ፈለግሁ ማንንም አላገኘሁም፡፡ +\v 21 ምግቤን ከሐሞት ጋር ቀላቀሉ ለጥማቴም ሆምጣጤ ሰጡኝ፡፡ + +\s5 +\v 22 በፊታቸው የቀረበው ማእድ ወጥመድ ይሁንባቸው ደኅና ነን ሲሉ አሽክላ ይሁንባቸው፡፡ +\v 23 ማየት እንዳይችሉ ዐይናቸው ይጨልም ጀርባቸውም ዘወትር ይጉበጥ፡፡ + +\s5 +\v 24 መዓትህን በላያቸው አፍስስ፤ የቁጣህም መቅሠፍት ድንገት ይድረስባቸው፡፡ +\v 25 መኖሪያቸው ወና ይሁን! በድንኳኖቻቸውም የሚኖር አይገኝ፡፡ + +\s5 +\v 26 አንተ የመታኸውን አሳደዋልና ያቆሰልሃቸውንም ሥቃይ አባብሰዋል፡፡ +\v 27 በበደላቸው ላይ በደልን ጨምርባቸው ወደ ጽድቅህ ድል አይግቡ፡፡ + +\s5 +\v 28 ከሕይወት መጽሐፍ ይደምሰሱ ከጻድቃንም ጋር አይጻፉ፡፡ +\v 29 እኔ ግን ምስኪንና ሐዘነተኛ ነኝና አምላክ ሆይ፣ ማዳንህ ደግፎ ይያዘኝ፡፡ + +\s5 +\v 30 የእግዚአብሔርን ስም በዝማሬ አመሰግናለሁ በውዳሴም ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ፡፡ +\v 31 ከበሬ ይልቅ፣ ቀንድና ጥፍር ካበቀለ እንቦሳ ይበልጥ ይህ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፡፡ + +\s5 +\v 32 ገሮች ይህን ባዩ ጊዜ ደስ ይላቸዋል እናንተ እግዚአብሔርን የምትሹ በርቱ፡፡ +\v 33 ያህዌ ችግረኞችን ይሰማልና በእስራት ያለውንም ሕዝቡን አይንቅም፡፡ + +\s5 +\v 34 ሰማይና ምድር፣ ባሕሮችና በውስጡ የሚንቀሳቀሱ ሁሉ ያመስግኑት፡፡ +\v 35 እግዚአብሔር ጽዮንን ያድናታልና የይሁዳንም ከተሞች መልሶ ይሠራቸዋልና ሕዝቡም በዚያ ይሰፍራል ይወርሷታልም፡፡ +\v 36 የባርያዎቹም ዘሮች ይወርሷታል ስሙንም የሚወዱ በዚያ ይኖራሉ፡፡ + +\s5 +\c 70 +\p +\v 1 አምላክ ሆይ አድነኝ፤ ያህዌ ሆይ፣ ፈጥነህም እርዳኝ፡፡ +\v 2 ሕይወቴን ማጥፋት የሚፈልጉ ይፈሩ ይዋረዱም፤ +\v 3 በእኔ ስቃይ ደስ የሚላቸው ተሸማቅቀው ወደ ኋላ ይመለሱ፡፡ + +\s5 +\v 4 ነገር ግን አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ደስ ይበላቸው ሐሤትም ያድርጉ፤ ማዳንህን የሚወዱ ሁሉ ሁልጊዜ፣ «እግዚአብሔር ታላቅ ነው» ይበሉ፡፡ +\v 5 እኔ ምስኪንና ችግረኛ ነኝ፤ አምላክ ሆይ ፈጥነህ ድረስልኝ፤ አንተ ረዳቴ ታዳጊዬም ነህና ያህዌ ሆይ አትዘግይ፡፡ + +\s5 +\c 71 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ አንተን መጠጊያ አደረግሁ ፈጽሞ አልፈር፡፡ +\v 2 በጽድቅህ ታደገኝ አስጥለኝም ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል አድነኝም፡፡ +\v 3 በምሄድበት ቦታ ሁሉ አንተ መጠጊያ ዐምባ ሁነኝ፡፡ አንተ ዐለቴ፣ ምሽጌ ነህና እኔን ለማዳን ትእዛዝ ከአንተ ይውጣ፡፡ + +\s5 +\v 4 አምላኬ ሆይ፣ ከዐመፀኛ ርኅራኄ ከሌለው ከጨካኝ እጅ ታደገኝ፡፡ +\v 5 ጌታ ያህዌ ሆይ፣ አንተ ተስፋዬ ነህና ከልጅነቴ ጀምሮ በአንተ ታምኛለሁና፡፡ + +\s5 +\v 6 ከተወለድሁ ጀምሮ በአንተ ተደገፍሁ ከእናቴ ማሕፀን ያወጣኸኝም አንተ ነህ ምስጋናዬ ዘወትር ለአንተ ነው፡፡ +\v 7 አንተ ብርቱ መጠጊያየ ስለሆንህልኝ ሕይወቴ ለብዙዎች ምሳሌ ሆነ፡፡ + +\s5 +\v 8 አፌ በምስጋናህ ተሞልቶአል ስለ ክብርህም ቀኑን ሙሉ እናገራለሁ፡፡ +\v 9 በእርጅና ዘመኔ አትጣለኝ ጉልበቴም በደከመ ጊዜ አትተወኝ፡፡ + +\s5 +\v 10 ጠላቶቼ ተነጋግረውብኛልና ሕይወቴን ማጥፋት የሚፈልጉም በእኔ በአንድነት አሢረዋል፡፡ +\v 11 እነርሱም፣ «እግዚአብሔር ትቶታል፣ የሚያስጥለው የለምና ተከታትላችሁ ያዙት» አሉ፡፡ + +\s5 +\v 12 አምላክ ሆይ፣ ከእኔ አትራቅ፣ አምላኬ ሆይ፣ እኔን ለማዳን ፍጠን፡፡ +\v 13 ተቃዋሚዎቼ ይፈሩ፤ ይጥፉም ሊጐዱኝ የሚፈልጉ ይፈሩ ይዋረዱም፡፡ + +\s5 +\v 14 እኔ ግን ዘወትር አንተን ተስፋ አደርጋለሁ በምስጋና ላይ ምስጋና አቀርብልሃለሁ፡፡ +\v 15 ምንም እንኳ ማስተዋል ቢያዳግተኝ አንደበቴ ዘወትር ስለ ጽድቅህና ስለ ማዳንህ ይናገራል፡፡ +\v 16 መጥቼ የጌታ ያህዌን ብርቱ ሥራ ዐውጃለሁ የአንተን ጽድቅ ብቻ እናገራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 17 እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ ከልጅነቴ ጀምረህ አስተማርኸኝ እኔም እስከ ዛሬ ድረስ ድንቅ ሥራህን እናገራለሁ፡፡ +\v 18 አምላክ ሆይ፣ ሳረጅና ስሸብትም አትተወኝ እኔም ኃያልነትህን ለመጪው ትውልድ ብርታህንም ኃላ ለሚነሣ ሕዝብ እናገራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 19 አምላክ ሆይ፣ ጽድቅህ እስከ ሰማያት ከፍ ያለ ነው አንተ ታላላቅ ነገሮችን አድርገሃል አምላክ ሆይ፣ እንደ አንተ ያለ ማን ነው? +\v 20 ብዙ ችግርና መከራ ብታሳየኝም ሕይወቴን እንደ ገና ታድሳለህ፡፡ ከምድር ጥልቅም እንደ ገና ታወጣኛለህ + +\s5 +\v 21 ክብሬን ትጨምራለህ ተመልሰህም ታጽናናኛለህ፡፡ +\v 22 አምላኬ ሆይ፣ ስለ ታማኝነትህ በበገና አመሰግንሃለሁ፤ የእስራኤል ቅዱስ ሆይ፣ በመሰንቆ እዘምርልሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 23 ለአንተ የምስጋና መዝሙር ሳቀርብ፣ ከንፈሮቼ በደስታ ይሞላሉ አንተ ያዳንሃት ነፍሴም እልል ትላለች፡፡ +\v 24 አንደበቴ ቀኑን ሙሉ ስለ ጽድቅህ ያወራል፤ የእኔን መጐዳት የሚፈልጉ አፍረዋልና ተዋርደዋልምና፡፡ + +\s5 +\c 72 +\p +\v 1 እግዚአብአብሔር ሆይ፣ ለንጉሡ ትክክለኛ ፍርድን ለንጉሡም ልጅ ጽድቅህን ስጠው፡፡ +\v 2 እርሱም ሕዝብህን በጽድቅ፣ ይዳኛል ለተቸገሩትም በትክክል ይፈርዳል፡፡ +\v 3 ተራሮች ሰላምን፣ ኮረብቶችም የጽድቅን ፍሬ ያመጣሉ፡፡ + +\s5 +\v 4 ለተቸገረው ሕዝብ ይሟገታል የችግረኞችን ልጆች ያድናል ጨቋኙንም ያደቀዋል፡፡ +\v 5 ፀሐይ እስካለች ድረስ፣ ጨረቃም እስከምትኖርበት ከትውልድ እስከ ትውልድ ድረስ፣ አንተን ያከብራሉ፡፡ + +\s5 +\v 6 በታጨደ መስክ ላይ እንደሚዘንብ ዝናብ ይውረድ እንደ ካፊያም ምድርን ያረስርስ፡፡ +\v 7 በዘመኑ ጽድቅ ይስፈን ጨረቃም ብርሃንዋ በምትሰጥበት ዘመን ሁሉ ብርልጽግና ይብዛለት፡፡ + +\s5 +\v 8 ግዛቱም ከባሕር እስከ ባሕር ከታላቁም ወንዝ እስከ ምድር ዳርቻ ይሁን፡፡ +\v 9 በምድረ በዳ የሚኖሩ በፊቱ ይስገዱ ጠላቶቹም ወደ መሬት ወድቀው ትቢያ ይላሱ፡፡ +\v 10 የተርሴስ ነገሥታትና ደሴቶች ስጦታ ያምጡለት የሳባና የዐረብ ነገሥታት እጅ መንሻ ያቅርቡለት፡፡ + +\s5 +\v 11 ነገሥታት ሁሉ ይስገዱለት ሕዝቦችም ሁሉ ያገልግሉት፡፡ +\v 12 ወደ እርሱ የሚጮኸውን ችግረኛ ሌላ ረዳት የሌለውን ድኻ ይረዳልና፡፡ + +\s5 +\v 13 ለድኻና ለችግረኛ ይራራል ምስኪኖችንም ከሞት ያድናል፡፡ +\v 14 ሕይወታቸውን ከጭቆናና ከግፍ ያድናል ደማቸውም በፊቱ የከበረ ነው፡፡ + +\s5 +\v 15 ዕድሜው ይርዘም፤ ከዐረብ ወርቅ ይምጣለት፤ ዘወትር ይጸልዩለት የእግዚአብሔር በረከት አይለየው፡፡ +\v 16 በምድሪቱ እህል ይትረፍረፍ በተራሮች አናት ያለው ሰብል ይወዛወዝ፡፡ ፍሬው እንደ ሊባኖስ ይንዠርገግ፤ በከተማ ያለውም ሕዝብ እንደ ሜዳ ሣር ይብዛ፡፡ + +\s5 +\v 17 ስሙ ለዘላለም ጸንቶ ይኑር ዝናውም ፀሐይ በሚወጣበት ዘመን ሁሉ ይሰማ፤ ሕዝቦች በእርሱ ይባረኩ ሰዎች ሁሉ ቡሩክ ነህ ይበሉት፡፡ + +\s5 +\v 18 ብቻውን ድንቅ የሚያደርግ የእስራኤል አምላክ ያህዌ ይባረክ፡፡ +\v 19 ክቡር ስሙ ለዘላለም ይባረክ ምድር ሁሉ በክብሩ ትሞላ፡፡ አሜን፤ አሜን +\v 20 የእሴይ ልጅ የዳዊት ጸሎት እዚህ ላይ ተፈጸመ። + +\s5 +\c 73 +\p +\v 1 ልባቸው ንጹሕ ለሆነ ለእስራኤል እግዚአብሔር ቸር ነው፡፡ +\v 2 እኔ ግን እግሬ ሊሰናከል፣ አዳልጦኝም ልወድቅ ጥቂት ቀረኝ፡፡ +\v 3 ክፉዎች ሲሳካላቸው ዐይቼ ቅናት አድሮብኝ ነበር፡፡ + +\s5 +\v 4 እስኪሞቱ ድረስ ሕመም አያውቃቸውም ሰውነታቸውም ጤነኛና ጠንካራ ነው፡፡ +\v 5 እንደ ሌሎች ሰዎች አይጨነቁም በሌሎች ላይ የሚደርሰው ስቃይ እነርሱ ላይ አይደርስም፡፡ + +\s5 +\v 6 ትዕቢት የአንገት ጌጣቸው ነው ግፍን እንደ ልብስ ለብሰውታል፡፡ +\v 7 የሰባ ዐይናቸውም ይጉረጠርጣል፣ ልባቸው ክፉ ሐሳብ ያፈልቃል፡፡ + +\s5 +\v 8 በፌዝና በክፋት ይናገራሉ በእብሪት ተነሣሥተው ሌሎች ላይ ይዝታሉ፡፡ +\v 9 አፋቸውን በሰማይ ያላቅቃሉ አንደበታቸውም ምድርን ያካልላል፡፡ + +\s5 +\v 10 ስለዚህ ሕዝቡ ወደ እነርሱ ይመለሳል ውሃቸውንም በገፍ ይጠጣሉ፡፡ +\v 11 «እግዚአብሔር እንዴት ሊያውቅ ይችላል በልዑልስ ዘንድ ዕውቀት አለ?» ይላሉ፡፡ +\v 12 እንግዲህ ክፉዎች እንደዚህ ናቸው ሁልጊዜ እንደ ተዝናኑ ናቸው በሀብት ላይ ሀብት ይጨምራሉ፡፡ + +\s5 +\v 13 ለካ ልቤን ንጹሕ ያደረግሁት እኔን በየዋህነት የታጠብሁት በከንቱ ኖሮአል! +\v 14 ቀኑን ሙሉ ተሰቃየሁ በየማለዳውም ተቀጣሁ፡፡ +\v 15 እኔ እንደዚህ እናገራለሁ ብል ኖሮ የልጆችህን ትውልድ በከዳሁ ነበር፡፡ + +\s5 +\v 16 እነዚህን ነገሮች ለመረዳት ብሞክርም በጣም ከባድ ሆነብኝ፡፡ +\v 17 ወደ መቅደስህ እስክገባ ድረስ ምንም ማወቅ አልቻልሁም በኋላ ግን በክፉዎች ላይ ምን እንደሚደርስባቸው ተረዳሁ፡፡ + +\s5 +\v 18 በእርግጥ በሚያዳልጥ ስፍራ አኑረሃቸዋል ወድቀው እንዲጠፉም አድርገሃል፡፡ +\v 19 እንዴት ፈጥነው በቅጽበት ጠፉ! በከባድ ድንጋጤ ፈጽመው ወደሙ፡፡ +\v 20 ሰው ከሕልሙ ሲነቃ እንደሚሆነው፣ ጌታ ሆይ፣ አንተም በምትነሣበት ጊዜ፣ እነርሱ በማለዳ እንደሚረሳ ሕልም ይሆናሉ፡፡ + +\s5 +\v 21 ልቤ በጣም ተማረረች፣ እኔም እጅግ ቆሰልሁ፡፡ +\v 22 ስሜት የሌለው አላዋቂ ሆንሁ በፊትህም እንደ እንስሳ ሆንሁ፡፡ + +\s5 +\v 23 ይህም ሆኖ ዘወትር ከአንተ ጋር ነኝ አንተም ቀኝ እጄን ይዘኸኛል፡፡ +\v 24 በምክርህ ትመራኛለህ በመጨረሻም በክብር ትቀበለኛለህ፡፡ + +\s5 +\v 25 በሰማይ ከአንተ በቀር ማን አለኝ? በምድርም ከአንተ ሌላ የምፈልገው የለኝም፡፡ +\v 26 ሥጋዬና ልቤ ደከሙ እግዚአብሔር ግን ለዘላለም የልቤ ብርታትና አለኝታ ነው፡፡ + +\s5 +\v 27 እነሆ፣ ከአንተ የሚርቁ ይጠፋሉ ለአንተ ያልታመኑትንም ታጠፋቸዋለህ፡፡ +\v 28 ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፣ ጌታ ያህዌን መጠጊያዬ አድርጌዋለሁ ሥራህንም ሁሉ እናገራለሁ፡፡ + +\s5 +\c 74 +\p +\v 1 አምላክ ሆይ፣ ለዘላለም የጣልኸን ለምንድነው? በመሰማሪያህ በጐችህስ ላይ ቁጣህ የነደደው ለምንድነው? +\v 2 ከጥንት ጀምሮ የመረጥኸውን ሕዝብ ርስትህ እንዲሆን የዋጀኸውን ነገድ፣ መኖርያህ ያደረግሃትን የጽዮን ተራራን አስብ፡፡ + +\s5 +\v 3 ጠላት ለዘለቄታው ባድማ ያደረገውን መቅደስህ ውስጥ ያወደመውን ሁሉ ተመልከት፡፡ +\v 4 ጠላቶችህ አንተ በመረጥኸው ቦታ መካከል ደነፉ፤ የጦርነት ዓርማቸውንም ምልክት አድርገው በዚያ አቆሙ፡፡ +\v 5 እነርሱ ጥቅጥቅ ባለው ደን ውስጥ እንጨቶችን በመጥረቢያ የሚቆርጥ ሰው ይመስላሉ፡፡ +\v 6 በእደ ጥበብ ያጌጠውን ሥራ ሁሉ፣ በመጥረቢያና በመዶሻ ሰባብረው አደቀቁት፡፡ + +\s5 +\v 7 መቅደስህን አፍርሰው በእሳት አቃጠሉት የስምህን ማደሪ አረከሱ፡፡ +\v 8 በልባቸውም፣ «ገና ሁሉንም እናጠፋቸዋለን!» አሉ፡፡ በምድሪቱ ያሉ የተቀደሱ ቦታዎችን ሁሉ አቃጠሉ፡፡ + +\s5 +\v 9 የምናየው ምልክት የለም ከእንግዲህ ወዲህ ነቢያትም አይኖሩም፤ ይህ እስከ መቼ እንደሚቀጥል ከእኛ መካከል የሚያውቅ የለም +\v 10 አምላክ ሆይ፤ ጠላት የሚሳደበው እስከ መቼ ነው? ባላንጣስ ለዘላለም በስምህ ያላግጣልን? +\v 11 እጅህን፣ ቀኝ እጅህን የምትመልሰው ለምንድነው? ቀኝ እጅህን ከብብትህ አውጥተህ አጥፋቸው፡፡ + +\s5 +\v 12 እግዚአብሔር ሆይ፣ ከጥንት ጀምሮ አንተ ንጉሤ ነህ ማዳንህንም በምድር ላይ አደረግህ፡፡ +\v 13 በኃይልህ ባሕሩን ከፈልህ የባሕሩንም አውሬ ራስ ውሃ ውስጥ ቀጠቀጥህ፡፡ + +\s5 +\v 14 የሌዋታንን ራሶች አደቀቅህ ሥጋውንም በምድረ በዳ ለሚኖሩ ምግብ አድርገህ ሰጠሃቸው፡፡ +\v 15 ምንጮችንና ፈሳሾችን አፈለቅህ ወራጅ ወንዞችን አደረቅህ + +\s5 +\v 16 ቀኑ የአንተ ነው፣ ሌሊቱም የአንተ ነው፤ ፀሐይንና ጨረቃንም በቦታቸው አደረግህ፡፡ +\v 17 የምድር ዳርቻዎችን ሁሉ የወሰንህ አንተ ነህ ክረምትና በጋ እንዲፈራረቁ አደረግህ፡፡ + +\s5 +\v 18 ያህዌ ሆይ፣ ጠላቶችህ በአንተ ላይ መሳለቃቸውን ጅል ሰዎችም ስምህን መዳፈራቸውን ተመልከት፡፡ +\v 19 የርግብህን ነፍስ ለዱር አራዊት አሳልፈህ አትስጥ፤ የተጨቆኑ ሕዝብህንም ለዘላለም አትርሳ፡፡ + +\s5 +\v 20 የምድር ጨለማ ቦታዎች በዐመፅ ተሞልተዋልና ኪዳንህን አስብ፡፡ +\v 21 የተጨቆኑት አፍረው አይመለሱ ችግረኞችና ጭቁኖች ስምህን ያመስግኑ፡፡ + +\s5 +\v 22 አምላክ ሆይ፣ ተነሥ ለክብርህ ተሟገት ከንቱ ሰው ቀኑን ሙሉ አንተ ላይ ማላገጡን ተመልከት፡፡ +\v 23 የባላጋራዎችህን ድንፋታ ዘወትር የሚሰነዝሩትን ስድብ አትርሳ፡፡ + +\s5 +\c 75 +\p +\v 1 አምላክ ሆይ፣ እናመሰግንሃለን ሐልዎትህን ስለ ገለጥህ ምስጋና ለአንተ እንሰጣለን፤ ሰዎች ድንቅ ሥራህን ይናገራሉ፡፡ +\v 2 አንተም እንዲህ አልህ፣ «ለይቼ በወሰንሁት ሰዓት በቅን የምፈርድ እኔ ነኝ፡፡ +\v 3 ምድር ብትናወጥ በውስጧ የሚኖሩትም ቢንቀጠቀጡ እኔ የምድርን መሠረት አጸናለሁ፡፡ ሴላ፡፡ + +\s5 +\v 4 ትዕቢተኞችን፣ አትታበዩ ክፉዎችን ‹አታምፁ› እላቸዋለሁ፤ +\v 5 ቀንድህን ወደ ሰማይ አታንሣ፤ ዐንገትህንም መዝዘህ አትናገር፡፡» +\v 6 ክብር ከምሥራቅ ወይም ከምዕራብ፣ ወይም ከምድረ በዳ አይመጣም፡፡ + +\s5 +\v 7 ነገር ግን አንዱን ዝቅ፣ ሌላውን ከፍ በማድረግ በትክክል የሚፈርድ እግዚአብሔር ነው፡፡ +\v 8 ያህዌ በእጁ የቁጣው ወይን ጠጅ የሞላበት ጽዋ ይዞአል ሲያፈስሰው ክፉዎች ሁሉ ጨልጠው ይጠጡታል፡፡ + +\s5 +\v 9 እኔ ግን ዘወትር ሥራህን እናገራለሁ፤ ለያዕቆብ አምላክም ዝማሬ አቀርባለሁ፡፡ +\v 10 እርሱ «የክፉዎችን ሁሉ ቀንድ እሰብራለሁ፤ የጻድቃን ቀንድ ግን ከፍ ከፍ አደርጋለሁ» ይላል፡፡ + +\s5 +\c 76 +\p +\v 1 እግዚአብሔር በይሁዳ ታወቀ ስሙም በእስራኤል ታላቅ ነው፡፡ +\v 2 ድንኳኑ በሳሌም መኖሪያውም በጽዮን ነው፡፡ +\v 3 በዚያም የቀስቱን ፍላጻዎች ጋሻውን፣ ጦሩንና ሌሎች የጦር መሣሪያዎችን ሰበረ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 4 ጠላቶችህን ካጠፋህበት ተራሮች ስትወርድ ደምቀህ አበራህ፤ ክብርህንም ገለጥህ፡፡ +\v 5 ጀግኖች ተኝተው እያሉ የማረኩትን ተቀሙ ጦረኞችም ሁሉ ዐቅመ ቢስ ሆኑ፡፡ + +\s5 +\v 6 የያዕቆብ አምላክ ሆይ፤ ከተግሣጽህ የተነሣ ፈረሱና ፈረሰኛው ጭልጥ ብለው ተኝተዋል፡፡ +\v 7 መፈራት ያለብህ አንተ ብቻ ነህ፤ በተቆጣህ ጊዜ ፊትህ መቆም የሚችል ማነው? + +\s5 +\v 8 አንተ ከሰማይ ፍርድህን አሰማህ ምድርም ፈርታ ጸጥ አለች +\v 9 አንተ በምድር የተጨቆኑትን ለማዳን ለፍርድ ስትነሣ ዓለም ጸጥ አለ፡፡ + +\s5 +\v 10 በእርግጥ የሰው ልጅ ላይ የሚወርደው ቁጣ ፍርድህ አንተን ያመሰግንሃል ከቁጣ የተረፉትንም ትገታቸዋለህ፡፡ + +\s5 +\v 11 ለአምላካችሁ ለያህዌ ተሳሉ፣ ስእለቱንም አግቡ በእርሱ ዙሪያ ያሉ ሁሉ መፈራት ለሚገባው እጅ መንሻ ያምጡ፡፡ +\v 12 እርሱ የገዦችን መንፈስ ይሰብራል በምድር ነገሥታትም ዘንድ የተፈራ ይሆናል፡፡ + +\s5 +\c 77 +\p +\v 1 ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደ እግዚአብሔር እጮኻለሁ ይሰማኝ ዘንድ ድምፄን ከፍ አድርጌ እግዚአብሔርን እጠራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 2 በመከራዬ ቀን ጌታን ፈለግሁት በሌሊትም ያለ ዕረፍት እጆቼን ዘረጋሁ፤ ነፍሴ አልጽናና አለች፡፡ +\v 3 አምላኬ ሆይ፣ አንተን ባሰብሁ ቁጥር ቃተትሁ ባወጣሁ ባወረድሁ መጠን መንፈሴ ዛለች፡፡ + +\s5 +\v 4 ዐይኖቼ እንዳይከደኑ አደረግህ መናገር እስኪሳነኝ ድረስ ታወክሁ፡፡ +\v 5 የቀድሞውን ዘመን አሰብሁ የድሮውን ዘመን አወጠነጠንሁ፡፡ + +\s5 +\v 6 በሌሊት ዝማሬዬን አስታወስሁ በጥልቅ በማሰብ እየሆነ ያለውን መረዳት ሞከርሁ፡፡ +\v 7 እግዚአብሔር ለዘላለም ጥሎኛልን? ከእንግዲህስ ቸርነት አያደርግልኝምን? + +\s5 +\v 8 የኪዳን ታማኝነቱስ እስከ ወዲያኛው ተሻረን? የተስፋ ቃሉንስ ዘነጋ? +\v 9 እግዚአብሔር ቸርነቱን ረሳ? ወይስ ከቁጣው የተነሣ መራራቱን ትቶአልን? ሴላ + +\s5 +\v 10 እኔም፣ «የልዑል ቀኝ እጅ እንደ ተለወጠ ማሰቤ ይህ የእኔ ደካማነት ነው» አልሁ፡፡ + +\s5 +\v 11 ያህዌ ሆይ፣ ሥራዎችህን ሁሉ አስታውሳለሁ ድሮ ያደረግኸውን ድንቅ ሥራ አስባለሁ፡፡ +\v 12 ሥራዎችህን ሁሉ አሰላሰላለሁ ድንቅ ሥራህን ሁሉ አውጠነጥናለሁ፡፡ + +\s5 +\v 13 አምላክ ሆይ፣ መንገድህ ቅዱስ ነው እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማን ነው? +\v 14 እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ ድንቆችን የምታደርግ አምላክ ነህ በሕዝቦች መካከል ኃይልህን ገለጥህ፡፡ +\v 15 በታላቅ ኃይልህ ለሕዝብህ ለያዕቆብና ለዮሴፍ ልጆች ድል ሰጠሃቸው፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 16 አምላክ ሆይ፣ ውሆች አዩህ ውሆች አንተን አይተው ፈሩ፤ ጥልቆችም ተነዋወጡ፡፡ +\v 17 ደመኖች ውሃ አንጠባጠቡ፡፡ ሰማያት አንጐዳጐዱ ፍላጾችህም ዙሪያውን አንጸባረቁ፡፡ + +\s5 +\v 18 የድምፅህ ነጐድጓድ ዐውሎ ነፋስ ውስጥ አስተጋባ የመብረቅ ብልጭታ ዓለምን አበራ ምድር ራደች ተንቀጠቀጠች፡፡ +\v 19 መንገድህ በባሕር ውስጥ ነው መሄጃህም በታላቅ ውሃ ውስጥ ነው ዱካህንም ማንም አላየም፡፡ +\v 20 በሙሴና በአሮን እጅ ሕዝብህን እንደ በግ መንጋ መራኸው፡፡ + +\s5 +\c 78 +\p +\v 1 ሕዝቤ ሆይ፣ ትምህርቴን ሰሙ የአፌንም ቃል አድምጡ፡፡ +\v 2 አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ ከጥንት ጀምሮ የተሰወረውን ምስጢር እገልጣለሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 ይህም የሰማነውና ያወቅነው አባቶቻችንም የነገሩን ነው፡፡ +\v 4 እኛም ከልጆቻቸው አንደብቀውም ስለ እግዚአብሔር ኃይል ስላከናወናቸውም ታላላቅ ሥራዎችና ስላደረጋቸው ድንቅ ነገሮች ለተከታዩ ትውልድ እንገራለን፡፡ + +\s5 +\v 5 ለያዕቆብ ሥርዐትን መሠረተ ለእስራኤልም ሕግን ደነገገ፡፡ ይህንንም ለሚቀጥለው ትውልድ እንዲያስተምሩ አባቶቻችንን አዘዘ፡፡ +\v 6 ይህም የሚመጣው ትውልድ ሥርዐቱን እንዲያውቅ እነርሱም በተራቸው ለልጆቻቸው ገና ለሚወለዱትም እንዲነግሩ ነው፡፡ + +\s5 +\v 7 እነርሱም በእግዚአብሔር ይታመኑ የእግዚአብሔርን ሥራ አይረሱም ትእዛዞቹንም ይጠብቃሉ፡፡ +\v 8 እንደ ቀድሞ አባቶቻቸው እልኸኛና ዐመፀኛ አይሆኑም፤ እነርሱ እግዚአብሔርን በማመን አልጸኑም ለእግዚአብሔር ታማኝ ሆነው አልኖሩም፡፡ + +\s5 +\v 9 የኤፍሬም ሰዎች የታጠቁ ቀስተኖች ቢሆኑም በጦርነት ቀን ወደ ኃላ ተመለሱ፡፡ +\v 10 የእግዚአብሔርን ኪዳን አልጠበቁም፣ በሕጉ መሠረት መኖርም አልፈለጉም፡፡ +\v 11 ሥራዎቹን ረሱ ያሳያቸውንም ድንቆች ዘነጉ፡፡ + +\s5 +\v 12 በግብፅ ምድር፣ በዞዓር ምድር በአባቶቻቸው ፊት ያደረጋቸውን ድንቆች ዘነጋ፡፡ +\v 13 ባሕሩን ከፍሎ አሻገራቸው ውሃውንም እንደ ግድግዳ አቆመው፡፡ +\v 14 ቀን በደመና፣ ሌሊቱንም ሁሉ በእሳት ብርሃን መራቸው፡፡ + +\s5 +\v 15 በምድረ በዳ ዐለቱን ሰነጠቀ እንደ ባሕር የበዛ ውሃ ሰጣቸው፡፡ +\v 16 ከዐለቱ ምንጭ አፈለቀ ውሃውም እንደ ወንዝ እንዲፈስ አደረገ + +\s5 +\v 17 እነርሱ ግን ኃጢአት ማድረጋቸውን ቀጠሉ፤ በምድረ በዳ በልዑል ላይ ዐመፁ፡፡ +\v 18 የተመኙትን ምግብ በመጠየቅ፣ ሆን ብለው እግዚአብሔርን ተፈታተኑት፡፡ + +\s5 +\v 19 እንዲህ በማለትም በእግዚአብሔር ላይ ተናገሩ፣ «ለመሆኑ፣ እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማዕድ ማዘጋጀት ይችላልን?» +\v 20 ዐለቱን ሲመታው ውሃ ተንዶለዶለ ጅረቶችም ጐረፉ፡፡ ታዲያ፣ እርሱ እንጀራንም መስጠት ይችላል? ለሕዝቡስ ሥጋ ማቅረብ ይችላል? + +\s5 +\v 21 ያህዌ ይህን ሲሰማ እጅግ ተቆጣ በያዕቆብ ላይ እሳት ነደደ በእስራኤልም ላይ ቁጣው ተቀጣጠሉ፡፡ +\v 22 በእግዚአብሔር አላመኑም በእርሱም ማዳን አልተማመኑም፡፡ + +\s5 +\v 23 ሆኖም እርሱ ከላይ ያሉትን ሰማያትን አዘዘ የሰማይንም በሮች ከፈተ +\v 24 ይበሉ ዘንድ ለሕዝቡ መና አዘነበላቸው የሰማይንም ምግብ ሰጣቸው፡፡ +\v 25 ሰዎች የመላእክትን እንጀራ በሉ፡፡ ጠግበው እስከሚተርፍ ድረስ ምግብ ላከላቸው፡፡ + +\s5 +\v 26 የምሥራቅን ነፋስ ከሰማይ አስነሣ የደቡብንም ነፍስ በኃይሉ አመጣ፡፡ +\v 27 ሥጋን እንደ ዐፈር ብዙ ውፎችንም እንደ ባሕር አሸዋ አዘነበላቸው፡፡ +\v 28 ሰፈራቸው መሓል በድንኳኖቻቸውም ዙሪያ አወረደ፡፡ + +\s5 +\v 29 ስለዚህ እስኪጠግቡ ድረስ በሉ አጥብቀው የተመኙትን ሰጣቸው፡፡ +\v 30 ነገር ግን ገና ምኞታቸውን ሳያረኩ፣ ምግቡ ገና አፋቸው ውስጥ እያለ፣ + +\s5 +\v 31 የእግዚአብሔር ቁጣ እነርሱ ላይ ተነሣ የእስራኤልን ኃያላን ሰዎች ገደለ ምርጥ ወጣቶችንም በአጭር ቀጨ፡፡ +\v 32 ይህም ሆኖ፣ ኃጢአት ማድረጋቸውን ቀጠሉ፤ ድንቅ ሥራዎቹንም አላመኑም፡፡ + +\s5 +\v 33 ስለዚህ ዘመናቸውን አሳጠረ ዕድሜያቸውም በሽብር እንዲያልቅ አደረገ፡፡ +\v 34 እርሱ በገደላቸው ጊዜ ፈለጉት ከልባቸው በመሻትም ወደ እርሱ ተመለሱ፡፡ + +\s5 +\v 35 እግዚአብሔር ዐለታቸው፣ ልዑል አምላክ ታዳጊያቸው እንደ ሆነ አስቡ፡፡ +\v 36 ነገር ግን በአፋቸው ሸነገሉት በአንደበታቸውም ዋሹት፡፡ +\v 37 ልባቸው በእርሱ የጸና አልነበረም ለኪዳኑም ታማኞች አልነበሩም፡፡ + +\s5 +\v 38 እርሱ ግን መሐሪ ስለሆነ ኃጢአታቸውን ይቅር አለ፤ እነርሱንም አላጠፋም ቁጣውን ብዙ ጊዜ ገታ መዐቱንም አላወረደም፡፡ + +\s5 +\v 39 ካለፈ በኋላ እንደማይመለስ ነፋስ ሥጋ ለባሾች መሆናቸውን አሰበ፡፡ +\v 40 በምድረ በዳ ስንት ጊዜ ዐመፁበት በበረሐስ ምን ያህል አሳዘኑት! +\v 41 ደግመው ደጋግመው እግዚአብሔርን ተፈታተኑት የእስራኤልንም ቅዱስ አስቆጡት፡፡ + +\s5 +\v 42 ኃይሉን አላሰቡም፣ እነርሱን ከጠላቶቻቸው እጅ ያዳነበትን፣ ቀንና ታላቁን ኃይሉን አላስታወሱም፡፡ +\v 43 በግብፅ አገር፣ በዞዓር ሜዳ ያደረጋቸውን ታላላቅ ድንቆችና ምልክቶች ዘነጉ፡፡ + +\s5 +\v 44 ከወንዞቻቸው ወሃ መጠጣት እንዳይችሉ የግብፃውያንን ወንዞች ወደ ደም ለወጠ፡፡ +\v 45 ተናዳፊ የዝንብ ሰራዊት ሰደደባቸው፣ ጓጉንቸርም ላከባቸው፤ ምድራቸውንም አጠፋ፡፡ +\v 46 ሰብላቸውን ለኩብኩባ፣ ምርታቸውንም ለአንበጣ ሰጠ፡፡ + +\s5 +\v 47 የወይን ተክላቸውን በበረዶ የበለስ ዛፎቻቸውንም በውርጭ አጠፋ፡፡ +\v 48 ከብቶቻቸውን በበረዶ በጐቻቸውንም በመብረቅ ገደለ፡፡ +\v 49 ጽኑ ቁጣውን በላያቸው ሰደደ መዓቱን፣ የቅናቱንም ቁጣና መቅሠፍት ላከባቸው አጥፊ የመላእክት ሰራዊትም ሰደደባቸው፡፡ + +\s5 +\v 50 ለቁጣው መንገድ አዘጋጀ፤ ከሞትም አላዳናቸውም፡፡ ነገር ግን ሕይወታቸውን ለመቅሠፍት አሳልፎ ሰጠ፡፡ +\v 51 የዐፍላ ጉልበታቸው መጀመሪያ የሆኑትን በካም ድንኳኖች፣ በኩሮቻቸውንም ሁሉ በግብፅ ምድር ፈጀ፡፡ + +\s5 +\v 52 ሕዝቡን ግን እንደ በግ አሰማራቸው በምድረ በዳ እንደ መንጋ መራቸው +\v 53 በሰላም ስለ መራቸው አልፈሩም ጠላቶቻቸውን ግን ባሕር ዋጣቸው፡፡ + +\s5 +\v 54 ከዚያም ወደ ተቀደሰች ምድሩ፣ ቀኝ እጁም ወዳስገኘው ወደዚህ ተራራ አመጣቸው፡፡ +\v 55 ሕዝቦችን ከፊታቸው አባረረ ምድራቸውንም ርስት አድርጐ አከፋፈላቸው፡፡ የእስራኤል ነገዶችን በጠላቶቻቸው ድንኳን አኖረ፡፡ + +\s5 +\v 56 እነርሱ ግን አምላክን ተፈታተኑት በልዑልም ላይ ዐመፁ፤ ትእዛዞቹንም አልጠበቁም፡፡ +\v 57 እንደ አባቶቻቸው ዐመፀኞችና ከዳተኞች ሆኑ፡፡ እንደማያስተማምን ጠማማ ቀስት ተወላገዱ፡፡ + +\s5 +\v 58 በኮረብታ ማምለኪያዎቻቸው አስቆጡት በጣዖቶቻቸውም አስቀኑት፡፡ +\v 59 እግዚአብሔር በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ እስራኤልንም ፈጽሞ ተወ፡፡ + +\s5 +\v 60 በሰዎች መካከል የኖረባትን ድንኳን፣ በሴሎ የነበረች ማደሪያውን ተዋት፡፡ +\v 61 የኃይሉን ምልክት አስማረካት፣ ክብሩንም ለጠላቶች እጅ አሳልፎ ሰጠ፡፡ + +\s5 +\v 62 ሕዝቡን ለሰይፍ ዳረገ በርስቱም ላይ እጅግ ተቆጣ፡፡ +\v 63 ጐልማሶቻቸውን እሳት በላቸው ለልጃገረዶቻቸውም የሰርግ ዘፈን አልተዘፈነላቸውም፡፡ + +\s5 +\v 64 ካህናቶቻቸው በሰይፍ ተገደሉ መበለቶቻቸው ማልቀስ ተሳናቸው፡፡ +\v 65 ጌታም ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ የወይን ጠጅ ጠጥቶ ድፍረት እንደሚሰማው ጀግና ሆነ፡፡ +\v 66 ጠላቶቹን መትቶ ወደ ኋላ መለሳቸው የዘላለም ውርደትንም አከናነባቸው፡፡ + +\s5 +\v 67 የዮሴፍን ድንኳን ተዋት፣ የኤፍሬምንም ነገድ አልመረጠም፡፡ +\v 68 ነገር ግን የይሁዳን ነገድና የወደዳትን የጽዮን ተራራ መረጠ፡፡ +\v 69 መቅደሱን እንደ ሰማያት፣ እርሱ ለዘላለም እንደ መሠረታት ምድር ሠራት፡፡ + +\s5 +\v 70 ባርያውን ዳዊትን መረጠ ከበጐች ጉረኖ ወሰደው፤ +\v 71 ለሕዝቡ ለያዕቆብ፣ ለርስቱም ለእስራኤል እረኛ ሊደርገው የሚያጠቡ በጐችን ከመከተል አመጣው፡፡ +\v 72 ዳዊትም በፍጹም ቅንነት ጠበቃቸው፤ በእጁ ብልኃትም መራቸው፡፡ + +\s5 +\c 79 +\p +\v 1 አምላክ ሆይ፣ ባዕድ ሕዝቦች ርስትህን ወረሩ! የተቀደሰ መቅደስህን አረከሱ ኢየሩሳሌምን የፍርስራሽ ክምር አደረጓት፡፡ +\v 2 የባሪያዎችህን ሬሳ ለሰማይ ወፎች፣ የታማኞችህን ሥጋ ለምድር አራዊት ምግብ እንዲሆን ሰጡ፡፡ +\v 3 ደማቸውን በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውሃ አፈሰሱ የሚቀብራቸውም አልተገኘም፡፡ + +\s5 +\v 4 እኛም ለጐረቤቶቻችን መዘባበቻ በዙሪያችን ላሉትም መሣቂያ መሣለቂያ ሆንን፡፡ +\v 5 ያህዌ ሆይ፣ ይህ እስከ መቼ ነው? የምትቆጣው ለዘላለም ነውን? ቅናትህ እንደ እሳት ሲነድ ይኖራልን? + +\s5 +\v 6 አንተን በማያውቁ ሕዝቦች ላይ፣ ስምህን በማይጠሩ መንግሥታት ላይ መዓትህን አፍስስ፤ +\v 7 ያዕቆብን ውጠውታልና መኖሪያ ቦታውንም ባድማ አድርገዋል፡፡ + +\s5 +\v 8 የአባቶቻችንን ኃጢአት እኛ ላይ አትቁጠርብን እጅግ ተዋርደናልና ምሕረትህ ፈጥና ወደ እኛ ትምጣ፡፡ +\v 9 መድኃኒታችን እግዚአብሔር ሆይ፣ ስለ ስምህ ክብር ርዳን፤ ይቅርም በለን፡፡ + +\s5 +\v 10 ሕዝቦች፣ «አምካቸው የት አለ?» ለምን ይበሉ? ስለ ፈሰሰው የባሪያዎችህ ደም፣ ዐይናችን እያየ ሕዝቦችን ተበቀል፡፡ +\v 11 የእስረኞች ሰቆቃ ወደ አንተ ይድረስ በኃይልህ ብርታት ሞት የተፈረደባቸውን አድን፡፡ + +\s5 +\v 12 ጌታ ሆይ፣ ጐረቤቶቻችን አንተ ላይ ስለ ሰነዘሩት ስድብ ሰባት ዕጥፍ ተበቀላቸው፡፡ +\v 13 እኛ ሕዝብህ፣ የመሰማሪያ በጐችህ ለዘላለም ምስጋና እናቀርብልሃለን፡፡ ለትውልድ ሁሉ ምስጋናህን እንናገራለን፡፡ + +\s5 +\c 80 +\p +\v 1 ዮሴፍን እንደ በግ መንጋ የምትመራ፣ የእስራኤል እረኛ ሆይ፣ ስማን፡፡ በኪሩቤል ላይ ባለው ዙፋን የምትቀመጥ ሆይ፣ ብርሃንህ ይብራልን! +\v 2 በኤፍሬም፣ በብንያምና በምናሴ ፊት ኃይልህን ግለጥ፤ መጥተህም አድነን፡፡ +\v 3 አምላክ ሆይ፣ መልሰን ፊትህን አብራልን እኛም እንድናለን፡፡ + +\s5 +\v 4 የሰራዊት ጌታ ያህዌ ሆይ፣ በሕዝብህ ጸሎት ላይ የምትቆጣው እስከ መቼ ነው? +\v 5 የእንባ እንጀራ አበላሃቸው ስፍር የሞላ እንባም አጠጣሃቸው፡፡ +\v 6 የጐረቤቶቻችን መከራከሪያ አደረግኸን ጠላቶቻችንም ተሣሣቁብን፡፡ + +\s5 +\v 7 የሰራዊት አምላክ ሆይ፣ ፊትህን አብራልን እኛም እንድናለን፡፡ +\v 8 የወይን ግንድ ከግብፅ አመጣህ አሕዛብን አባርረህ እርሷን ተከልህ፡፡ + +\s5 +\v 9 መሬቱን መነጠርህላት፣ እርሷም ሥር ሰድዳ መሬቱን ሞላች፡፡ +\v 10 ተራሮችም በጥላዋ ተሸፈኑ የቅርንጫፎቿም ጥላ የሊባኖስን ዛፎች ሸፈነ፡፡ +\v 11 ቅርንጫፎቿን እስከ ባሕሩ ቁጥቋጦዋንም እስከ ኤፍራጥስ ወንዝ ዘረጋች፡፡ + +\s5 +\v 12 ታዲያ፣ አላፊ፣ አግዳሚው ፍሬዋን እንዲቀጥፍ በዙሪያዋ የነበሩ አጥሮችን ለምን አፈረስህ፡፡ +\v 13 የዱር አሳማ ያበላሻታል በሜዳ የሚንጋጋም አራዊት ይበላታል፡፡ + +\s5 +\v 14 የሰራዊት አምላክ ሆይ፣ ወደ እኛ ተመለስ፣ ከሰማይ ተመልከት እይም ይህችን የወይን ተክልም ተንከባከባት፡፡ +\v 15 ይህች ቀኝ እጅህ የተከላት ተክል አንተም ያጸደቅሃት ተክል ናት፡፡ +\v 16 ነገር ግን ቆራርጠው በእሳት አቃጠሏት ከቁጣህ የተነሣ ይጠፋሉ፡፡ + +\s5 +\v 17 እጅህ የቀኝ እጅህ የሆነው ሰው ላይ፣ አንተ ራስህ ብርቱ ያደረግኸው የሰው ልጅ ላይ ትሁን +\v 18 እኛም ከአንተ ወደ ኋላ አንልም፤ በሕይወት ጠብቀን፤ እኛም ስምህን እንጠራለን፡፡ + +\s5 +\v 19 ሰራዊት አምላክ ያህዌ ሆይ፣ መልሰን ፊትህን አብራልን እኛም እንድናለን፡፡ + +\s5 +\c 81 +\p +\v 1 ብርታታችን ለሆነው አምላክ በደስታ ዘምሩ ለያዕቆብ አምላክ በደስታ እልል በሉ፡፡ +\v 2 ለመዘመር ተነሡ፤ ከበሮም ምቱ በበገናና በመሰንቆ ደስ የሚል ዜማ አሰሙ፡፡ +\v 3 በሙሉ ጨረቃ በክብረ በዓላችን ቀን በወሩ መግቢያ ጨረቃ ስትወለድ ቀንደ መለከት ንፉ፡፡ + +\s5 +\v 4 ይህም ለእስራኤል የተደነገገ፣ የያዕቆብ አምላክ የሰጠው ሥርዐት ነው፡፡ +\v 5 ግብፅን ለቅቆ በወጣ ጊዜ ይህን ለዮሴፍ ደነገገ፤ በማላውቀውም ቋንቋ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤ + +\s5 +\v 6 «ከትከሻው ሸክምን አስወገድሁ እጆቹንም ቅርጫት ከመያዝ አሳረፍሁ፡፡ +\v 7 በመከራህ ጊዜ ጠራኸኝ፤ እኔም ረዳሁህ በነጐድጓድ መሰወሪያ ውስጥ መለስሁልህ በመሪባ ውሃ ዘንድ ፈተንሁህ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 8 ሕዝቤ ሆይ፣ ሳስጠነቅቅህ ስማኝ እስራኤል ሆይ፣ ምነው ባደመጥኸኝ! +\v 9 ባዕድ አምላክ በመካከልህ አይሁን ሌሎች አማልክት አታምልክ፡፡ +\v 10 እኔ ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ አምላክህ ያህዌ ነኝ፡፡ አፍህን በሰፊው ክፈት፤ እኔም እሞላዋለሁ፡፡ + +\s5 +\v 11 ሕዝቤ ግን ቃሌን አልሰማም እስራኤልም ለእኔ አልታዘዝም፡፡ +\v 12 ስለዚህ በእልከኝነት መንገዳቸው እንዲሄዱ፣ የፈለጉትንም እንዲያደርጉ ተውኳቸው፡፡ + +\s5 +\v 13 ምነው ሕዝቤ ባደመጠኝ ኖሮ፣ እስራኤል በመንገዴ ሄዶ ቢሆን ኖሮ፡፡ +\v 14 ፈጥኜ ጠላቶቻቸውን አስገዛላቸው ነበር እጄንም በጨቋኞቻቸው ላይ ባነሣሁ ነበር፡፡ + +\s5 +\v 15 ያህዌን የሚጠሉ በፊቱ በፍርሃት ይሸማቀቃሉ! ለዘላለምም ያፍራሉ፡፡ +\v 16 እስራኤልን ግን ምርጡን ስንዴ አበላዋለሁ ከዐለት ከሚገኘውም ማር አጠግባችኋለሁ፡፡» + +\s5 +\c 82 +\p +\v 1 እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ ቆመ፤ በአማልክትም ላይ፣ ይፈርዳል እንዲህም ይላል፤ +\v 2 ፍትሕ የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው? ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ + +\s5 +\v 3 ለድኾችና ለሙት ልጆች ተሟገቱ፤ የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ፡፡ +\v 4 ድኾችንና ምስኪኖችን ታደጉ፤ ከዐመፀኞችም እጅ አስጥሏቸው፡፡ + +\s5 +\v 5 ዕውቀትም ሆነ ማስተዋል የላቸውም በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ የምድር መሠረቶችም ተናወጡ፡፡ + +\s5 +\v 6 እኔም፣ «እናንተ አማልክት ናችሁ፤ ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ አልሁ፡፡ +\v 7 ሆኖም፣ እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ፡፡» + +\s5 +\v 8 እግዚአብሔር ሆይ፣ ተነሥ፤ ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና፤ በምድር ላይ ፍረድ፡፡ + +\s5 +\c 83 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ዝም አትበል አትተወን ችላ አትበል፡፡ +\v 2 ጠላቶችህ እንዴት እንደ ተነሣሡ ባላንጣዎችህም እንዴት ራሳቸውን ቀና ቀና እንዳደረጉ ተመልከት፡፡ + +\s5 +\v 3 በሕዝብህ ላይ ያደባሉ፣ አንተ በምትጠብቃቸውም ላይ ያሣራሉ፡፡ +\v 4 ‹የእስራኤል ስም ከእንግዲህ እንዳይታሰብ፣ ኑና ሕዝብ እንዳይሆኑ እንደምስሳቸው» አሉ፡፡ +\v 5 በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ተማከሩ አንተም ላይ ተማማሉ፡፡ + +\s5 +\v 6 የኤዶምና የእስማኤላውያን፣ የሞዓብና የአጋራውያን ድንኳኖች፣ +\v 7 ጌባል አሞንና አማሌቅ፣ ፍልስጥኤምም ከጢሮስ ሕዝብ ጋር አብረው ዶለቱ፡፡ + +\s5 +\v 8 አሦርም ከእነርሱ ጋር ተባበረ የሎጥም ልጆች ረዳት ሆነ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 9 ምድያም ላይ እንዳደረግኸው አድርግባቸው በቂሶን ወንዝ በሲሣራና በኢያቢስ ላይ ያደረስኸው ይድረስባቸው፡፡ +\v 10 እነርሱ በዐይንዶር ጠፉ እንደ ምድር ትቢያ ሆኑ፡፡ + +\s5 +\v 11 እንደ ሔሬብና እንደ ዜብ፣ መሳፍንቶቻቸውንም እንደ ዛብሄልና እንደ ስልማና አድርጋቸው፤ +\v 12 እነርሱም፣ «የእግዚአብሔርን ግጦሽ ቦታ እንውሰድ» አሉ፡፡ + +\s5 +\v 13 አምላኬ ሆይ፣ በዐውሎ ነፋስ እንደሚወሰድ ትቢያ፣ ነፋስ ፊት እንዳለ ገለባ አድርጋቸው፡፡ +\v 14 እሳት ደንን እንደሚያቃጥል ተራራውን እንደሚያዳርስ እሳት ነበልባል +\v 15 እንዲሁ በማዕበልህ አሳዳቸው በሞገድህም አስደንግጣቸው፡፡ + +\s5 +\v 16 አምላኬ ያህዌ ሆይ፣ ስምህን ይሹ ዘንድ፣ ፊታቸውን በእፍረት ሙላ፤ +\v 17 ለዘላለም ይፈሩ ይታወኩም፤ በውርደትም ይጥፉ፡፡ + +\s5 +\v 18 ስምህ ያህዌ የሆነው አንተ ብቻ በምድር ላይ ልዑል እንደ ሆንህ ይወቁ፡፡ + +\s5 +\c 84 +\p +\v 1 የሰራዊት ጌታ ያህዌ ሆይ፣ ማደሪያህ ምንኛ ያማረ ነው፡፡ +\v 2 ነፍሴ የያህዌን አደባባዮች ትናፍቃለች እጅግም ትጓጓለች፡፡ ልቤና ሁለንተናዬ ሕያው እግዚአብሔርን ይጣራሉ፡፡ + +\s5 +\v 3 ንጉሤና አምላኬ የሰራዊት አምላክ ሆይ፣ መሠዊያህ ባለበት ስፍራ ድንቢጥ እንኳ መኖሪያ ቤት ዋኖስም ጫጩቶችዋን የምታኖርበት ቦታ አገኘች፡፡ +\v 4 በቤትህ የሚኖሩ የተባረኩ ናቸው፤ እነርሱ ለዘላለም ያመሰግኑሃል፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 5 አንተን ብርታታቸው ያደረጉ በልባቸው የጽዮንን መንገድ የሚያስቡ ቡሩካን ናቸው፡፡ +\v 6 በልቅሶ ሸለቆ በሚያልፉበት ጊዜ የሚጠጡት የምንጭ ውሃ ያገኛሉ የበልግም ዝናብ ይሞላዋል፡፡ + +\s5 +\v 7 ከኃይል ወደ ኃይል ይሸጋገራሉ እያንዳንዱም በጽዮን ባለው አምላክ ፊት ይቀርባል፡፡ +\v 8 የሰራዊት አምላክ ያህዌ ሆይ፣ ጸሎቴን ስማ፣ የያዕቆብ አምላክ ሆይ፣ ቃሌን አድምጥ፡፡ ሴላ +\v 9 አምላክ ሆይ፣ ጋሻችንን ጠብቅ፣ ለቀባኸውም ራራለት፡፡ +\v 10 በሌላ ቦታ ሺህ ቀን ከመኖር፣ አንዲት ቀን በአደባባይህ መዋል ይሻላል፡፡ + +\s5 +\v 11 አምላካችን ያህዌ ፀሐይና ጋሻችን ነውና፤ ያህዌ ጸጋንና ክብርን ይሰጣል፤ በቅንነት የሚሄዱትን መልካም ነገር አይነፍጋቸውም፡፡ +\v 12 የሰራዊት ጌታ ያህዌ ሆይ፣ በአንተ የተማመነ ሰው ቡሩክ ነው፡፡ + +\s5 +\c 85 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ለምድርህ ሞገስ አሳየህ የያዕቆብን ምርኮ መለስህ፡፡ +\v 2 የሕዝብህን ኃጢአት ይቅር አልህ በደላቸውንም ሸፈንህ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 3 መዓትህን ሁሉ አራቅህ ከጽኑ ቁጣህም ተመለስህ፡፡ +\v 4 አዳኛችን እግዚአብሔር ሆይ፣ መልሰን፤ በእኛ ያዘንህብንን ሁሉ አርቅልን፡፡ +\v 5 የምትቆጣን ለዘላለም ነውን? ቁጣህንስ ከትውልድ ወደ ትውልድ ታስተላልፋለህን? + +\s5 +\v 6 እኛ ሕዝብህ በአንተ ደስ እንዲለን እንደ ገና በሕይወት አታኖረንምን? +\v 7 ያህዌ ሆይ፣ የኪዳን ታማኝነትህን አሳየን ማዳንህንም ስጠን፡፡ + +\s5 +\v 8 ያህዌ አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤ እንደ ገና በስሕተት መንገድ ካልሄዱ በቀር ለሕዝቡና ለታማኞቹ ሰላምን ያደርጋል፡፡ +\v 9 ክብሩ በምድራችን ይኖር ዘንድ ማዳኑ ለሚፈሩት በእርግጥ ቅርብ ነው፡፡ + +\s5 +\v 10 ምሕረትና ታማኝነት ተገናኙ፡ ጽድቅና ሰላም ተሳሳሙ፡፡ +\v 11 ታማኝነት ከምድር በቀለች ጽድቅ ከሰማይ ተመለከተች፡፡ + +\s5 +\v 12 ያህዌ መልካም ነገር ይሰጣል ምድራችንም ፍሬዋን ትሰጣለች፡፡ +\v 13 ጽድቅ በፊቱ ትሄዳለች ለአረማመዱም መንገድ ያዘጋጃል፡፡ + +\s5 +\c 86 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ እኔ ድኻና ምስኪን ነኝና እባክህ ስማኝ መልስልኝም፡፡ +\v 2 እኔ ለአንተ ታማኝ ስለሆንሁ ጠብቀኝ አምላኬ ሆይ፤ በአንተ የታመነውን ባርያህን አድነው፡፡ + +\s5 +\v 3 ጌታ ሆይ፣ ቀኑን ሙሉ ወደ አንተ እጮኻለሁና እባክህ ማረኝ፡፡ +\v 4 ጌታ ሆይ፣ ወደ አንተ እጸልያለሁና ባርያህን ደስ አሰኘው፡፡ + +\s5 +\v 5 ጌታ ሆይ፣ አንተ መልካምና ይቅር ባይ ነህ ለሚጠሩህ ሁሉ ምሕረትህ ወሰን የለውም፡፡ +\v 6 ያህዌ ሆይ ጸሎቴን አድምጥ የልመናዬንም ጩኸት ስማ፡፡ +\v 7 አንተ ስለምትመልስልኝ በመከራዬ ቀን ወደ አንተ እጣራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 8 ጌታ ሆይ፣ ከአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ የለም፡፡ ከአንተ ሥራ ጋር የሚወዳደር ሥራ የለም፡፡ +\v 9 ጌታ ሆይ፣ የሠራሃቸው ሕዝቦች ሁሉ መጥተው በፊት ይሰግዳሉ፡፡ ስምህን ያከብራሉ፡፡ + +\s5 +\v 10 አንተ ታላቅ ነህና ተአምራትን ታደርጋለህ አንተ ብቻህን አምላክ ነህ፡፡ +\v 11 ያህዌ ሆይ፣ መንገድህን አስተምረን፤ እኔም በእውነትህ እሄዳለሁ፡፡ ባልተከፋፈለ ልብም እንዳከብርህ አድርገኝ፡፡ +\v 12 ጌታ አምላኬ ሆይ፣ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ ስምህንም ለዘላለም አከብራለሁ + +\s5 +\v 13 ለእኔ የምታሳየው ዘላለማዊው ፍቅርህ እጅግ ታላቅ ነው፡፡ ነፍሴንም ከጥልቁ ሲኦል አወጣሃት፡፡ +\v 14 አምላክ ሆይ፣ እብሪተኞች ተነሥተውብኛል የክፉዎች ጉባኤ ነፍሴን ይፈልጓታል፡፡ አንተንም ከምንም አልቆጠሩም፡፡ + +\s5 +\v 15 አንተ ግን ጌታ ሆይ፣ መሐሪና ርኅሩኅ አምላክ ነህ ለቁጣ የዘገየህ፣ ምህረትህና ታማኝነትህ የበዛ ነው፡፡ +\v 16 ወደ እኔ ተመለስ ማረኝም ለባሪያህ ብርታትህን ስጥ የሴት ባሪያህንም ልጅ አድን፡፡ +\v 17 የሞገስህን ምልክት አሳየኝ አንተ ያህዌ ረድተኸኛልና አጽናንተኸኛልምና የሚጠሉኝ ይህን አይተው ያፍራሉ፡፡ + +\s5 +\c 87 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ከተማውን፣ በተቀደሰው ተራራ ላይ መሠረተ +\v 2 ያህዌ የጽዮንን ደጆች ከያዕቆብ መኖሪያዎች ይበልጥ ይወዳል፡፡ +\v 3 የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ፣ ስለ አንቺ አስደናቂ ነገሮች ተነግረዋል፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 4 ከሚያውቁኝ መካከል ረዓብንና ባቢሎንን እጠቅሳለሁ፤ እነሆ ፍልስጥኤምና ጢሮስ ከኢትዮጵያ ጋር ሆነው፣ «ይህ ሰው የተወለደው በዚያ ነው› ይላሉ፡፡ + +\s5 +\v 5 ስለ ጽዮን ግን፣ ልዑል እግዚአብሔር ራሱ ስለሚመሠርታት፣ «እነዚህ ሁሉ የተወለዱ እዚያ ነው» ይላሉ፡፡ +\v 6 ያህዌ ሕዝቦችን ሲመሠርት «ይህ ሰው የተወለደው በዚያ ነው» ብሎ ይጽፋል፡፡ + +\s5 +\v 7 ዘማሪዎችና መሣሪያ ተጫዋቾችም፣ «ምንጩ ሁሉ አንቺ ውስጥ ይገኛል» ይላሉ፡፡ + +\s5 +\c 88 +\p +\v 1 አዳኜ ያህዌ አምላክ ሆይ፤ ቀንና ሌሊት በፊትህ እጮኻለሁ፡፡ +\v 2 እባክህ ጸሎቴን ስማ፤ ጩኸቴንም አድምጥ፡፡ + +\s5 +\v 3 በመከራ ተሞልቻለሁና ነፍሴም ወደ ሲኦል ተቃርባለች፡፡ +\v 4 ወደ መቃብር ከሚወርዱ ጋር ተቆጥሬአለሁ፤ ዐቅም አጣሁ፡፡ + +\s5 +\v 5 በሙታን መካከል ፈጽሞ እንደ ተተዉ ሞተው መቃብር ውስጥ እንደ ተጋደሙ ከእንግዲህ ፈጽሞ እንደማታስታውሳቸውና ከእጅህ ወጥተው እንደ ተወገዱ ሆንሁ፡፡ +\v 6 ጥልቁ አዘቅት ውስጥ ጣልኸኝ ጨለማ ጉድጓድ ውስጥ ከተትኸኝ፡፡ + +\s5 +\v 7 ቁጣህ እጅግ ከብዶኛል ማዕበልህም ሁሉ አጥለቅልቆኛል፡፡ + +\s5 +\v 8 ወዳጆቼን ሁሉ ከእኔ አራቅህ እንዲጸየፉኝም አደረግህ ዙሪያውን ተከብቤአለሁና ማምለጥ አልችልም፡፡ + +\s5 +\v 9 ዐይኖቼ በሐዘን ፈዘዙ ያህዌ ሆይ፣ ቀኑን ሙሉ ወደ አንተ እጮኻለሁ እጆቼን ወደ አንተ ዘረጋሁ፡፡ +\v 10 ለሙታን ተአምራት ታደርጋለህን? የሞቱትስ ተነሥተው ያመሰግኑሃልን? ሴላ + +\s5 +\v 11 ምሕረትህ መቃብር ውስጥ ታማኝነትህስ በሙታን ዓለም ይነገራልን? +\v 12 ድንቅ ሥራህ በጨለማ ስፍራ ጽድቅህስ በመረሳት ምድር ትቃወቃለችን? + +\s5 +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ እኔ ግን ወደ አንተ እጮኻለሁ በጧትም ጸሎቴን ወደ ፊት አቀርባለሁ፡፡ +\v 14 ያህዌ ሆይ፣ ለምን ትተወኛለህ? ፊትህንስ ከእኔ ለምን ትሰውራለህ? + +\s5 +\v 15 ከልጅነቴ ጀምሮ ችግረኛና ሞት አፋፍ ላይ ያለሁ ሰው ነበርሁ፤ ከማስደንገጥህ የተነሣ ተስፋ ቆርጫለሁ፡፡ +\v 16 ቁጣህ እኔ ላይ ተከነበለ መዓትህም አጠፋኝ፡፡ + +\s5 +\v 17 ቀኑን ሙሉ እንደ ጐርፍ ከበቡኝ ዙሪያውን አጥረው ያዙኝ፡፡፡ +\v 18 ወዳጆቼንና የሚቀርቡኝን ሰዎች ሁሉ ከእኔ አራቅህ ጓደኛዬ ጨለማ ብቻ ሆኖ ቀረ፡፡ + +\s5 +\c 89 +\p +\v 1 ስለ ያህዌ ምሕረት ለዘላለሙ እዘምራለሁ፡፡ ታማኝነትህንም ለሚመጣው ትውልድ እናገራለሁ፡፡ +\v 2 ምሕረትህን ለዘላለም እንደምትመሠርት ታማኝነትህንም በሰማያት እንደምታጸና እናገራለሁና + +\s5 +\v 3 አንተም እንዲህ ብለሃል፣ «ከመረጥሁት ጋር ኪዳን አድርጌአለሁ፤ ለባርያዬ ለዳዊት ምዬአለሁ፡፡ +\v 4 ዘርህን ለዘላለም አተክላለሁ ዙፋንህንም በትውልድ ዘመን ሁሉ አጸናለሁ፡፡» ሴላ + +\s5 +\v 5 ያህዌ ሆይ፣ ሰማያት ድንቅ ሥራህን ያመሰግናሉ ጽድቅህም በቅዱሳን ጉባኤ ይወደሳል፡፡ +\v 6 በላይ በሰማያት ከያህዌ ጋር ማን ሊስተካከል ይችላል? ከአማልክት ልጆችስ መካከል እንደ ያህዌ ያለ ማን ነው? + +\s5 +\v 7 እርሱ በቅዱሳኑ ጉባኤ መካከል እጅግ የተፈራ ነው፤ በዙሪያው ካሉትም ሁሉ ታላቅና አስፈሪ ነው፡፡ +\v 8 የሰራዊት ጌታ ያህዌ ሆይ፣ እንደ አንተ ያለ ኃያል ማነው? ታማኝነትህም ከቦሃል፡፡ + +\s5 +\v 9 የባሕሩን ቁጣ በሥልጣንህ ታዝዛለህ ማዕበሉንም ጸጥ ታደርጋለህ፡፡ +\v 10 አንተ ረዓብን ቀጥቅጠህ ገደልኸው በታላቁ ኃይልህ ጠላቶችህን በተንሃቸው፡፡ + +\s5 +\v 11 ሰማያት የአንተ ናቸው ምድርም የአንተ ናት፡፡ አንተ ዓለምንና በውስጧ ያሉትን ሁሉ ፈጠርህ፡፡ +\v 12 ሰሜኑን ደቡቡንም አንተ ፈጠርህ ታቦርና አርሞንዔም በስምህ ደስ ይላቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 13 አንተ ክንደ ብርቱ ነህ እጅህ ኃያል ናት፤ ቀኝ እጅህም ከፍ ከፍ ያለች ናት፡፡ +\v 14 ጽድቅና ፍትሕ የዙፋንህ መሠረት ናቸው ምሕረትና ታማኝነት በፊት ይሄዳሉ፡፡ + +\s5 +\v 15 ያህዌ ሆይ፣ በፊት ብርሃን የሚሄድ አንተንም የሚያመልክ ሕዝብ ቡሩክ ነው፡፡ +\v 16 ቀኑን ሙሉ በስምህ ደስ ይላቸዋል በጽድቅህም ከፍ ከፍ ይላሉ፡፡ + +\s5 +\v 17 ገናናው ኃይልህ ብርታት ይሰጣቸዋል በሞገስህም ድል ተቀዳጀን፡፡ +\v 18 ጋሻችን የያህዌ ነው ንጉሣችንም የራሱ የእስራኤል ቅዱስ ነውና፡፡ + +\s5 +\v 19 ከረጅም ጊዜ በፊት በራእይ ለሕዝብህ ተናገርህ እንዲህም አልህ፤ «ኃያሉን ሰው ሥልጣን አጐናጸፍሁ፤ ከሕዝብ መካከል እኔ የመረጥሁትን አስነሣሁ፡፡ +\v 20 ባርያዬ ዳዊትን መረጥሁት በተቀደሰው ዘይቴም ቀባሁት +\v 21 እጄ ይደግፈዋል ክንዴም ያበረታዋል፡፡ +\v 22 ጠላት አይረታውም ክፉ ሰውም አያሸንፈውም፡፡ +\v 23 ጠላቶቹን በፊቱ አደቃለሁ፤ ባላንጣዎቹንም እገድላለሁ፡፡ + +\s5 +\v 24 እውነቴና ታማኝነቴ ከእርሱ ጋር ይሆናል በስሜ ድል ይቀዳጃል፡፡ +\v 25 እጁን በባሕሮች ቀኝ እጁንም በወንዞች ላይ አደርጋለሁ፡፡ +\v 26 እርሱም፣ «አንተ አባቴ፣ አምላኬ የድነቴም ዐለት» ብሎ ይጠራኛል፡፡ + +\s5 +\v 27 እኔም ደግሞ በኩሬ አደርገዋለሁ ከምድር ነገሥታትም ሁሉ በላይ ከፍ ይላል፡፡ +\v 28 ምሕረቴንም ለዘላለም ለእርሱ እዘረጋለሁ ለእርሱ ጋር ያደረግሁትም ኪዳን ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል፡፡ +\v 29 የዘር ሐረጉን ለዘላለም ዙፋኑንም በሰማያት ዕድሜ ልክ አጸናለሁ + +\s5 +\v 30 ልጆቹ ሕጌን ቢተው፣ ሥርዐቴን ባይጠብቁ፣ +\v 31 ደንቤን ቢተላለፉ፣ ትእዛዞቼ ባያከብሩ፣ +\v 32 ኃጢአታቸውን በበትር፣ በደላቸውንም በአለንጋ እቀጣለሁ፡፡ + +\s5 +\v 33 ለእርሱ ያለኝ ፍቅር ግን አይቋረጥም ታማኝነቴንም አላጓድልበትም፡፡ +\v 34 ኪዳኔን አላፈርስም ከአፌ የወጣውን አላጥፍም፡፡ + +\s5 +\v 35 አንዴ በቅድስናዬ ምያለሁና ለዳዊት አልዋሽም፡፡ +\v 36 ልጆቹ ለዘላለም ዙፋኑም በፀሐይ ዕድሜ ልክ ጸንቶ ይኖራል፡፡ +\v 37 በሰማይ ታማኝ ምስክር ሆና እንደምትኖረው እንደ ጨረቃ እርሱም ለዘላለም ይመሠረታል፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 38 አሁን ግን ናቅኸው፤ ጣልኸውም በቀባኸውም ንጉሥ ላይ ተቆጣህ፡፡ +\v 39 ለባርያህ የገባኸውን ኪዳን አፈረስህ የክብር ዘውዱን መሬት ላይ ጣልህ፡፡ +\v 40 ቅጥሮቹን ሁሉ አፈረስህ ምሽጉንም ደመሰስህ፡፡ + +\s5 +\v 41 ዐላፊ አግዳሚ ሁሉ ዘረፈው ለጐረቤቶቹም መዘባበቻ ሆነ፡፡ +\v 42 የጠላቶቹን ቀኝ እጅ ከፍ አደረግህ ባላንጣዎቹም ሁሉ ደስ አላቸው፡፡ +\v 43 የሰይፉን ስለት አጠፍህ በጦርነትም ጊዜ አልረዳኸውም፡፡ + +\s5 +\v 44 የክብሩን ውበት አጠፋህበት ዙፋኑንም መሬት ላይ ጣልህበት፡፡ +\v 45 የወጣትነት ዘመኑን አሳጠርኸው ዕፍረትንም አከናነብኸው፡፡ + +\s5 +\v 46 ያህዌ ሆይ፣ ይህ እስከ መቼ ነው? ራስህንስ ለዘላለም ትሰውራለህን? ቁጣህስ እንደ እሳት የሚነደው እስከ መቼ ነው? +\v 47 ዕድሜዬ ምን ያህል አጭር እንደ ሆነ አስብ፤ የሰውን ልጆች እንዲሁ ለከንቱ ፈጠርሃቸው! +\v 48 ሞትን ሳያይ ሕያው ሆኖ የሚኖር ማን ነው? ሕይወቱን ከሲኦል እጅ ማዳን የሚችል ማነው? ሴላ + +\s5 +\v 49 ጌታ ሆይ፣ በታማኝነትህ ለዳዊት የማልህለት የቀድሞ ምሕረትህ የታለ? +\v 50 ጌታ ሆይ፣ ባርያህ ላይ የደረሰውን ፌዝ የብዙ ሰዎችንም ስድብ እንደ ታቀፍሁ አስብ፡፡ +\v 51 ያህዌ ሆይ፣ ጠላቶችህ የሚሳደቡትን፣ አንተ የቀባኸውን ሰው ርምጃ የነቀፉበትን ሁኔታ አስብ፡፡ + +\s5 +\v 52 ያህዌ ለዘላለም ይባረክ፡፡ አሜን፣ አሜን + +\s5 +\c 90 +\p +\v 1 ጌታ ሆይ፣ አንተ ከትውልድ እስከ ትውልድ መጠጊያችን ነህ፡፡ +\v 2 ተራሮችን ከመሥራትህና ዓለምንም ከመፍጠርህ በፊት አንተ ከዘላለም እስከ ዘላለም አምላክ ነህ + +\s5 +\v 3 ሰዎችን ወደ ዐፈር ትመልሳለህ፤ «የሰው ልጆች ሆይ ወደ ቦታችሁ ተመለሱ» ትላለህ፡፡ +\v 4 ሺህ ዓመት በፊትህ፣ እንዳለፈው ትናንት ቀን እንደ ሌሊትም ጥቂት ሰዓቶች ነው፡፡ + +\s5 +\v 5 እንደ ጐርፍ ጠርገህ ስትወስዳቸው እንደ ሕልም ይበናሉ በየማለዳው እንደሚታደስ የሣር ቡቃያ ይሆናሉ፡፡ +\v 6 ሣር ወዲያው አድጐ ያብባል ሲመሽ ግን ጠውልጐ ይጠፋል፡፡ + +\s5 +\v 7 እኛ በቁጣህ ጠፍተናል በመዓትህም ደንግጠናል፡፡ +\v 8 ኃጢአታችንን በፊትህ፣ የተሰወረ ኃጢአታችንንም በግልጽ በሚታይ ቦታ ታኖራለህ፡፡ + +\s5 +\v 9 ዘመናችን ሁሉ በቁጣህ ያልፋል ዕድሜያችንም በቅጽበት እንደሚያልፍ እስትንፋስ ነው፡፡ +\v 10 ዕድሜያችን ሰባ፣ ጤነኞች ከሆንንም ሰማንያ ዓመት ነው፡፡ እነዚያም ቢሆኑ፣ በመከራና ሐዘን የተሞሉ ናቸው፡፡ ዕድሜያችን ቶሎ ያልቃል፤ እኛም ወዲያው እንነጉዳለን፡፡ + +\s5 +\v 11 የቁጣህን ኃይል ማን ያውቃል? መዓትህም የመፈራትህን ያህል ታላቅ ነው፡፡ +\v 12 ጥበበኞች መሆን እንድንችል ዕድሜያችን ምን ያህል መሆኑን አስተምረን፡፡ +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ ተመለስ፤ ይህ እስከ መቼ ይሆናል፤ ለባሪያዎችህም ራራላቸው፡፡ + +\s5 +\v 14 በዘመናችን ሁሉ ደስ እንዲለን፣ ሐሤትም እንድናደርግ በማለዳ ምሕረትህን አጥግበን፡፡ +\v 15 መከራ ባየንበት ዘመን መጠን ችግር ባየንባቸው ዓመታት ልክ ደስ አሰኘን፡፡ +\v 16 እኛ ባርያዎችህ ታላቁን ሥራህን፣ ልጆቻችንም ግርማህን እንዲያዩ ፍቀድልን፡፡ + +\s5 +\v 17 የጌታ አምላካችን ሞገስ እኛ ላይ ይሁን የእጆቻችንን ሥራ ፍሬያማ ያድርግልን አዎን ፍሬያማ ያድርግልን፡፡ + +\s5 +\c 91 +\p +\v 1 በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ሥር ያድራል፡፡ +\v 2 ያህዌን፣ «መጠጊያዬ፣ ምሽጌ፣ የምታመንብህ አምላኬ» እለዋለሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 ከአዳኝ ወጥመድ ከአደገኛም መቅሠፍት ያድንሃል +\v 4 በላባዎቹ ይጋርድሃል በክንፎቹም ሥር መሸሸጊያ ታገኛለህ፡፡ ታማኝነቱም ጋሻና መከታ ይሆንልሃል፡፡ + +\s5 +\v 5 የሌሊትን ሽብር፣ በቀን ከሚወረወር ፍላጻም አትፈራም +\v 6 በጨለማ ከሚያደባ ቸነፈር በቀትርም ከሚወርድ መቅሠፍት አትሰጋም፡፡ +\v 7 በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም ዐሥር ሺህ ይወድቃሉ ወደ አንተ ግን አይቀርብም፡፡ + +\s5 +\v 8 በዐይንህ ብቻ ታያለህ የክፉዎችንም መቀጣት ትመለከታለህ፡፡ +\v 9 አንተ ያህዌን መሸሸጊያ ልዑል አምላክንም መጠጊያህ አድርገኸዋልና፡፡ + +\s5 +\v 10 ክፉ ነገር አያገኝህም መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይጠጋም፡፡ +\v 11 በመንገድህ ሁሉ እንዲጠብቁህ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 12 እግሮችህ በድንጋይ እንዳይሰናከሉ በእጆቻቸው ያነሡሃል፡፡ +\v 13 አንበሳና እፉኝት ላይ ትጫማለህ ደቦሉን አንበሳና ዘንዶውን ትረግጣለህ፡፡ + +\s5 +\v 14 ወዶኛልና አታደገዋለሁ በእኔ ተማምኖአልና እጠብቀዋለሁ፡፡ +\v 15 ይጠራኛል እኔም እመልስለታለሁ በመከራው ጊዜ ከእርሱ ጋር እሆናለሁ ድል አቀዳጀዋለሁ፤ አከብረውማለሁ፡፡ +\v 16 ረጅም ዕድሜ አጠግበዋለሁ ማዳኔንም አሳየዋለሁ፡፡ + +\s5 +\c 92 +\p +\v 1 ያህዌን ማመስገን መልካም ነው፤ ልዑል ሆይ፣ ለስምህ መዘመር መልካም ነው፡፡ +\v 2 ምህረትህን በማለዳ ታማኝነትህን በሌሊት ማወጅ መልካም ነው፡፡ +\v 3 ዐሥር አውታር ባለው በገና ከመሰንቆም ጣዕመ ዜማ ጋር ማወጅ መልካም ነው፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌ ሆይ፣ በሥራህ ደስ ስላሰኘኸኝ ስለ እጅህ ሥራ በደስታ እዘምራለሁ፡፡ +\v 5 ያህዌ ሆይ፣ ሥራህ እንዴት ታላቅ ነው? ሐሳብህ እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ + +\s5 +\v 6 ደነዝ ሰው ይህን አያስተውልም ሞኝም ይህን አይረዳም፣ +\v 7 ክፉ ሰዎች እንደ ሣር ቢበቅሉ ተንኰለኞችም ቢለመልሙ ለዘላለሙ ይጠፋሉ፡፡ + +\s5 +\v 8 አንተ ግን ያህዌ ሆይ፣ ለዘላለም ትነግሣለህ፡፡ +\v 9 ጠላቶችህ ያህዌ ሆይ፣ ጠላቶችህ ይጠፋሉ ክፉ አድራጊዎችም ሁሉ ይበተናሉ፡፡ + +\s5 +\v 10 እንደ ጐሽ ቀንድ ቀንዴን ከፍ ከፍ አደረግህ በትኩስ ዘይትም ቀባኸኝ፡፡ +\v 11 ዐይኖቼ የባላንጣዎቹን ውድቀት አዩ ጆሮቼም የክፉ ጠላቶቼን ጥፋት ሰሙ፡፡ + +\s5 +\v 12 ጻድቃን እንደ ዘንባባ ዛፍ ይለመልማሉ እንደ ሊባኖስ ዛፍም ያድጋሉ፡፡ +\v 13 በያህዌ ቤት ተተክለዋል በአምላካችን አደባባይ ይንሰራፋሉ፡፡ + +\s5 +\v 14 ባረጁ ጊዜ እንኳ ያፈራሉ እንደ ለመለሙና እንደ ጠነከሩም ይኖራሉ፡፡ +\v 15 እግዚአብሔር ትክክለኛ ነው፤ እርሱ ዐለቴ ነው፤ በእርሱ ዘንድ እንከን የለም፡፡ + +\s5 +\c 93 +\p +\v 1 ያህዌ ነገሠ ግርማንም ለበሰ፣ ያህዌ ግርማን ተጐናጸፈ ብርታትንም ታጠቀ ዓለምን በአንድ ስፍራ አጸናት፤ ከቶም አትናወጥም፡፡ +\v 2 ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የጸና ነው አንተም ከዘላለም እስከ ዘላለም ነህ፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ ባሕሮች ይነሣሉ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው ይጮኻሉ ወንዞች የሚያስገመግም ማዕበላቸውን ከፍ አደረጉ፡፡ +\v 4 ከብዙ ውሆች ድምፅ ይልቅ ከባሕርም ሞገድ ይልቅ ከፍ ብሎ ያለው ያህዌ ብርቱ ነው፡፡ + +\s5 +\v 5 ትእዛዛትህ ያጸኑ ናቸው ያህዌ ሆይ፣ ቤትህ ለዘላለም በቅድስና ይዋባል፡፡ + +\s5 +\c 94 +\p +\v 1 የበቀል አምላክ አንተ ያህዌ ሆይ፣ የበቀል አምላክ ሆይ፣ ብርሃንህ ይብራልን፡፡ +\v 2 የምድር ዳኛ ሆይ፣ ተነሥ ለትዕቢተኞች የእጃቸውን ስጣቸው፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ ክፉዎች እስከ መቼ፣ ክፉዎች እስከ መቼ ነው የሚፈነጩት? +\v 4 የእብሪት ቃሎች ያዥጐደጉዳሉ ክፉ አድራጊዎችም ሁሉ ጉራ ይነዛሉ፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ ሆይ፣ ሕዝብህን ያደቅቃሉ የአንተን ወገኖች ይጨቁናሉ፡፡ +\v 6 በአገራቸው የሚኖሩ መበለቶችንና መጻተኞችን ይገድላሉ፤ +\v 7 «ያህዌ አያይም፤ የያዕቆብ አምላክም አያስተውልም» ይላሉ፡፡ + +\s5 +\v 8 እናንት አላዋቂዎች ይህን አስተውሉ፤ እናንት ሞኞች ለመሆኑ፣ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው? +\v 9 ጆሮን የተከለ እርሱ አይሰማምን? ዐይንን የሠራ እርሱ አያይምን? + +\s5 +\v 10 ሕዝቦችን የሚገሥጸው አይቀጣምን? ለሰው ዕውቀት የሚሰጥ እርሱ ነው፡፡ +\v 11 ያህዌ የሰው ሐሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል፡፡ + +\s5 +\v 12 ያህዌ ሆይ፣ አንተ የምትገሥጸው ሕግህንም የምታስተምረው ሰው ቡሩክ ነው፡፡ +\v 13 ለክፉዎች ጉድጓድ እስኪቆፈር ድረስ አንተ እርሱን ከመከራ ታሳርፈዋለህ፡፡ + +\s5 +\v 14 ያህዌ ሕዝቡን አይጥልምና ርስቱንም አይተውም፡፡ +\v 15 ፍርድ ተመልሶ በጽድቅ አሠራር ላይ ይመሠረታል ልበ ቀናዎችም ሁሉ ይከተሉታል፡፡ +\v 16 ክፉዎችን የሚቋቋምልኝ ማን ነው? ከክፉ አድራጊዎች የሚሟገትልንስ ማን ነው? + +\s5 +\v 17 ያህዌ ረዳቴ ባይሆን ኖሮ ፈጥኜ ወደ ዝምታው ዓለም በወረድሁ ነበር፡፡ +\v 18 እኔ፣ «እግሬን አዳለጠኝ» ባልሁ ጊዜ ያህዌ ሆይ፣ ምሕረትህ ደግፎ ያዘኝ፡፡ +\v 19 ሐዘኔ በበዛ ጊዜ፣ ማጽናናትህ ደስ አሰኘኝ፡፡ + +\s5 +\v 20 ዓመፅን ሕጋዊ የሚያደርግ የጥፋት ዙፋን ከአንተ ጋር ሊያብር ይችላልን? +\v 21 ጻድቃንን ለማጥፋት ያሤራሉ በንጹሐን ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ ይበይናሉ፡፡ + +\s5 +\v 22 ለእኔ ግን ያህዌ ጠንካራ ምሽግ አምላኬም መጠጊያ ዐለት ሆኖኛል፡፡ +\v 23 ኃጢአታቸውን ወደ ራሳቸው ይመልሳል በገዛ ክፋታቸውም ያጠፋቸዋል፡፡ ያህዌ አምላካችን ይደመስሳቸዋል፡፡ + +\s5 +\c 95 +\p +\v 1 ኑ፣ ያህዌን እናመስግን የመዳን ዐለታችን ለሆነው ለእርሱ በደስታ እንዘምር፡፡ +\v 2 ወደ ፊቱ በምስጋና እንግባ በዝማሬም እናወድሰው፡፡ +\v 3 ያህዌ ታላቅ አምላክ ነውና ከአማልክትም ሁሉ የበለጠ ታላቅ ንጉሥ ነው፡፡ + +\s5 +\v 4 የምድር ጥልቆች በእጁ ናቸው የተራራ ጫፎችም የእርሱ ናቸው፡፡ +\v 5 ባሕር የእርሱ ነው፤ እርሱ ሠራው እጆቹም የብሱን አበጁ፡፡ + +\s5 +\v 6 ኑ እናምልከው እንስገድለትም በፈጠረን በያህዌ ፊት እንንበርከክ +\v 7 እርሱ አምላካችን ነውና እኛ የመሰማሪያው ሕዝብ የእጁም በጐች ነን፡፡ ዛሬ ድምፁን ብትሰሙ + +\s5 +\v 8 «በምድረ በዳ በነበራችሁበት ቀን በማሳህ፣ በመረባም እንዳደረጋችሁት ልባችሁን አታደንድኑት፡፡ +\v 9 ሥራዬን ቢያዩም አባቶቻችሁ ፈተኑኝ፤ ተፈታተኑኝም፤ + +\s5 +\v 10 ያንን ትውልድ አርባ ዓመት ሙሉ ተቆጣሁት፣ እኔም፣ «ልቡ የሸፈተ ሕዝብ ነው፤ መንገዴንም አላወቁም» አልሁ፡፡ +\v 11 ስለዚህ፣ «በፍጹም ወደ እኔ ዕረፍቴ ቦታ አይገቡም» ብዬ በቁጣየ ማልሁ፡፡ + +\s5 +\c 96 +\p +\v 1 ለያህዌ አዲስ መዝሙር ዘምሩ ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር ዘምሩ +\v 2 ለያህዌ ዘምሩ፤ ስሙንም ባርኩ ማዳኑንንም ዕለት በዕለት ተናገሩ፡፡ + +\s5 +\v 3 ክብሩን በሕዝቦች መካከል ድንቅ ሥራውንም በሕዝቦች መካከል ተናገሩ፡፡ +\v 4 እግዚአብሔር ታላቅ ነው፣ ከፍ ያለ ምስጋናም ይገባዋል ከአማልክት ሁሉ በላይ ሊፈራ ይገባዋል፡፡ + +\s5 +\v 5 የሕዝቦች አማልክት ሁሉ ጣዖቶች ናቸው ያህዌ ግን ሰማያትን ሠራ፡፡ +\v 6 ክብርና ግርማ በፊቱ ናቸው ብርታትና ውበትም መቅደሱ ውስጥ አሉ፡፡ + +\s5 +\v 7 የሕዝብ ወገኖች ሁሉ ለያህዌ ምስጋና ስጡ ክብርንና ብርታትን ለያህዌ ስጡ፡፡ +\v 8 ለስሙ የሚገባውን ክብር ለያህዌ ስጡ ስጦታ ይዛችሁ ወደ አደባባዩ ግቡ፡፡ + +\s5 +\v 9 ክብርን በተሞላ ቅድስና ለያህዌ ስገዱ ምድር ሁሉ በፊቱ፤ ተንቀጥቀጡ፡፡ +\v 10 በሕዝቦች መካከል፣ «እግዚአብሔር ነገሠ» በሉ፤ ምድር በጽኑ ስለ ተመሠረተች አትናወጥም፡፡ እርሱ ሕዝቦች ላይ በጽድቅ ይፈርዳል፡፡ + +\s5 +\v 11 ሰማያት ደስ ይበላቸው፤ ምድርም ሐሴት ታድርግ፡፡ ባሕርና በውስጧ ያለው ሁሉ እልል ይበል፡፡ +\v 12 መስክና በላዩ ያለው ሁሉ ይፈንጥዝ ያን ጊዜ የዱር ዛፎች ሁሉ በደስታ ይዘምራሉ፡፡ +\v 13 እርሱ ይመጣልና በያህዌ ፊት ይዘምራሉ በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣል በዓለም ላይ በጽድቅ፣ በሕዝቦችም ላይ በእውነት ይበይናል፡፡ + +\s5 +\c 97 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ነገሠ ምድር ደስ ይበላት፤ በሩቅ ያሉ የባሕር ጠረፎች ሐሤት ያድርጉ፡፡ +\v 2 ደመናና ጥቅጥቅ ያለ ጭጋግ በዙሪያው አለ ጻድቅና ፍትሕ የዙፋኑ መሠረት ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 3 እሳት በፊቱ ይሄዳል በዙሪያው ያሉ ባላንጣዎቹን ይፈጃል፡፡ +\v 4 መብረቁ ዓለምን አበራ ምድር ዐይታ ተንቀጠቀጠች፡፡ +\v 5 ተራሮች ያህዌ ፊት የምድር ሁሉ ጌታ ፊት እንደ ሰም ቀለጡ + +\s5 +\v 6 ሰማያት ጽድቁን ያውጃሉ ሕዝቦችም ሁሉ ክብሩን ያያሉ፡፡ +\v 7 የተቀረጹ ምስሎች የሚያመልኩ፣ በጣዖቶች የሚመኩ ሁሉ ይፈሩ እናንት አማልክት ሁላችሁ ለእርሱ ስገዱ +\v 8 ያህዌ ሆይ፣ ስለ ፍርድህ ጽዮን ሰምታ ደስ አላት የይሁዳም ከተሞች ሐሤት አደረጉ፡፡ + +\s5 +\v 9 ያህዌ ሆይ፣ አንተ በምድር ሁሉ ልዑል ነህና ከአማልክት ሁሉ ይልቅ እጅግ ከፍ ያልህ ነህ፡፡ +\v 10 ያህዌን የምትወዱ ክፋትን ጥሉ! እርሱ የቅዱሳኑን ሕይወት ይጠብቃል ከክፉዎችም እጅ ይታደጋቸዋል፡፡ +\v 11 ብርሃን ለጻድቃን ሐሤትም ለልበ ቅኖች ወጣ፡፡ + +\s5 +\v 12 እናንተ ጻድቃን በያህዌ ደስ ይበላችሁ ቅዱስ ስሙንም አመስግኑ፡፡ + +\s5 +\c 98 +\p +\v 1 እርሱ ድንቅ ነገሮችን አድርጐአልና ለያህዌ አዲስ መዝሙር አቅርቡ ቀኝ እጁ፣ ቅዱስ ክንዱም ድል ሰጥተውታል፡፡ +\v 2 ያህዌ ማዳኑን አሳወቀ ጽድቁንም ለሕዝቦች ሁሉ በግልጽ አሳየ፡፡ + +\s5 +\v 3 ለእስራኤል ቤት ምሕረቱን ታማኝነቱንም አሰበ፡፡ የምድር ዳርቻዎች ሁሉ የአምላካችንን ድል አድራጊነት አዩ፡፡ +\v 4 ምድር ሁሉ ለያህዌ እልል በሉ ውዳሴ አፍልቁ፤ በደስታና በዝማሬ አመስግኑ፡፡ + +\s5 +\v 5 በገና በመደርደርና በመዝሙር ለያህዌ ምስጋና አቅርቡ፡፡ +\v 6 በመለከትና በእምቢልታ ድምፅ በንጉሡ በያህዌ ፊት እልል በሉ፡፡ + +\s5 +\v 7 ባሕርና በውስጡ ያለው ሁሉ ዓለምና የሚኖሩባትም ሁሉ ያስገምግሙ +\v 8 ወንዞች ያጨብጭቡ ተራሮችም በደስታ እልል ይበሉ፡፡ +\v 9 ያህዌ በምድር ላይ ለመፍረድ ይመጣል በዓለም ላይ በጽድቅ በሕዝቦችም ላይ በእውነት ይበይናል፡፡ + +\s5 +\c 99 +\p +\v 1 ያህዌ ነገሠ፤ ሕዝቦች ይንቀጥቀጡ በኪሩቤል ላይ በዙፋኑ ተቀምጧል፤ ምድር ትናወጥ፡፡ +\v 2 ያህዌ በጽዮን ታላቅ ነው ከሕዝቦችም ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፡፡ +\v 3 ታላቁንና አስፈሪውን ስምህን ይወድሱ እርሱ ቅዱስ ነው፡፡ + +\s5 +\v 4 ፍትሕ የምትወድ ኃያል ንጉሥ ሆይ ጽድቅንና ፍትሕን ለያዕቆብ አደረግህ፡፡ +\v 5 አምላካችን ያህዌን አመስግኑት በእግሩ መርገጫ ስገዱ፡፡ እርሱ ቅዱስ ነው፡፡ + +\s5 +\v 6 ሙሴና አሮን ካህናቱ መካከል ነበሩ ሳሙኤልም ስሙን ከጠሩት መካከል ነበረ እነርሱ ወደ ያህዌ ጸለዩ እርሱም መለሰላቸው፡፡ +\v 7 በደመና ዐምድ ውስጥ ተናገራቸው እነርሱም ሥርዐቱንና የሰጣቸውን ድንጋጌ ጠበቁ፡፡ + +\s5 +\v 8 አምላካችን ያህዌ ሆይ፣ አንተ መለስህላቸው ይቅር ባይ አምላክ ሆንህላቸው ኃጢአታቸውን ግን ቀጣህ፡፡ +\v 9 አምላካችን ያህዌን አመስግኑ አምላካችን ያህዌ ቅዱስ ነውና በቅዱስ ተራራው ሰገዱ፡፡ + +\s5 +\c 100 +\p +\v 1 ምድር ሁሉ ለያህዌ እልል በሉ +\v 2 ያህዌን በደስታ አገልግሉት፡፡ በደስታ ዝማሬ ፊቱ ቅረቡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ አምላክ መሆኑን ዕወቁ እርሱ ፈጠረን፤ እኛም የእርሱ ነን፡፡ እኛ ሕዝቡ የመሰማሪያውም በጐች ነን፡፡ + +\s5 +\v 4 በምስጋና ወደ ደጆቹ፣ በውዳሴም ወደ አደባባዮቹ ግቡ፡፡ አመስግኑት ስሙንም ባርኩ፤ +\v 5 ያህዌ ቸር ነው፤ ምሕረቱም ለዘላለም ነው፤ ታማኝነቱም ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው፡፡ + +\s5 +\c 101 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ስለ ታማኝነትህና ስለ ትክክለኛ ፍርድህ ምስጋና እዘምራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 2 ነቀፋ በሌለበት መንገድ እሄዳለሁ አንተ ወደ እኔ የምትመጣው መቼ ነው? በቤቴ ውስጥ ያለ ነቀፋ እመላለሳለሁ፡፡ +\v 3 በዐይኖቼ ፊት በደል አላኖርም የክፉዎችን ሥራ እጠላለሁ ከቶም አልተባበራቸውም፡፡ + +\s5 +\v 4 ጠማማ ሰዎች ከእኔ ይርቃሉ ከክፋት ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም፡፡ +\v 5 ባልንጀራውን በስውር የሚያማውን አጠፋለሁ፡፡ ትዕቢተኛ ዐይንና እብሪተኛ ልብ ያለውን ሰው አልታገሠውም፡፡ +\v 6 ከእኔ ጋር እንዲኖሩ፣ ዐይኖቼ በምድሪቱ ያሉ ታማኞች ላይ ናቸው በንጹሕና የሚሄድ እርሱ ያገለግለኛል፡፡ + +\s5 +\v 7 አታላይ ሰው ቤቴ ውስጥ አይኖርም ሐሰተኛም በዐይኖቼ ፊት አይከብርም፡፡ +\v 8 በምድሪቱ ያሉትን ክፉ አድራጊዎች በየማለዳው አጠፋቸዋለሁ፤ ክፉ አድራጊዎችን ሁሉ ከያህዌ ከተማ አስወግዳቸዋለሁ፡፡ + +\s5 +\c 102 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ ጸሎቴን ሰማ ጩኸቴንም አድምጥ፡፡ +\v 2 በመከራዬ ጊዜ ፊትህን ከእኔ አትሰውር ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል ወደ አንተ ስጣራ ፈጥነህ አድምጠኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 ዘመኔ እንደ ጢስ እየበነነ ነው ዐጥንቶቼም እንደ እሳት እየነደዱ ነው፡፡ +\v 4 ልቤ ተሰብሮአል፤ እኔም እንደ ደረቀ ሣር ሆኛለሁ፡፡ እህል መብላትንም ዘንግቻለሁ፡፡ + +\s5 +\v 5 ዘወትር ከመቃተቴ የተነሣ ዐጥንቴ ከቆዳዬ ጋር ተጣበቀ፡፡ +\v 6 በምድረ በዳ እንዳለ እርኩም መሰልሁ፤ በፍርስራሽ መካከል እንዳ ጉጉት ሆንሁ፡፡ + +\s5 +\v 7 ያለ እንቅልፍ አድራለሁ፤ በቤት ጣራ ላይ እንዳለ ብቸኛ ወፍ ሆኛለሁ +\v 8 ጠላቶቼ ቀኑን ሙሉ ይሳለቁብኛል የሚያፌዙብኝም ስሜን እንደ ርግማን ቆጥረውታል፡፡ + +\s5 +\v 9 ዐመድ እንደ እህል ቅሜአለሁ! እንባዬም ከምጠጣው ነገር ጋር ተደባልቆአል፡፡ +\v 10 ወደ ላይ አነሣኸኝ፤ ከቁጣህና ከመዓትህም የተነሣ መልሰህ ጣልኸኝ፡፡ + +\s5 +\v 11 ዘመኖቼ ቶሎ እንደሚያልፍ ጥላ ናቸው እኔም እንደ ሣር ደረቅሁ +\v 12 አንተ ግን ያህዌ ሆይ፣ ለዘላለም ትኖራለህ ስምህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ገናና ነው፡፡ + +\s5 +\v 13 ትነሣህ፤ ጽዮንንም ትምራታለህ ለእርሷ ርኅራኄህን የምታሳይበት ጊዜ ነው፤ +\v 14 አገልጋዮችህ ድንጋዮዋን ወደዋልና ለፍርስራሾቿ ራርተዋል፡፡ +\v 15 ሕዝቦች የያህዌን ስም የምድር ነገሥታትም ክብርህን ይፈራሉ፡፡ +\v 16 ያህዌ ጽዮንን እንደ ገና ይሠራታልና በክብሩም ይገለጣል፡፡ + +\s5 +\v 17 በዚያ ጊዜ እርሱ ለችግረኞች ጸሎት መልስ ይሰጣል፤ ልመናቸውንም አይንቅም፡፡ +\v 18 ገና ያልተወለዱ ሰዎች እንዲያመሰግኑት ይህ ያህዌ ያደረገው ድንቅ ነገር ለሚመጣው ትውልድ ይጻፍ፡፡ + +\s5 +\v 19 በከፍታ ካለው መቅደሱ ወደ ታች ተመልክቶአልና ያህዌ ከሰማይ ምድርን ዐይቶአል፡፡ +\v 20 ይኸውም የእስረኞችን መቃተት ይሰማ ዘንድ ሞት የተፈረደባቸውን ያድን ዘንድ ነው፡፡ + +\s5 +\v 21 ስለዚህ የያህዌ ስም በጽዮን፣ ምስጋናውም በኢየሩሳሌም ይነገራል፡፡ +\v 22 ይህም የሚሆነው ሕዝቦችና መንግሥታት ያህዌን ለማምለክ በአንድት ሲሰበሰቡ ነው፡፡ + +\s5 +\v 23 በሕይወቴ እኩሌታ ብርታቴን ቀጨው ዕድሜዬንም ባጭሩ አስቀረው፡፡ +\v 24 እኔም፣ «አምላኬ ሆይ፣ የአንተ ዘመን ከትውልድ እስከ ትውልድ ስለሆነ በዕድሜዬ እኩሌታ አትውሰደኝ» አልሁ፡፡ + +\s5 +\v 25 አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ ሰማያትም የእጆችህ ሥራ ናቸው፡፡ +\v 26 እነርሱ ይጠፋሉ፤ አንተ ግን ጸንተህ ትኖራለህ እነርሱ እንደ ልብስ ያረጃሉ እንደ መጐናጸፊያ ትለውጣቸዋለህ እነርሱም ወዲያ ይጣላሉ፡፡ +\v 27 አንተ ግን ያው አንተ ነህ ዘመኖችህም ፍጻሜ የላቸውም፡፡ + +\s5 +\v 28 የአገልጋዮችህ ልጆች በሰላም ይኖራሉ ትውልዳቸውም በፊትህ ጸንቶ ይኖራል፡፡ + +\s5 +\c 103 +\p +\v 1 ነፍሴ ሆይ፣ ያህዌ አመስግኚ የያህዌን ቅዱስ ስም በሙሉ ልቤ አመሰግናለሁ፡፡ +\v 2 ነፍሴ ሆይ፣ ያህዌን አመሰግኚ ውለታውንም ሁሉ አትርሺ፡፡ + +\s5 +\v 3 ኃጢአትሽን ሁሉ ይቅር ይላል ደዌሽንም ሁሉ ይፈውሳል፡፡ +\v 4 ሕይወትሽንም ከጥፋት ጉድጓድ ያድናል ምሕረትና ርኅራኄውን ያቀዳጅሻል፡፡ +\v 5 ወጣትነትሽ እንደ ንስር ይታደስ ዘንድ ሕይወትሽን በመልካም ነገር ያጠግባል፡፡ + +\s5 +\v 6 ያህዌ ለተጨቆኑ ሁሉ፣ ቅን ፍርድንና ፍትሕን ይሰጣል፡፡ +\v 7 መንገዱን ለሙሴ፣ ሥራውንም ለእስራኤል ልጆች አሳወቀ፡፡ +\v 8 ያህዌ መሐሪና ይቅር ባይ ለቁጣ የዘገየ፣ ታማኝነቱም የበዛ ነው፡፡ + +\s5 +\v 9 እርሱ ሁልጊዜ አይገሥጽም ለዘላለምም አይቆጣም፡፡ +\v 10 እንደ ኃጢአታችን አላደረግብንም እንደ በደላችንም አልከፈለንም፡፡ + +\s5 +\v 11 ሰማይ ከምድር ከፍ የማለቱን ያህል እንዲሁ ለሚፈሩት ምሕረቱ ታላቅ ነው፡፡ +\v 12 ምሥራቅ ከምዕራብ እንደሚርቅ በደልና ኃጢአታችንን በዚያው መጠን ከእኛ አስወገደ፡፡ +\v 13 አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ ያህዌም ለሚፈሩት ይራራል፡፡ + +\s5 +\v 14 እርሱ አፈጣጠራችንን ያውቃልና ትቢያ መሆናችንንም ይገነዘባል፡፡ +\v 15 ሰው እኮ እንደ ሣር እንደሚያድግ የዱር አበባ ነው፡፡ +\v 16 ነፋስ በሚነፍስበት ጊዜ ድራሹ ይጠፋል፤ የነበረበት ስፍራ እንኳ አይታወቅም፡፡ + +\s5 +\v 17 የያህዌ ምሕረት ግን ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚፈሩት ላይ ነው፡፡ ጽድቁም እስከ ልጅ ልጃቻቸው ዘመን በላያቸው ይሆናል፤ +\v 18 ይህም ኪዳኑን በሚጠብቁት ላይ ትእዛዙንም በሚያከብሩት ላይ ይሆናል፡፡ +\v 19 ያህዌ ዙፋኑን በሰማይ አጽንቶአል መንግሥቱም ሁሉን ትገዛለች፡፡ + +\s5 +\v 20 እናንተ ለቃሉ የምትታዘዙ መላእክት ትእዛዙንም የምትፈጽሙ እናንተ ኃያላን፣ ያህዌን አመስግኑ፡፡ +\v 21 አገልጋዩ የሆናችሁ፣ ፈቃዱንም የምትፈጽሙ እናንተ የሰማይ ሰራዊት ያህዌን አመስግኑ፡፡ +\v 22 በግዛቱ ሁሉ የምትገኙ ፍጥረቶቹ ያህዌን አመስግኑ፤ ነፍሴ ሆይ ያህዌን አመስግኚ፡፡ + +\s5 +\c 104 +\p +\v 1 ነፍሴ ሆይ፣ ያህዌን አመስግኚ አምላኬ ያህዌ ሆይ፣ አንተ እጅግ ታላቅ ነህ ውበትና ግርማን ለብሰሃል፡፡ +\v 2 ብርሃንን እንደ ሸማ ተጐናጽፈሃል ሰማያትን እንደ ድንኳን መጋረጃ ዘረጋህ፡፡ +\v 3 በጠፈር ላይ ካለው ውሃ በላይ ቤትህን ሠርተሃል ደመናትን ሰረገላህ አደረግህ በነፋስ ክንፎች ትሄዳለህ፡፡ + +\s5 +\v 4 ነፋሶችን መልእክተኞቹ፣ ነበልባልንም አገልጋዮቹ አደረግ፡፡ +\v 5 ምድርን መሠረት ላይ አጸና ከቶም አትናወጥም፡፡ + +\s5 +\v 6 በጥልቁ እንደ ልብስ ሸፈንሃት ውሆችም ከተራሮች በላይ ቆሙ፡፡ +\v 7 በገሠጸካቸው ጊዜ ግን ፈጥነው ሄዱ የነጐድጓድህንም ድምፅ በሰሙ ጊዜ ሸሹ፡፡ + +\s5 +\v 8 በተራሮች ላይ ፈሰሱ አንተ ወዳዘጋጀህላቸው ስፍራ ወደ ሸለቆዎች ወረዱ፡፡ +\v 9 ዳግመኛ ምድርን እንዳይሸፍኑም አልፈውም እንዳይመጡ ድንበር አበጀህላቸው፡፡ + +\s5 +\v 10 ምንጮች በሸለቆው ውስጥ እንዲ ወንዞችም በተራሮች መካከል እንዲወርዱ አደረግህ፡፡ +\v 11 የዱር እንስሳት ከዚያ ይጠጣሉ የሜዳ አህዮችም ጥማቸውን ያረካሉ፡፡ +\v 12 ወንዙ ዳር ወፎች ጐጆአቸውን ይሠራሉ በቅርንጫፎቹም መካከል ይዘምራሉ፡፡ + +\s5 +\v 13 ከላይ ከእልፍኙ ተራሮችን ያጠጣል፤ ምድርም በሥራው ፍሬ ትረካለች፡፡ +\v 14 ከምድር ምግብን ታወጣ ዘንድ ለእንስሶች ሣርን ታበቅላለህ ለሰው ልጆች ሥራ አትክልቶችን ታበቅላለህ፡፡ +\v 15 ስለዚህ ልቡን ደስ የሚሰኘውን ወይን ጠጅ፣ ፊቱን የሚያበራ ዘይትና በሕይወት የሚያኖረውን እህል ያዘጋጃል፡፡ + +\s5 +\v 16 ደግሞም የያህዌ ዛፎች፣ እርሱ የተከላቸውም የሊባኖስ ዝግባዎች በቂ ዝናብ ያገኛሉ፡፡ +\v 17 በዚያ ወፎች ጐጆአቸውን ይሠራሉ ሽመላዎችም በጥዶቹ ውስጥ ማደሪያ ያገኛሉ፡፡ +\v 18 ረጃጅሙ ተራራ የዋልያ ተራራ የዐለቱም ዋሻዎች የሽኮኮ መሸሸጊያ ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 19 ጨረቃ የወቅቶች ምልክት እንድትሆን አደረገ ፀሐይም የምትጠልቀበትን ጊዜ ታውቃለች፡፡ +\v 20 ጨለማን ፈጠርህ፤ ሌሊትም ሆነ፤ በጨለማም የዱር አውሬዎች ሁሉ ይወጣሉ፡፡ + +\s5 +\v 21 የአንበሳ ግልግሎች ምግብ ለማግኘት ይጫኸሉ፤ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምግባቸውን ይፈልጋሉ፡፡ +\v 22 ፀሐይ በወጣች ጊዜ ሸሽተው ይሄዳሉ፤ በየመኖሪያቸው ውስጥ ይተኛሉ፡፡ + +\s5 +\v 23 ሰውም ወደ ሥራው ይሄዳል እስኪመሽም ድረስ ሲሠራ ይውላል፡፡ +\v 24 ያህዌ ሆይ፣ ሥራህ እንዴት ብዙ ነው! ሁሉን በጥበብ አደረግህ ምድርም በፍጥረትህ ተሞላች፡፡ + +\s5 +\v 25 እዚያ ደግሞ ሰፊና የተንጣለለ ባሕር አለ ታላላቅና ታናናሽ እንስሳት፣ ስፍር ቁጥር የሌላቸውም ነፍሳት በውስጡ አሉ፡፡ +\v 26 መርከቦች በላዩ ይመላለሳሉ አንተ የፈጠርኸው ሌዋታን በውስጡ ይፈነጫል፡፡ + +\s5 +\v 27 እነዚህ ሁሉ በጊዜው ምግባቸውን እንድትሰጣቸው አንተን ተስፋ ያደርጋሉ፡፡ +\v 28 በሰጠሃቸው ጊዜ አንድ ላይ ይከማቻሉ፣ እጅህንም ስትዘረጋ በመልካም ነገር ይጠግባሉ፡፡ + +\s5 +\v 29 ፊትህን ስትሰውር፣ በጣም ይደነግጣሉ እስትንፋሳቸውን ስትወስድ ይሞታሉ፤ ወደ አፈርም ይመለሳሉ፡፡ +\v 30 መንፈስህ ስትልክ እነርሱ ይፈጠራሉ የምድርንም ገጽ ታድሳለህ፡፡ + +\s5 +\v 31 ለዘላለም ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን ያህዌ በፍጥረቱ ደስ ይበለው፡፡ +\v 32 ከላይ ምድርን ሲመለከት ትንቀጠቀጣለች ተራሮችን ሲዳስሳቸው ይጨሳሉ + +\s5 +\v 33 በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ለያህዌ እዘምራለሁ በሕይወትም እስካለሁ ድረስ ለአምላኬ የምስጋና መዝሙር አቀርባለሁ፡፡ +\v 34 ደስታዬ በእርሱ ስለሆነ የልቤ ሐሳብ እርሱን ደስ ያሰኘው፡፡ + +\s5 +\v 35 ኅጥአን ከምድር ይጥፉ ዐመፀኞች ከእንግዲህ አይኑሩ፡፡ ነፍሴ ሆይ፣ ያህዌን አመስግኚ፡፡ ያህዌ ይመስገን፡፡ + +\s5 +\c 105 +\p +\v 1 ያህዌን አመስግኑ፣ ስሙንም ጥሩ ሥራውንም በሕዝቦች መካከል ግለጡ፡፡ +\v 2 ለእርሱ የምስጋና መዝሙር አቅርቡ ድንቅ ሥራዎቹን ሁሉ ተናገሩ፡፡ +\v 3 በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ ያህዌን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌንና ብርታቱን ፈልጉ ፊቱንም ዘወትር ፈልጉ፡፡ +\v 5 ያደረጋቸውን ድንቅ ሥራዎች ተአምራቱንና ከአፉ የወጣውን ፍርድ ፈልጉ፡፡ +\v 6 እናንት የአገልጋዩ የአብርሃም ዘሮች እርሱ የመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች ሆይ አስታውሱ፡፡ + +\s5 +\v 7 እርሱ አምላካችን ያህዌ ነው ፍርዱም በምድር ሁሉ ላይ ነው፡፡ +\v 8 ኪዳኑን ለዘላለም፣ ያዘዘውንም ቃል እስከ ሺህ ትውልድ ዘመን ያስታውሳል፡፡ + +\s5 +\v 9 ከአብርሃም ጋር ያደረገውን ኪዳን ለይስሐቅም በመሐላ የሰጠውን ተስፋ አይረሳም፡፡ +\v 10 ይህን ለያዕቆብ ሥርዐት ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን አድርጐ አጸናው፡፡ +\v 11 እንዲህም አለ፣ «የርስትህ ድርሻ እንዲሆን የከነዓንን ምድር እሰጥሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 12 ይህን ያለው እነርሱ በቁጥር አነስተኞች፣ እጅግ ጥቂትና ባይተዋሮች ሳሉ፣ +\v 13 ከሕዝብ ወደ ሕዝብ ሲንከራተቱ፣ ከአንዱ መንግሥት ወደ ሌላው መንግሥት ሲቅበዘበዙ ነበር፡፡ + +\s5 +\v 14 ማንም እንዲጨቁናቸው አልፈቀደም ስለ እነርሱም ነገሥታትን ገሠጸ፡፡ +\v 15 «የቀባኋቸውን አትንኩ፤ ነቢያቶቼንም አትጉዱ» አለ፡፡ + +\s5 +\v 16 በምድር ላይ ችጋርን ጠራ የምግብንም አቅርቦት ሁሉ አቋረጠ፡፡ +\v 17 ከእነርሱ አስቀድሞ በባርነት የተሸጠው ዮሴፍን ላከ፡፡ + +\s5 +\v 18 እግሮቹ በእግር ብረት ተላላጡ አንገቱም ላይ የብረት ማነቆ ገባ፡፡ +\v 19 የተናገረው እስኪፈጸም ድረስ የያህዌ ቃል ፈተነው፡፡ + +\s5 +\v 20 እርሱን እንዲፈቱ ንጉሡ አገልጋዮቹን ላከ፤ የሕዝቦችም ገዢ ነጻ አወጣው፡፡ +\v 21 የቤቱ ጌታ የንብረቱም ሁሉ አስተዳዳሪ አደረገው፡፡ +\v 22 በንጉሡ ባለ ሥልጣኖች ላይ አዛዥ ሆነ ለንጉሡም አማካሪዎች ጥበብን እንዲያስተምር ሥልጣን ተሰጠው፡፡ +\v 23 ከዚያም እስራኤል ወደ ግብፅ ሄደ እስከ ጊዜው ድረስ ያዕቆብ በካም ምድር ተቀመጠ፡፡ + +\s5 +\v 24 ያህዌ ሕዝቡን እጅግ አበዛ ከጠላቶቻቸውም ይልቅ ብርቱ አደረጋቸው፡፡ +\v 25 ሕዝቡን እንዲጠሉ ባርያዎቹንም እንዲበድሉ ልባቸውን አስጨከነ፡፡ +\v 26 ባርያውን ሙሴን እርሱ የመረጠውንም አሮንን ላከ፡፡ +\v 27 በግብፃውያን መካከል ምልክቶችን በካም ምድርም ድንቆችን አደረጉ፡፡ + +\s5 +\v 28 ጨለማን ልኮ ምድርን ጽልመት አለበሳት ይሁን እንጂ ትእዛዞቹን አልፈጸሙም፡፡ +\v 29 ውሃቸውን ወደ ደም ለወጠ ዓሣዎቻቸውንም ፈጀ፡፡ +\v 30 የነገሥታት እልፍኝ እንኳ ሳይቀር ምድራቸው በእንቁራሪት ተሸፈነች፡፡ + +\s5 +\v 31 እርሱ ሲናገር ተናካሽ ዝንቦችና ተናዳፊ ትንኞች በአገራቸው ተርመሰመሱ፡፡ +\v 32 በአገራቸው ላይ የበረዶ ድንጋይና መብረቅ አወረደ፡፡ +\v 33 ወይናቸውንና በለሳቸውን መታ ሌሎች ዛፎቻቸውንም ሰባበረ፡፡ + +\s5 +\v 34 እርሱ ሲናገር አንበጣ መጣ ስፍር ቁጠር የሌለውም ኩብኩባ ከተፍ አለ፡፡ +\v 35 አንበጣ የምድሪቱን ዕፅዋት ሁሉ በላ እህላቸውንም ሁሉ ፈጀ፡፡ +\v 36 ደግሞም የእያንዳንዱን ግብፃዊ በኩር ሁሉ የኃይላቸውንም ሁሉ በኩራት መታ፡፡ + +\s5 +\v 37 እስራኤላውያንን ከወርቅና ከብር ጋር ከዚያ መርቶ አወጣ፤ ከነገዶቻቸው አንዱ እንኳ አልተደናቀፈም፡፡ +\v 38 እጅግ ፈርተዋቸው ነበርና እስራኤላውያን አገር ለቀው ሲወጡ ግብፅ ደስ አላት፡፡ +\v 39 በሚሄዱበት ጊዜ በደመና ጋረዳቸው እሳትም በሌሊት አበራላቸው፡፡ + +\s5 +\v 40 ምግብ እንዲሰጣቸው በለመኑት ጊዜ ድርጭት አመጣላቸው የሰማይንም እንጀራ አጠገባቸው፡፡ +\v 41 ዐለቱን ሰነጠቀ፤ ውሃም ተንዶለዶለ +\v 42 ለባርያው ለአብርሃም የሰጠውን ቅዱስ የተስፋ ቃል አስታውሶአልና + +\s5 +\v 43 ሕዝቡን በደስታ፣ ምርጦቹንም በእልልታ መራቸው፡፡ +\v 44 የሕዝቦችን ምድር ሰጣቸው የእነርሱንም ሀብት ወረሱ፡፡ +\v 45 ይህም ሥርዐቱን ይጠብቁ ዘንድ ሕጉንም ይፈጽሙ ዘንድ ነው፡፡ ያህዌ ይመስገን + +\s5 +\c 106 +\p +\v 1 ያህዌን አመስግኑ ቸር ነውና ያህዌን አመስግኑ ምሕረቱም ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 2 የያህዌን ብርቱ ሥራ ማን ሊናገር ይችላል? ምስጋናውንስ ሁሉ ማን ተናግሮ ይጨርሳል? + +\s5 +\v 3 ዘወትር መልካሙንና ትክክል የሆነውን የሚያደርጉ የተባረኩ ናቸው፡፡ +\v 4 ያህዌ ሆይ፣ ለሕዝብህ ሞገስ ስታደርግ አስበኝ፤ በምታድናቸውም ጊዜ ርዳኝ፡፡ +\v 5 ይኸውም፣ አንተ የመረጥሃቸውን መበልጸግ እንዳይ፣ በሕዝብህ ደስ መሰኘት እኔንም ደስ እንዲለኝ በርስትህም ክብር መመካት እንድችል ነው፡፡ + +\s5 +\v 6 እኛም እንደ አባቶቻችን ኃጢአት ሠራን፣ በደልን፣ ክፉም አደረግን፡፡ +\v 7 አባቶቻችን በግብፅ ምድር ያደረግኸውን አላስተዋሉም፡፡ ብዙዎቹን የቸርነት ሥራዎቹን አላስተዋሉም፡፡ በባሕሩ አጠገብ፣ ቀይ ባሕር አጠገብ ዐመፁብህ፡፡ + +\s5 +\v 8 እርሱ ግን የኃይሉን ታላቅነት ለማሳየት ስለ ስሙ አዳናቸው፡፡ +\v 9 ቀይ ባሕርን ገሠጸ፤ እርሱም ደረቀ በምድረ በዳ እንደሚታለፍ በጥልቅ ውሃ መካከል መራቸው፡፡ + +\s5 +\v 10 ከባላጋራቸው እጅ አዳናቸው ከጠላትም እጅ ታደጋቸው፡፡ +\v 11 ባላጋራዎቻቸውን ውሃ ዋጣቸው ከእነርሱ አንድ አልተረፈም፡፡ +\v 12 ከዚያ በኋላ የተስፋ ቃሉን አመኑ በዝማሬም አመሰገኑት፡፡ + +\s5 +\v 13 ሆኖም፣ ወዲያውኑ እርሱ ያደረገውን ረሱ በምክሩም ለመሄድ አልታገሡም፡፡ +\v 14 በምድረ በዳ ብዙ ነገር ተመኙ፤ በበረሐም እግዚአብሔርን ተፈታተኑት፡፡ +\v 15 እርሱም የለመኑትን ሰጣቸው ነገር ግን የሚያኮሰምን ደዌ ሰደደባቸው፡፡ + +\s5 +\v 16 ሰፈር ውስጥ በሙሴ ላይ የተቀደሰው የያህዌ ካህን ላይ ቀኑ፡፡ +\v 17 ምድር ተከፍታ ዳታንን ዋጠች የአቤሮንንም ሰዎች ሰለቀጠች፡፡ +\v 18 በመካከላቸው እሳት ነድዶ ነበልባልም ክፉዎችን ፈጅቶ አስወገደ፡፡ + +\s5 +\v 19 በኮሬብ ጥጃ ሠሩ ቀልጦ ለተሠራ ምስል ሰገዱ፡፡ +\v 20 ክብራቸውን ሣር በሚበላ የበሬ ምስል ለወጡ፡፡ +\v 21 በግብፅ ታላላቅ ነገሮች ያደረገውን ያዳናቸውን እግዚአብሔርን ረሱ፡፡ + +\s5 +\v 22 እርሱ በካም ምድር ድንቅ ሥራ በቀይ ባሕርም አስደናቂ ነገር አደረገ፡፡ +\v 23 ቁጣውን እንዲመልስ እርሱ የመረጠው ሙሴ በመካከል ባይገባ ኖሮ እነርሱን ለማጥፋት ወስኖ ነበር፡፡ + +\s5 +\v 24 መልካሚቱን ምድር ናቁ በተስፋ ቃሉም አላመኑም፡፡ +\v 25 ድንኳናቸው ውስጥ አጉረመረሙ ለያህዌም አልታዘዙም፡፡ + +\s5 +\v 26 ስለዚህ በምድረ በዳ እንደሚያጠፋቸው እጁን አንሥቶ ማለ፡፡ +\v 27 ዘሮቻቸውን በአሕዛብ መካከል ለመጣል እነርሱንም ወደ ተለያየ አገሮች እንደሚበትናቸው ማለ፡፡ + +\s5 +\v 28 ብዔል ፌጐርን አመለኩ ለሙታን የተሠዋውን በሉ፡፡ +\v 29 በተግባራቸውም እግዚአብሔርን አስቆጡት፤ በዚህም ምክንያት በመካከላቸው መቅሠፍት ተነሣ፡፡ + +\s5 +\v 30 ፊንሐስ ተነሥቶ ጣልቃ ገባ፤ መቅሠፍቱም ተገታ፡፡ +\v 31 ይህም ከትውልድ እስከ ትውልድ ለዘላለም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት፡፡ + +\s5 +\v 32 ደግሞም በመሪባ ውሃ አጠገብ ያህዌን አስቆጡት ሙሴም በእነርሱም ምክንያት ችግር ላይ ወደቀ፡፡ +\v 33 ሙሴን ስላስመረሩት ራሱን ባለ መቆጣጠር ተናገረ፡፡ +\v 34 እግዚአብሔር ባዘዛቸው መሠረት ሕዝቦችን ከማጥፋት ወደ ኃላ አሉ፡፡ +\v 35 እንዲያውም ከእነርሱ ጋር በመደባለቅ የእነርሱን መንገድ ተማሩ፡፡ +\v 36 ጣዖቶቻቸውን አመለኩ፤ ይህም ወጥመድ ሆነባቸው፡፡ + +\s5 +\v 37 ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን ለአጋንንት ሠዉ፡፡ +\v 38 የወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን ደም ለከነዓን ጣዖቶች መሥዋዕት በማቅረባቸው ንጹሕ ደም አፈሰሱ ምድሪቱንም አረከሱ፡፡ +\v 39 እነርሱ በሥራቸው ረከሱ በድርጊታቸውም አመንዝሮች ሆኑ፡፡ + +\s5 +\v 40 ስለዚህ ያህዌ በሕዝቡ ላይ እጅግ ተቆጣ ርስቱንም ተጸየፈ፡፡ +\v 41 ለአሕዛብ አሳልፎ ሰጣቸው ጠላቶቻቸውም በላያቸው ገዢዎች ሆኑባቸው፡፡ + +\s5 +\v 42 ጠላቶቻቸው ጨቆኑአቸው በሥልጣናቸውም ሥር አደረጓቸው፡፡ +\v 43 እርሱ ብዙ ጊዜ ታደጋቸው እነርሱ ግን ዐመፅ ማድረጋቸውን ገፉበት፡፡ በገዛ ኃጢአታቸው ተዋረዱ፡፡ + +\s5 +\v 44 ይህም ሆኖ እንዲረዳቸው ወደ እርሱ ሲጮኹ ጩኸታቸውን ሰማ ጭንቀታቸውንም ተመለከተ፡፡ +\v 45 ለእነርሱ ሲል ቃል ኪዳኑን አሰበ እንደ ምሕረቱም ብዛት ከቁጣው ተመለሰ፡፡ +\v 46 የሚጨቁኑአቸው ሁሉ እንዲራሩላቸው አደረገ፡፡ + +\s5 +\v 47 አምላካችን ያህዌ ሆይ፣ አድነን፤ ለቅዱስ ስምህ ምስጋና እንድናቀርብ፣ አንተን በመወደስ እንድንከብር ከሕዝቦች መካከል ሰብስበህ አምጣን፡፡ +\v 48 የእስራኤል አምላክ ያህዌ ከዘላለም እስከ ዘለላም ይባረክ፡፡ ሕዝብም ሁሉ አሜን ይበል፡፡ ያህዌ ይባረክ፡፡ + +\s5 +\c 107 +\p +\v 1 ቸር ነውና ምሕረቱም ለዘላለም ነውና ያህዌን አመስግኑ፡፡ +\v 2 ያህዌ የተቤዣቸው ከጠላትም እጅ የታደጋቸው ይናገሩ፡፡ +\v 3 ለባዕድ ምድር፣ ከምሥራቅና ከምዕራብ፣ ከሰሜንና ከደቡብ ሰበሰባቸው፡፡ + +\s5 +\v 4 በበረሐ መንገድ ጠፍቶአቸው በምድረ በዳ ተንከራተቱ የሚኖሩበትም ከተማ አላገኙም፡፡ +\v 5 ተራቡ፤ ተጠሙ ከድካም የተነሣ ዛሉ፡፡ +\v 6 በተጨነቁ ጊዜ ወደ ያህዌ ጮኹ እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው፡፡ +\v 7 ወደሚኖሩበት ከተማ በቀና መንገድ መራቸው፡፡ + +\s5 +\v 8 ለሰው ልጆች ስላደረገው ድንቅ ነገርና ስለዘላለማዊ ፍቅሩ ሕዝቡ ያህዌን ያመስግኑ፡፡ +\v 9 እርሱ የተጠማችውን ነፍስ አርክቶአልና የተራበችውን ነፍስ በመልካም ነገር አጥግቦአል፡፡ +\v 10 አንዳንዶች በሰንሰለት ታስረው ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ + +\s5 +\v 11 ይህም የሆነው በእግዚአብሔር ቃል በማመፃቸው የልዑልንም ምክር በማቃለላቸው ነበር፡፡ +\v 12 በከባድ ሥራ ልባቸውን አዛለ ተዘለፈለፉ፤ የሚረዳቸውም አላገኙም፡፡ +\v 13 በተጨነቁ ጊዜ ወደ ያህዌ ጮኹ፤ እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው፡፡ + +\s5 +\v 14 ከነበሩበት ድቅድቅ ጨለማ አወጣቸው የታሰሩበትንም ሰንሰለት ሰባበረ፡፡ +\v 15 ለሰው ልጆች ስላደረገው ድንቅ ነገርና ስለ ዘላለማዊ ፍቅሩ ሕዝቡ ያህዌን ያመስግኑ፡፡ +\v 16 እርሱ የናሱን በሮች ሰብሮአልና የብረቱንም መወርወሪያ ቆርጦአል፡፡ + +\s5 +\v 17 አንዳንዶች የዐመፃን መንገድ በመከተላቸው ቂሎች ሆኑ ከበደላቸው የተነሣ ችግር ውስጥ ወደቁ፡፡ +\v 18 ምግብ የመብላት ፍላጐት አጡ፤ ወደ ሞት በሮችም ተቃረቡ፡፡ +\v 19 በተጨነቁ ጊዜ ወደ ያህዌ ጮኹ እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው፡፡ + +\s5 +\v 20 ቃሉን ልኮ ፈወሳቸው፡፡ ከመቃብር አፋፍ መለሳቸው፡፡ +\v 21 ለሰው ልጆች ስላደረገው ድንቅ ነገርና ስለ ዘላለማዊ ፍቅሩ ሕዝቡ ያህዌን ያመስግኑ፡፡ +\v 22 የምስጋና መሥዋዕት ያቅርቡለት በዝማሬም ሥራውን ያውጁ፡፡ + +\s5 +\v 23 አንዳንዶች በመርከብ እየተጓዙ ንግዳቸውን ያካሄዱ ነበር፡፡ +\v 24 እነርሱ የያህዌን ሥራ አዩ ድንቅ አድራጐቱንም በጥልቅ ውስጥ ተመለከቱ፡፡ + +\s5 +\v 25 ትእዛዝ በሰጠ ጊዜ ባሕሩን የሚያናውጥ ዐውሎ ነፋስ ነፈሰ፡፡ +\v 26 ወደ ሰማይ ወጡ፤ ወደ ጥልቅም ወረዱ ከመከራቸው የተነሣ ልባቸው ቀለጠ፡፡ +\v 27 እንደ ሰካራም ዞሮባቸው ወዲያ ወዲህ ተንገዳገዱ፤ መላው ጠፍቶባቸው የሚያደርጉትን አጡ፡፡ + +\s5 +\v 28 በመከራቸው ጊዜ ወደ ያህዌ ጮኹ፤ እርሱም ከመከራቸው አዳናቸው፡፡ +\v 29 ዐውሎ ነፋሱን ጸጥ አደረገ ሞገዱም ረጭ አለ፡፡ +\v 30 ባሕሩ ጸጥ በማለቱ ደስ አላቸው ወዳሰቡትም ወደብ አደረሳቸው፡፡ + +\s5 +\v 31 ለሰው ልጆች ስላደረገው ድንቅ ነገር ስለ ዘላለማዊ ፍቅሩ ሕዝቡ ያህዌን ያመስግኑ፡፡ +\v 32 በሕዝቦች ጉባኤ መካከል ከፍ ከፍ ያደርጉት በሽማግሌዎችም ሸንጐ ያመስግኑት፡፡ + +\s5 +\v 33 ወንዞችን ወደ ምድረ በዳ የውሃ ምንጮችንም ወደ ደረቅ ምድር ለወጠ፡፡ +\v 34 ከነዋሪዎቿ ክፋት የተነሣ ፍሬያማዋን መሬት ደረቅ ምድር አደረገ፡፡ +\v 35 ምድረ በዳውን ወደ ኩሬ ደረቁንም ምድር ወደ ውሃ ምንጭ ቀየረ፡፡ + +\s5 +\v 36 የተራቡትን በዚያ አኖረ የሚኖሩበትንም ከተማ ሠሩ፡፡ +\v 37 በእርሻዎች እህል ዘሩ ወይንን ተከሉ፤ ብዙ መከርም ሰበሰቡ፡፡ +\v 38 ይባርካቸዋል፤ እነርሱም እጅግ ይበዛሉ የከብቶቻቸውም ብዛት እንዲያንስ አያደርግም፡፡ + +\s5 +\v 39 በጭንቅ፣ በመከራና በሐዘን፣ ቁጥራቸው አንሶ ተዋርደው ነበር፤ በመኳንንቱም ላይ መናቅን አወረደባቸው +\v 40 መውጪያ መግቢያው በማይታወቅ በረሐ ውስጥም አንከራተታቸው፡፡ + +\s5 +\v 41 ሆኖም፣ ችግረኞችን ከስቃይ አወጣቸው ለቤተ ሰቡም እንደ በግ መንጋ ተጠነቀቀ፡፡ +\v 42 ቅኖች ይህን ዐይተው ደስ ይላቸዋል ክፋትም አፏን ትዘጋለች፡፡ +\v 43 አስተዋይ የሆነ ሰው ይህን ልብ ይበል፤ እርሱም የያህዌን ምሕረት ያስተውል፡፡ + +\s5 +\c 108 +\p +\v 1 እግዚአብሔር ሆይ፣ ልቤ ጽኑ ነው፡፡ እዘምራለሁ፤ በፍጹም ልቤም እዘምራለሁ፡፡ +\v 2 በገናና መሰንቆም ተነሡ፤ እኔም ማልጄ እነሣለሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ በመንግሥታት መካከል የምስጋና መዝሙር አቀርብልሃለሁ +\v 4 ምሕረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናትና ታማኝነትህም እስከ ጠፈር ይደርሳል፡፡ + +\s5 +\v 5 አምላክ ሆይ፣ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል ክብርህም በምድር ሁሉ ይንሰራፋ፡፡ +\v 6 የምትወደው ሕዝብህ ይድን ዘንድ በቀኝ እጅህ ታደግ መልሰልኝም፡፡ + +\s5 +\v 7 እግዚአብሔር በቅድስናው እንዲህ አለ፤ ደስ እያለኝ ሴኬምን እከፍላለሁ የሱከትንም ሸለቆ እለካለሁ፡፡ +\v 8 ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤ ኤፍሬም የራስ ቁሬ፣ ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው፡፡ + +\s5 +\v 9 ሞዓብ መታጠቢያ ገንዳዬ ነው በኤዶም ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤ በፍልስጥኤም ላይ በድል አድራጊነት እፎክራለሁ፡፡ +\v 10 ወደ ተመሸገችው ከተማ ማን ይወስደኛል? ወደ ኤዶምስ ማን ያደርሰኛል? + +\s5 +\v 11 እግዚአብሔር ሆይ፣ ያጣልኸን አንተ አይደለህምን? ከሰራዊታችንም ጋር ወደ ጦርነት አልወጣህም፡፡ +\v 12 አሁንም የሰው ማዳን ከንቱ ነውና በጠላታችን ላይ ድል አቀዳጀን፡፡ +\v 13 በእግዚአብሔር ረድኤት ድል እናደርጋለን ጠላቶቻችንንም ከእግሩ በታች የሚረግጥ እርሱ ነው፡፡ + +\s5 +\c 109 +\p +\v 1 የማመሰግንህ አምላክ ሆይ፣ ዝም አትበለኝ +\v 2 ክፉዎችና አታላዮች አጥቅተውኛልና በእኔ ላይ ሐሰት ይናገራሉ፡፡ +\v 3 በጥላቻ ዙሪያዬን ከበቡኝ ያለ ምክንያትም በድለውኛል፡፡ + +\s5 +\v 4 ስወዳቸው ይወነጅሉኛል፤ እኔ ግን ለእነርሱ እጸልያለሁ፡፡ +\v 5 በመልካም ፈንታ ክፋትን በወደድኃቸው ፈንታ ጥላቻን ይመልሱልኛል፡፡ + +\s5 +\v 6 በእንዲህ ያለው ሰው፣ ክፉ ሰው በላዩ ሹም ከሳሽም በቀኙ ይቁም፡፡ +\v 7 በተሟገተ ጊዜ ተረትቶ ይግባ ጸሎቱ እንኳ እንደ ኃጢአት ይቆጠርበት፡፡ + +\s5 +\v 8 ዕድሜው ይጠር ሹመቱን ሌላው ይውሰደው፡፡ +\v 9 ልጆቹ ድኻ አደጐች ይሁኑ ሚስቱም መበለት ትሁን፡፡ +\v 10 ልጆቹ ይንከራተቱ፤ ለማኞችም ይሁኑ ከፈረሰው ቤታቸው ይሰደዱ፡፡ + +\s5 +\v 11 ንብረቱ ሁሉ በዕዳ ይያዝበት ለፍቶ ያገኘውን ጥሪት ባዕዳን ሰዎች ይውሰዱበት፡፡ +\v 12 ማንም ሰው ደግ አይሁንለት ለድኻ አደግ ልጆቹ የሚራራላቸው አይገኝ፡፡ +\v 13 ዘሩ ተለይቶ ይጥፋ ስማቸውም በሚቀጥለው ትውልድ ይደምሰስ፡፡ + +\s5 +\v 14 የአባቶቹ ኃጢአት በያህዌ ፊት ይታሰብ የእናቱም ኃጢአት አይደምሰስ፡፡ +\v 15 በደላቸው ሁልጊዜ በያህዌ ፊት ይሁን የእነርሱ መታሰቢያ ግን ጨርሶ ይጥፋ፡፡ +\v 16 ይህ ሰው ምሕረት ከማድረግ ይልቅ፣ ችግረኛውንና ምስኪኑን ልቡም የቆሰለውን እስከ ሞት አሳድዶአልና ያህዌ ይህን ያደርግበት + +\s5 +\v 17 መርገምን ወደደ፤ ወደ እርሱም መጣች መባረክ አልወደደም በረከት ከእርሱ ይራቅ፡፡ +\v 18 መርገምን እንደ ልብስ ለበሳት፤ ስለዚህ መርገም እንደ ውሃ ወደ ውስጥ ሰውነቱ፣ እንደ ዘይትም ወደ አጥንቱ ዘለቀች፡፡ + +\s5 +\v 19 ገላውን እንደሚሸፍንበት ልብስ፣ ዘወትር እንደሚታጠቀውም መቀነት ትሁነው፡፡ +\v 20 ለሚወነጅሉኝ ሰዎች፣ እኔ ላይ ክፉ ለሚናገሩ ያህዌ የሚከፍለው ይኸው ይሁን፡፡ + +\s5 +\v 21 አምላኬ ያህዌ ሆይ፣ ስለ ስምህ ስትል እኔን በበጐ ተመልከተኝ፡፡ +\v 22 እኔ ድኽና ችግረኛ ነኝ ልቤም በውስጤ ቆስሎአል፡፡ +\v 23 እንደ ምሽት ጥላ ላልፍ ተቃርቤአለሁ እንደ አንበጣም ረግፌአለሁ፡፡ + +\s5 +\v 24 በጾም ምንያት ጉልበቴ ደከመ ሰውነቴም ከስቶ ዐመድ መሰለ፡፡ +\v 25 ለጠላቶቼ መሣለቂያ ሆንሁላቸው ሲያዩኝም ራሳቸውን ይነቀንቁብኛል፡፡ + +\s5 +\v 26 አምላኬ ያህዌ ሆይ፣ ርዳኝ ስለ ታማኝነትህም አድነኝ፡፡ +\v 27 ያህዌ ሆይ፣ እጅህ ይህን እንዳደረገች አንተም ይህን እንደ ፈጸምህ ይወቁ፡፡ + +\s5 +\v 28 እነርሱ ቢራገሙ እንኳ አንተ ግን ባርከኝ እኔን ሲያጠቁኝ ይዋረዱ ባርያህ ግን ሐሤት ያደርጋል፡፡ +\v 29 ባላንጣዎቼ ውርደትን እንደ ልብስ ይልበሱ እፍረትንም እንደ ሸማ ይጐናጸፉ፡፡ + +\s5 +\v 30 በአንደበቴ ያህዌን እጅግ አመሰግለሁ በጉባኤም መካከል እባርከዋለሁ፡፡ +\v 31 በእርሱ ላይ ከሚፈርዱ ለማዳን እርሱ በችግረኛው ቀኝ ይቆማልና፡፡ + +\s5 +\c 110 +\p +\v 1 ያህዌ ጌታዬን፣ «ጠላቶችህን ለእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ» አለው፡፡ + +\s5 +\v 2 ያህዌ ብርቱ በትርህን ከጽዮን ወደ ውጭ ይሰዳል አንተም በጠላቶችህ መካከል ትገዛለህ፡፡ +\v 3 በኃይልህ ቀን ተከታዮችህ የተቀደሰ ልብስ ተጐናጽፈው በፈቃዳቸው ይከተሉሃል፡፡ ከንጋት ማሕፀን ጐልማሳነትህ እንደ ጠል ይወጣል፡፡ + +\s5 +\v 4 «እንደ መልከጼዴቅ ሥርዐት አንተ ለዘላለም ካህን ነህ» ብሎ ያህዌ ምሎአል፤ እርሱም ሐሳቡን አይለውጥም፡፡ + +\s5 +\v 5 ጌታ በቀኝህ ነው በቁጣው ቀን ነገሥታትን ይገድላል፡፡ +\v 6 በሕዝብ ላይ ይፈርዳል የጦር ሜዳዎችን ሬሳ በሬሳ ያደርጋል፡፡ የብዙ አገሮችን ነገሥታት ይደመሰሳል፡፡ + +\s5 +\v 7 መንገድ ዳር ካለች ፈሳሽ ውሃ ይጠጣል ከድል በኃላ ራሱን ቀና ያደርጋል፡፡ + +\s5 +\c 111 +\p +\v 1 ያህዌ ይመስገን፡፡ በቅኖች ሸንጐ በጉባኤም መካከል በፍጹም ልቤ ያህዌን አመሰግናለሁ፡፡ +\v 2 የያህዌ ሥራ ታላቅ ናት፤ የሚፈልጓትም ሁሉ አጥብቀው ይናፍቋታል፡፡ +\v 3 ሥራው ባለ ግርማና ባለ ክብር ነው ጽድቁም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌ ቸርና መሐሪ ነው ሲታወስ የሚኖር ድንቅ ሥራ አደረገ፡፡ +\v 5 ለሚፈሩት ምግባቸውን ይሰጣል ኪዳኑንም ዘወትር ያስባል፡፡ +\v 6 ለእነርሱ የአሕዛብን ርስት በመስጠት የአሠራሩን ብርታት አሳይቶአል፡፡ + +\s5 +\v 7 የእጁ ሥራ እውነተኛና ቅን ነው ትእዛዞቹም የታመኑ ናቸው፡፡ +\v 8 እነርሱም ለዘላለም የጸኑ ናቸው በታማኝነትና በቅንነት ይጠበቃሉ፡፡ +\v 9 ለሕዝቡ ድልን ሰጠ ኪዳኑን ለዘላለም አዘዘ ስሙም የተቀደሰና የተፈራ ነው፡፡ + +\s5 +\v 10 ያህዌን መፍራት የጥበብ መጀመሪያ ነው ትእዛዙንም የሚጠብቁ ጥሩ ማስተዋል አላቸው፡፡ ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል፡፡ + +\s5 +\c 112 +\p +\v 1 ያህዌ ይመስገን ያህዌን የሚፈራ በትእዛዞቹም እጅግ ደስ የሚሰኝ የተባረከ ነው፡፡ +\v 2 ዘሩ በምድር ላይ ኃያል ይሆናል የቅኖች ትውልድ ይባረካል፡፡ + +\s5 +\v 3 ሀብትና ብልጽግና ቤቱን ይሞላል ጽድቁም ለዘላለም ይኖራል፡፡ +\v 4 ምሕረትና ቸርነት፣ ቅንነትንም ለሚያደርግ ደግ ሰው በጨለማ ውስጥ ብርሃን ይወጣለታል፡፡ +\v 5 ሥራውን በትክክል የሚያከናውን፣ ለጋስና ሳይሰስት የሚያበድር ሰው መልካም ይሆንለታል፡፡ + +\s5 +\v 6 እርሱ ከቶውንም አይናወጥምና ጻድቅ ሰው ሲታወስ ይኖራል፡፡ +\v 7 እምነቱን ያህዌ ላይ ያደረገ ልበ ሙሉ ስለሆነ ክፉ ወሬ አያሸብረውም፡፡ + +\s5 +\v 8 ልቡ እግዚአብሔርን በመተማመን የጸና ነው፡፡ በመጨረሻ የጠላቶቹን ውድቀት ያያል፡፡ +\v 9 በልግስና ለድኾች ይሰጣል ጽድቁም ለዘላለም ይኖራል፡፡ በክብር ከፍ ከፍ ይላል፡፡ + +\s5 +\v 10 ክፉ ሰው ይህን፤ በማየት ይበሳጫል ጥርሱን ያፋጫል፤ እየመነመነም ይጠፋል፡፡ የክፉዎች ምኞት ትጠፋለች፡፡ + +\s5 +\c 113 +\p +\v 1 ያህዌ ይመስገን፡፡ የያህዌ አገልጋዮች ሆይ፣ የያህዌን ስም አመስግኑ፡፡ +\v 2 ከአሁን እስከ ዘላለም የያህዌ ስም ይመስገን፡፡ + +\s5 +\v 3 ከፀሐይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ የያህዌ ስም ይመስገን፡፡ +\v 4 ያህዌ ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤ ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው፡፡ + +\s5 +\v 5 እንደ አምላካችን እንደ ያህዌ በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው? +\v 6 ራሱን ዝቅ አድርጐ በሰማይና በምድር ያሉትንስ የሚያይ ማን ነው? + +\s5 +\v 7 ድኻውን ከትቢያ ያነሣል ችግረኛውንም ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፡፡ +\v 8 ከመኳንንት ጋር፣ ከሕዝቡም ሹማምንት ጋር ያስቀምጠዋል፡፡ + +\s5 +\v 9 መካኒቱን በቤት ያኖራታል ደስ የተሰኘች የልጆች እናት ያደርጋታል፡፡ ያህዌ ይመስገን! + +\s5 +\c 114 +\p +\v 1 እስራኤል ከግብፅ ወጥቶ ሲሄድ የያዕቆብም ቤት ከባዕድ ሕዝብ ተለይቶ ሲወጣ +\v 2 ይሁዳ ቅዱስ ማደሪያው እስራኤልም ግዛቱ ሆነ፡፡ + +\s5 +\v 3 ባሕር ዐይታ ሸሸች ዮርዳኖስም ወደ ላኋው ተመለሰ፡፡ +\v 4 ተራሮች እንደ አውራ በግ ፈነጩ ኮረብቶችም እንደ ጠቦት ዘለሉ፡፡ + +\s5 +\v 5 አንተ ባሕር ምን ሆነህ ሸሸህ? አንተስ ዮርዳኖስ ለምን ወደ ኃላህ ተመለስህ? +\v 6 እናንተ ተራሮች ስለምን እንደ አውራ በግ ፈነጫችሁ? ኮረብቶችስ ለምን እንደ ጠቦት ዘለላችሁ? +\v 7 ምድር ሆይ፣ በጌታ ፊት በያዕቆብ አምላክ ፊት ተንቀጥቀጪ፡፡ + +\s5 +\v 8 እርሱ ዐለቱን ወደ ውሃ ኩሬ ቋጥኙንም ወደ ውሃ ምንጭ ለወጠ፡፡ + +\s5 +\c 115 +\p +\v 1 ለእኛ ሳይሆን፣ ያህዌ ሆይ ለእኛ ሳይሆን ስለ ፍቅርህ፣ ስለ ታማኝነትህ ስምህን አክብረው፡፡ +\v 2 ስለ ምን ሕዝቦች፣ «አምላካቸው የት አለ?» ይበሉ + +\s5 +\v 3 አምላካችን በሰማይ ነው እርሱ ደስ የሚለውን አደረገ፡፡ +\v 4 የአሕዛብ ጣዖቶች ብርና ወርቅ የሰው እጅ ሥራዎችም ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 5 አፍ አላቸው ግን አይናገሩም ዐይን አላቸው ግን አያዩም +\v 6 ጆሮ አላቸው ግን አይሰሙም አፍንጫ አላቸው ግን አያሸቱም፡፡ + +\s5 +\v 7 እጅ አላቸው ግን አይዳሰስም እግር አላቸው ግን አይራመዱም ድምፅም ማሰማት አይችሉም፡፡ +\v 8 የሠሩአቸውና የሚታመኑባቸው ሁሉ እንደ እነዚህ ጣዖቶች ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 9 የእስራኤል ቤት ሆይ፣ በያህዌ ታመኑ ረዳታችሁና ጋሻችሁ እርሱ ነው፡፡ +\v 10 የአሮን ቤት ሆይ፣ በያህዌ ታመኑ ረዳታችሁና ጋሻችሁ እርሱ ነው፡፡ +\v 11 እናንት ያህዌን የምትፈሩ፣ በእርሱ ታመኑ ረዳታችሁና ጋሻችሁ እርሱ ነው፡፡ + +\s5 +\v 12 ያህዌ ያስበናል፤ ይባርከናልም፤ እርሱ የእስራኤልን ቤት ይባርካል የአሮንንም ቤት ይባርካል፡፡ +\v 13 ታላላቆችም ሆኑ ታናናሾች እርሱ የሚፈሩትን ሁሉ ይባርካል፡፡ +\v 14 ያህዌ እናንተንና ልጆቻችሁን በባርኮቱ ይባርካችሁ፡፡ + +\s5 +\v 15 ሰማይና ምድርን የፈጠረ ያህዌ ይባርካችሁ፡፡ +\v 16 ሰማያት የእግዚአብሔር ናቸው ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት፡፡ + +\s5 +\v 17 ወደ ዝምታ ዓለም፣ ወደ መቃብር የወረዱ ሙታን ያህዌን ሊያመሰግኑ አይችሉም፡፡ +\v 18 እኛ ግን፣ ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም ያህዌን እንባርካለን፡፡ ያህዌ ይመስገን፡፡ + +\s5 +\c 116 +\p +\v 1 የልመናዬን ድምፅ ስለ ሰማ ያህዌን ወደድሁት፡፡ +\v 2 እርሱ ሰምቶኛልና በሕይወት ዘመኔ ሁሉ ወደ እርሱ እጣራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 የሞት ወጥመድ ያዘኝ የሲኦልም ጣር አገኘኝ ጭንቅና ሐዘን በረታብኝ፡፡ +\v 4 እኔም የያህዌን ስም ጠራሁ «ያህዌ ሆይ፣ እባክህ ነፍሴን አድናት፡፡» + +\s5 +\v 5 ያህዌ ቸርና መሐሪ ነው፡፡ አምላካችን ርኅሩኅ ነው፡፡ +\v 6 አምላካችን ገሮችን ይጠብቃል እኔም በተቸገርኩ ጊዜ አድኖኛል፡፡ + +\s5 +\v 7 ያህዌ መልካም ነገር አድርጐልኛልና ከእንግዲህ ነፍሴ ወደ እረፍት ቦታ ትመለሳለች፡፡ +\v 8 አንተ ነፍሴን ከሞት፣ ዐይኔን ከእንባ እግሮቼን ከመሰናክል አድነሃልና፡፡ + +\s5 +\v 9 እኔም በሕያዋን ምድር ያህዌን አገለግላለሁ፡፡ +\v 10 «እጅግ ተጨንቄአለሁ» ባልሁ ጊዜ እንኳ በእርሱ ማመኔን አልተውሁም፡፡ +\v 11 ግራ በተጋባሁ ጊዜ፣ «ሰው ሁሉ ሐሰተኛ ነው» አልሁ፡፡ + +\s5 +\v 12 ስላደረገልኝ መልካም ነገር ሁሉ ለያህዌ ምን ልክፈለው? +\v 13 የመዳንን ጽዋ አነሣለሁ የያህዌንም ስም እጠራለሁ፡፡ +\v 14 በሕዝቡ ሁሉ ፊት ስእለቴን ለያህዌ እፈጽማለሁ፡፡ +\v 15 የቅዱሳኑ ሞት በያህዌ ፊት የከበረ ነው፡፡ + +\s5 +\v 16 ያህዌ ሆይ፣ እኔ በእውነት ባርያህ ነኝ፣ የሴት ባርያህም ልጅ ነኝ፡፡ ከእስራቴም ፈታኸኝ፡፡ +\v 17 ለአንተ የምስጋና መሥዋዕት አቀርባለሁ የያህዌንም ስም እጠራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 18 በሕዝቡ ሁሉ ፊት ስእለቴን ለያህዌ እፈጽማለሁ +\v 19 ኢየሩሳሌም ሆይ፣ በመካከልሽ በያህዌ ቤት አደባባይ ይህን አደርጋለሁ፡፡ + +\s5 +\c 117 +\p +\v 1 አሕዛብ ሁላችሁ ያህዌን አመስግኑት ሕዝቦችም ሁሉ በምስጋና ከፍ ከፍ አድርጉት፡፡ +\v 2 እርሱ ለእኛ ያሳየው ምሕረት ታላቅ ነውና የያህዌ ታማኝነት ጸንቶ ይኖራል፡፡ ያህዌ ይመስገን፡፡ + +\s5 +\c 118 +\p +\v 1 ቸር ነውና ያህዌን አመስግኑት ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች፡፡ +\v 2 የእስራኤል ሕዝብ ሁሉ «ምሕረቱ ለዘላለም ነው» ይበል፡፡ + +\s5 +\v 3 የአሮን ቤት፣ «ምሕረቱ ለዘላለም ነው» ይበል፡፡ +\v 4 ያህዌን የሚፈሩ ሁሉ፣ «ምሕረቱ ለዘላለም ነው» ይበሉ፡፡ + +\s5 +\v 5 በተጨነቅሁ ጊዜ ያህዌን ጠራሁት እርሱም ሰማኝ፤ ነጻም አወጣኝ፡፡ +\v 6 ያህዌ ከእኔ ጋር ነው፤ አልፈራም ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል? +\v 7 ይረዳኝ ዘንድ ያህዌ ከእኔ ጋር ነው የጠላቶቼንም ውድቀት አያለሁ፡፡ + +\s5 +\v 8 በሰው ከመታመን ይልቅ ያህዌን መከታ ማድረግ ይሻላል፡፡ +\v 9 በመሪዎች ከመመካት ይልቅ ያህዌን መጠጊያ ማድረግ ይሻላል፡፡ + +\s5 +\v 10 ሕዝቦች ሁሉ ከበቡኝ ነገር ግን በያህዌ ስም አሸነፍኃቸው +\v 11 መክበቡንስ፣ ዙሪያዬን ከበቡኝ ነገር ግን በያህዌ ስም አሸነፍኃቸው፡፡ +\v 12 እንደ ንብ መንጋ ከበቡኝ ሆኖም፣ እንደሚነድ እሾኽ ከሰሙ በእርግጥም በያህዌ ስም አሸነፍኃቸው፡፡ + +\s5 +\v 13 ሊጥሉኝ ገፈተሩኝ ያህዌ ግን ረዳኝ፡፡ +\v 14 ያህዌ ብርታቴና ደስታዬ ነው፤ የሚታደገኝም እርሱ ነው፡፡ + +\s5 +\v 15 በጻድቃን ድንኳን፣ የእልልታና የሆታ ድምፅ፣ እንዲህ እያለ ያስተጋባል የያህዌ ቀኝ እጅ አሸነፈ፡፡ +\v 16 የያህዌ ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አለ፤ የያህዌ ቀኝ እጅ አሸነፈ፡፡ + +\s5 +\v 17 በሕይወት እኖራለሁ እንጂ፣ አልሞትም የያህዌንም ሥራ ገና እናገራለሁ፡፡ +\v 18 ያህዌ ክፉኛ ቀጥቶኝ ነበር ነገር ግን ለሞት አሳልፎ አልሰጠኝም፡፡ + +\s5 +\v 19 የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ ወደዚያ ገብቼ ያህዌን አመሰግናለሁ፡፡ +\v 20 ይህች የያህዌ ደጅ ናት፤ ጻድቃንም በእርሷ በኩል ይገባሉ፡፡ +\v 21 ሰምተህ መልሰህልኛና፣ አዳኝም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 22 ግንበኞች የናቁት ድንጋይ የማእዘን ራስ ሆነ፡፡ +\v 23 ይህም የያህዌ ሥራ ነው ለዐይኖቻችንም ድንቅ ነው፡፡ + +\s5 +\v 24 ያህዌ የሠራት ቀን ይህች ናት፣ በእርሷ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም እናደርጋለን፡፡ +\v 25 ያህዌ ሆይ፣ እባክህ ድል አቀዳጀን! ያህዌ ሆይ፣ እባክህ አከናውንልን፡፡ + +\s5 +\v 26 በያህዌ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እኛም ከያህዌ ቤት ባረክናችሁ፡፡ +\v 27 ያህዌ አምላካችን ነው፤ ብርሃኑንም በላያችን አበራ መሥዋዕቱን መሠዊያው ቀንዶች ላይ በገመድ እሰሩ፡፡ +\v 28 አንተ አምላኬ ነህ፤ አመሰግንሃለሁ፤ አንተ አምላኬ ነህ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 29 ቸር ነውና ያህዌን አመስግኑ ምሕረቱም ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች፡፡ + +\s5 +\c 119 +\p +\v 1 መንገዳቸው ነቀፋ የሌለበት በያህዌም ሕግ የሚሄዱ የተባረኩ ናቸው፡፡ +\v 2 ትእዛኦቹን የሚጠብቁ በሙሉ ልባቸውም የሚፈልጉት የተባረኩ ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 3 በመንገዱ ይሄዳሉ እንጂ ዐመፅ አያደርጉም፡፡ +\v 4 ጠንቅቀን እንጠብቃት ዘንድ አንተ ሥርዐትን አዝዘሃል፡፡ + +\s5 +\v 5 ሥርዐትህን እጠብቅ ዘንድ ምነው መንገዴ ጽኑ በሆነልኝ ኖሮ! +\v 6 ትእዛዞችህን ሁሉ በጥንቃቄ ካስተዋልሁ እፍረት ከቶ አይደርስብኝም፡፡ + +\s5 +\v 7 የጽድቅ ፍርድህን ስማር በቅን ልብ ምስጋና አቀርብልሃለሁ፡፡ +\v 8 ሥርዐትህን እጠብቃለሁ አንተ ፈጽሞ አትተወኝ፡፡ ቤት + +\s5 +\v 9 ጐልማሳ መንገዱን እንዴት ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው፡፡ +\v 10 በሙሉ ልቤ እፈልግሃለሁ ከትእዛዞችህ እንድርቅ አትተወኝ፡፡ + +\s5 +\v 11 አንተን እንዳልበድል ቃልህን በልቤ አኖራለሁ፡፡ +\v 12 ያህዌ ሆይ፣ አንተ ቡሩክ ነህ ሥርዐትህን አስተምረኝ፡፡ + +\s5 +\v 13 አንተ የገለጥኸውን የጽድቅ ሥርዐት ሁሉ በአንደበቴ እናገራለሁ፡፡ +\v 14 ከብዙ ሀብት ይልቅ በኪዳንህ ሥርዐት ደስ ይለኛል፡፡ + +\s5 +\v 15 ድንጋጌህን አሰላስላለሁ መንገድህም ላይ አተኩራለሁ፡፡ +\v 16 በሥርዐትህ ደስ ይለኛል ቃልህንም አልዘነጋም፡፡ ጋሜል + +\s5 +\v 17 በሕይወት እንድኖርና ቃልህን እንድጠብቅ ለባርያህ መልካም አድርግ፡፡ +\v 18 ከሕግህ ድንቅ ነገር እንዳይ ዐይኖቼን ክፈት፡፡ + +\s5 +\v 19 በምድር ላይ መጻተኛ ነኝ ትእዛዞችህን ከእኔ አትሰውር፡፡ +\v 20 ጻድቅ ሥርዐትህን ለማወቅ ዘወትር ከመናፈቄ የተነሣ ነፍሴ እጅግ ዛለች፡፡ + +\s5 +\v 21 ከትእዛዞችህ የሳቱትን የተረጉሙ ዕቡያንን ገሠጽህ፡፡ +\v 22 ሥርዐቶችህን ጠብቄአለሁና ስድብና ውርደትን ከእኔ አርቅ፡፡ + +\s5 +\v 23 ገዦች ተሰብስበው በእኔ ላይ ቢዶልቱም እንኳ ባርያህ ሥርዐትህን ያሰላስላል፡፡ +\v 24 ትእዛዝህ ለእኔ ደስታዬ ነው መካሪየም ነው፡፡ ዳሌጥ + +\s5 +\v 25 ነፍሴ ከዐፈር ጋር ተጣበቀች በቃልህ ሕይወት ስጠኝ፡፡ +\v 26 ስለ መንገዴ ገልጬ ነገርሁህ አንተም መልሰህልኝ ሥርዐትህን አስተምረኝ፡፡ + +\s5 +\v 27 ድንቅ ሥራህን አሰላስል ዘንድ የድንጋጌህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፡፡ +\v 28 ሐዘን በርትቶብኛል በቃልህ አበርታኝ፡፡ + +\s5 +\v 29 የሽንገላን መንገድ ከእኔ አርቅ በቸርነትህ ሕግህን አስተምረኝ፡፡ +\v 30 የእውነትን መንገድ መርጫለሁ ሕግህንም ፊት ለፊቴ አድርጌአለሁ፡፡ + +\s5 +\v 31 ከሥርዐትህ ጋር ተጣብቄአለሁ ያህዌ ሆይ፣ ለውርደት አሳልፈህ አትስጠኝ፡፡ +\v 32 ያን እንዳደርግ አንተ ልቤን አስፍተኸዋል በትእዛዞችህ መንገድ እሮጣለሁ፡፡ ሄ + +\s5 +\v 33 ያህዌ ሆይ፣ የሥርዐትህን መንገድ አስተምረኝ እኔም እስከ መጨረሻው እጠብቀዋለሁ፡፡ +\v 34 ሕግህን እንድጠብቅ፣ በፍጹም ልቤም እንድታዘዘው ማስተዋልን ስጠኝ፡፡ + +\s5 +\v 35 በዚያ መሄድ ደስ ይለኛልና በትእዛዞችህ መንገድ ምራኝ፡፡ +\v 36 ጽድቅ ከሌለበት ጥቅም ይልቅ ልቤን ወደ ሥርዐትህ አዘንብል፡፡ + +\s5 +\v 37 ከንቱ ነገር ከማየት ዐይኖቼን መልስ በጽድቅህ ሕይወቴን አድስልኝ፡፡ +\v 38 ለእኔ ለአገልጋይህና ለሚፈሩህ ሁሉ የሰጠኸውን ተስፋ ቃል ፈጽም፡፡ + +\s5 +\v 39 ጻድቅ ፍርድህ መልካም ነውና የምፈራውን ስድብ አርቅልኝ፡፡ +\v 40 እነሆ፣ ድንጋጌህን ናፈቅሁ በጽድቅህም ሕያው አድርገኝ፡፡ ዋው + +\s5 +\v 41 ያህዌ ሆይ፣ ዘላለማዊ ፍቅርህን ስጠኝ በተስፋ ቃልህ መሠረት አድነኝ፡፡ +\v 42 በቃልህ ታምኛለሁና ለሚሰድቡኝ መልስ እሰጣለሁ፡፡ + +\s5 +\v 43 ሕግህን ተስፋ አድርጌአለሁና የእውነትን ቃል ከአፌ አታርቅ፡፡ +\v 44 ከዘላለም እስከ ዘላለም ሕግህን ዘወትር እጠብቃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 45 ሥርዐትህን እሻለሁና በፍጹም ነጻነት እኖራለሁ፡፡ +\v 46 ትእዛዞችህን በነገሥታት ፊት እናገራለሁ ይህን በማድረጌም እፍረት አይሰማኝም፡፡ + +\s5 +\v 47 አጥብቄ እወደዋለሁና በትእዛዞችህ ደስ ይለኛል፡፡ +\v 48 እጆቼን ወደምወዳቸው ትእዛዞችህ አነሣለሁ፤ ሥርዐትህንም አሰላስላለሁ፡፡ ዛይ + +\s5 +\v 49 በዚያ ተስፋ ሰጥተኸኛልና ለባርያህ የገባኸውን ቃል አስብ፡፡ +\v 50 የተስፋ ቃልህ ሕያው አድርጐኛልና ይህ በመከራዬ መጽናኛዬ ሆነ፡፡ + +\s5 +\v 51 ትዕቢተኞች እጅግ ተሳለቁብኝ እኔ ግን ከሕግህ ንቅንቅ አላልሁም፡፡ +\v 52 ያህዌ ሆይ፣ ከጥንት የነበረውን ድንጋጌህን አሰብሁ በዚህም ተጽናናሁ፡፡ + +\s5 +\v 53 ሕግህን ከናቁ ክፉዎች የተነሣ እጅግ ተቆጣሁ፡፡ +\v 54 በእንግድነቴ አገር ሥርዐትህ መዝሙሬ ሆነ፡፡ + +\s5 +\v 55 ያህዌ ሆይ፣ ስምህን በሌሊት አስባለሁ ሕግህንም እጠብቃለሁ፡፡ +\v 56 ሥርዐትህን ጠብቄአለሁና ይህ የሁልጊዜ ልምዴ ሆነ፡፡ ሔት + +\s5 +\v 57 ያህዌ ዕድል ፈንታዬ ነው ቃልህን ለመታዘዝ ቆርጫለሁ፡፡ +\v 58 በፍጹም ልቤ የአንተን ሞገስ እፈልጋለሁ እንደ ቃልህ ቸርነት አሳየኝ፡፡ + +\s5 +\v 59 መንገዴን መረመርሁ አካሄዴንም ወደ ሥርዐትህ አቀናሁ፡፡ +\v 60 ትእዛዝህን ለመጠበቅ ቸኮልሁ፤ አልዘገየሁም፡፡ + +\s5 +\v 61 የክፉዎች ገመድ ተተበተበብኝ እኔ ግን ሕግህን አልረሳሁም፡፡ +\v 62 ስለ ጻድቅ ሥርዐትህ አንተን ለማመስገን በእኩለ ሌሊት እነሣለሁ፡፡ + +\s5 +\v 63 እኔ አንተን የሚፈሩና ሥርዐትህንም የሚጠብቁ ሁሉ ባልንጀራ ነኝ፡፡ +\v 64 ያህዌ ሆይ፣ ምድር በምሕረትህ ተሞላች ሥርዐትህን አስተምረኝ፡፡ጤት + +\s5 +\v 65 ያህዌ ሆይ፣ እንደ ቃልህ ለአገልጋይህ መልካም አድርገሃል፡፡ +\v 66 በትእዛዞችህ አምናለሁና ተገቢውን ማስተዋልና ዕውቀትን አስተምረኝ፡፡ + +\s5 +\v 67 አንዳች ጉዳት ሳይደርስብኝ መንገድ ስቼ ሄድሁ አሁን ግን ቃልህን እጠብቃለሁ፡፡ +\v 68 አንተ መልካም ነህ፤ የምታደርገውም መልካም ነው እንግዲህ ሥርዐትህን አስተምረኝ፡፡ + +\s5 +\v 69 እብሪተኞች በሐሰት ስሜን አጠፉ እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዝህን እጠብቃለሁ፡፡ +\v 70 ልባቸው የሰባና የደነደነ ነው እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል፡፡ + +\s5 +\v 71 ሥርዐትህን እማር ዘንድ በመከራ ውስጥ ማለፌ መልካም ሆነልኝ፡፡ +\v 72 ከአእላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ ይሻለኛል፡፡ ዮድ + +\s5 +\v 73 እጆችህ ሠሩኝ፣ አበጃጁኝም ትእዛዞችህን እንድማር ማስተዋልን ስጠኝ፡፡ +\v 74 ቃልህን ተስፋ አድርጌአለሁና የሚፈሩህ እኔን ዐይተው ደስ ይላቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 75 ያህዌ ሆይ፣ ፍርድህ እውነተኛ እንደ ሆነ ያስጨነቅኸኝም በታማኝነት እንደ ሆነ ዐውቃለሁ፡፡ +\v 76 ለአገልጋይህ በገባኸው ቃል መሠረት ምሕረትህ መጽናኛዬ ይሁንልኝ፡፡ + +\s5 +\v 77 ሕግህ ደስታዬ ነውና በሕይወት እንድኖር ራራልኝ፡፡ +\v 78 በሐሰት የሚከሱኝ ትዕቢተኞች ይዋረዱ እኔ ግን ሥርዐትህን አሰላስላለሁ፡፡ + +\s5 +\v 79 አንተን የሚፈሩህ ሥርዐቶችህንም የሚያውቁ ወደ እኔ ይመለሱ፡፡ +\v 80 እፍረት እንዳይደርስብኝ ልቤ በሥርዐትህ ያለ ነቀፋ ይሁን፡፡ ካፍ + +\s5 +\v 81 ነፍሴ ማዳንህን እጅግ ናፈቀች ቃልህንም ተስፋ አድርጌአለሁ፡፡ +\v 82 «መቼ ታጽናናኛለህ?» እያልሁ በመጠባበቅ ዐይኖቼ ፈዘዙ፡፡ + +\s5 +\v 83 ጢስ እንደ ጠገበ የወይን ጠጅ አቁማዳ ሆኛለሁ ሥርዐትህን አልረሳሁም፡፡ +\v 84 እኔ አገልጋይህ እስከ መቼ ልቆይ? በሚያሳድዱኝ ላይ የምትፈርደው መቼ ነው? + +\s5 +\v 85 ሕግህን የማያከብሩ፤ ትዕቢተኞች ጉድጓድ ቆፈሩልኝ፡፡ +\v 86 ትእዛዞችህ ሁሉ አስተማማኝ ናቸው ሰዎች ያለ ምክንያት እያሳደዱኝ ስለሆነ ርዳኝ፡፡ + +\s5 +\v 87 ከምድር ሊያጠፉኝ ጥቂት ቀራቸው እኔ ግን ትእዛዞችህን ችላ አላልሁም፡፡ +\v 88 ሕግህን እጠብቅ ዘንድ በዘላለማዊ ፍቅርህ ሕያው አድርገኝ፡፡ ላሜድ + +\s5 +\v 89 ያህዌ ሆይ፣ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል፡፡ +\v 90 ታማኝነትህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ሁሉ ነው ምድርን መሠረትሃት እርሷም ጸንታ ትኖራለች፡፡ + +\s5 +\v 91 ነገሮች ሁሉ አገልጋዮችህ ስለሆኑ በሕግህ መሠረት እስከ ዛሬ ድረስ ጸንተው ይኖራሉ፡፡ +\v 92 ሕግህ ደስታዬ ባይሆን ኖሮ፣ በደረሰብኝ መከራ በጠፋሁ ነበር፡፡ + +\s5 +\v 93 በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ትእዛዞችህን ከቶ አልረሳሁም፡፡ +\v 94 እኔ የአንተ ነኝ፤ እባክህ አድነኝ ሕግህንም ፈልጌአለሁ፡፡ + +\s5 +\v 95 ክፉዎች ሊያጠፉኝ አድብተዋል እኔ ግን ሕግህን መረዳት እፈልጋለሁ፡፡ +\v 96 ማንኛውም ነገር የራሱ ወሰን እንዳለው አየሁ፤ ትእዛእህ ግን እጅግ ሰፊ ነው፡፡ ሜም + +\s5 +\v 97 አቤቱ ሕግህን ምንኛ ወደዱሁ ቀኑን ሙሉ አሰላስለዋለሁ፡፡ +\v 98 ዘወትር ከእኔ ጋር በመሆኑ፣ ሕግህ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ፡፡ + +\s5 +\v 99 ሥርዐቶችህን አሰላስላለሁና ከአስተማሪዎቼ ሁሉ የበለጠ ማስተዋል አለኝ፡፡ +\v 100 መመሪያህን ተከትዬ ስለምሄድ ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋይ ሆንሁ፡፡ + +\s5 +\v 101 ቃልህን እጠብቅ ዘንድ እግሬን ከክፉ መንገድ ከለከልሁ፡፡ +\v 102 አንተው ራስህ አስተምረኸኛልና ከድንጋጌህ ዘወር አላልሁም፡፡ + +\s5 +\v 103 ቃልህ ለምላሴ ምንኛ ጣፋጭ ነው ለአፌም ከማር ወለላ ይልቅ ጣዕም አለው፡፡ +\v 104 ከመመሪያህ ማስተዋል አገኘሁ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ሁሉ ጠላሁ፡፡ ኖን + +\s5 +\v 105 ቃልህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴም ብርሃን ነው፡፡ +\v 106 ጻድቅ ትእዛዞችህን ለመጠበቅ በመሐላ የገባሁትን ቃል አጸናለሁ፡፡ + +\s5 +\v 107 እጅግ ተጐድቻለሁና ያህዌ ሆይ፣ እንደ ቃል ሕያው አድርገኝ፡፡ +\v 108 ያህዌ ሆይ፣ ፈቅጄ የማቀርበውን የአፌን ምስጋና መሥዋዕት ተቀበል፡፡ + +\s5 +\v 109 ነፍሴ ዘወትር አደጋ ላይ ናት፤ እኔ ግን ሕግህን አልረሳሁም፡፡ +\v 110 ክፉዎች ወጥመድ ዘረጉብኝ እኔ ግን ከመመሪያህ ፈቀቅ አላልሁም፡፡ + +\s5 +\v 111 ሕግህ የዘላለም ውርሴ ነው የልቤም ደስታ ይኸው ነው፡፡ +\v 112 ትእዛዝህን እስከ መጨረሻው ለዘላለም ለመፈጸም ልቤን ወደዚያው አዘነበልሁ፡፡ ሳምኬት + +\s5 +\v 113 መንታ ልብ ያላቸው ወላዋዮችን ጠላሁ፤ ሕግህን ግን ወደድሁ፡፡ +\v 114 አንተ ጋሻዬና መሸሸጊያ ነህ ቃልህን በተስፋ እጠብቃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 115 የአምላኬን ትእዛዞች እጠብቅ ዘንድ እናንት ክፉ አድራጊዎች ከእኔ ራቁ +\v 116 በሕይወት እኖር ዘንድ በቃልህ ደግፈኝ ተስፋዬም መና ቀርቶ አልፈር፡፡ + +\s5 +\v 117 ያለ ስጋት እንድኖር ደግፈህ ያዘኝ ሥርዐትህንም ዘወትር አሰላስላለሁ፡፡ +\v 118 አታላዮችና የማያስተማምኑ ስለሆኑ ከሥርዐትህ የሚያፈነግጡትን ሁሉ ወዲያ አስወገድሃቸው፡፡ + +\s5 +\v 119 የምድርን ክፉዎች ሁሉ እንደ ጥራጊ አስወገድሃቸው፡፡ ስለዚህ እኔ ትእዛዞችህን ወደድሁ፡፡ +\v 120 አንተን በመፍራት ሥጋዬ ተንቀጠቀጠ ፍርድህን እፈራለሁ፡፡ ዔ + +\s5 +\v 121 ትክክልና መልም የሆነውን አድርጌአለሁና ለሚጨቁኑኝ አሳልፈህ አትስጠኝ፡፡ +\v 122 ለባርያህ ደኅንነት ዋስትና ሁን ትዕቢተኛ እንዲረግጠኝ አትፍቀድለት፡፡ + +\s5 +\v 123 ማዳንህንና የጽድቅ ቃልህን በመጠባበቅ ዐይኖቼ ደከሙ፡፡ +\v 124 ለእኔ ለአገልጋይህ ታማኝትህን አሳይ፣ ሥርዐቶችህንም አስተምረኝ፡፡ + +\s5 +\v 125 እኔ አገልጋይህ ነኝ፤ ሥርዐትህንም እንዳውቅ ማስተዋልን ስጠኝ፡፡ +\v 126 ያህዌ ሆይ፣ ሕግህ እየተጣሰ ነውና ጊዜው አንተ የምትሠራበት ነው፡፡ + +\s5 +\v 127 ከወርቅ፣ ከንጹሕም ወርቅ ይልቅ በእውነት ትእዛዞችህን ወደድሁ፡፡ +\v 128 ስለዚህ መመሪያዎችን በጥንቃቄ ጠበቅሁ የሐሰትንም መንገድ ጠላሁ፡፡ ፌ + +\s5 +\v 129 ሥርዐቶችህ አስደናቂ ናቸው እኔም በሙሉ ልቤ እታዘዛቸዋለሁ፡፡ +\v 130 የቃልህ ፍቺ ያበራል አላዋቂዎችን አስተዋይ ያደርጋል፡፡ + +\s5 +\v 131 ትእዛዝህን በመናፈቄ አፌን ከፊትሁ አለከለክሁም፡፡ +\v 132 ስምህን ለሚፈሩ ዘወትር እንደምታደርገው ወደ እኔ ተመልሰህ ምሕረት አድርግልኝ፡፡ + +\s5 +\v 133 እንደ ቃልህ አካሄዴን ቀና አድርግልኝ ኃጢአት እንዲሠለጥንብኝም አትፍቀድ፡፡ +\v 134 ትእዛዝህን መጠበቅ እንድችል ከሰዎች ጥቃት አድነኝ፡፡ + +\s5 +\v 135 ፊትህ በባርያህ ላይ ያብራ ሥርዐትህንም አስተምረኝ፡፡ +\v 136 ሰዎች ሕግህን ስለ ጣሱ እንባዬ እንደ ወራጅ ውሃ ፈሰሰ፡፡ + +\s5 +\v 137 ያህዌ ሆይ፣ አንተ ጻድቅ ነህ ፍርድህም ትክክል ነው፡፡ +\v 138 ሕግህ በፍጹም እውነትና ትክክል ነው፡፡ + +\s5 +\v 139 ጠላቶቼ ቃልህን መዘንጋታቸው በጣም አበሳጨኝ፡፡ +\v 140 ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው ባርያህም ወደደው፡፡ + +\s5 +\v 141 እኔ የማልጠቅምና የተናቅሁ ብሆን እንኳ፣ መመሪያህን አልዘነጋሁም፡፡ +\v 142 ጽድቅህ ለዘላለም ትክክል ነው ሕግህም የታመነ ነው፡፡ + +\s5 +\v 143 መከራና ስቃይ ቢደርስብኝ እንኳ አሁንም ትእዛዝህ ደስታዬ ነው፡፡ +\v 144 ሥርዐትህ ለዘላለም ጻድቅ ነው በሕይወት መኖር እንድችል ማስተዋል ስጠኝ፡፡ ቆፍ + +\s5 +\v 145 ያህዌ ሆይ፣ በፍጹም ልቤ እጮኻለሁና መልስልኝ፤ ሥርዐትህንም እጠብቃለሁ፡፡ +\v 146 ወደ አንተ እጣራለሁና አድነኝ ሥርዐትህንም እጠብቃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 147 ጐሕ ከመቅደዱ በፊት ርዳታህን በመፈለግ ወደ አንተ እጮኻለሁ፤ ቃልህንም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ +\v 148 ቃልህን አሰላስል ዘንድ ሌሊቱን ሙሉ ዐይኔ ሳይከደን ያድራል፡፡ + +\s5 +\v 149 እንደ ቸርነትህ መጠን ድምፄን ስማ ያህዌ ሆይ፣ በትእዛዝህ መሠረት ሕይወቴን ጠብቅ፡፡ +\v 150 የሚያሳድዱኝ ወደ እኔ ቀርበዋል ከሕግህ ግን ርቀዋል፡፡ + +\s5 +\v 151 ያህዌ ሆይ፣ አንተ ቅርብ ነህ መመሪያዎችህም የታመኑ ናቸው፡፡ +\v 152 ለዘላለም እንደ መሠረትሃቸው ጥንት ከሥርዐትህ ተምሬአለሁ፡፡ ሬስ + +\s5 +\v 153 ሕግህን አልረሳሁምና መከራዬን ተመልከት አድነኝም፡፡ +\v 154 ተሟገትልኝ አድነኝም እንደ ተስፋ ቃልህም ጠብቀኝ፡፡ + +\s5 +\v 155 ሥርዐትህን ስለማይፈልጉ ድነት ከክፉዎች የራቀ ነው፡፡ +\v 156 ያህዌ ሆይ፣ ርኅራኄህ ታላቅ ነው፤ እንደ ሁልጊዜው በሕይወት ጠብቀኝ፡፡ + +\s5 +\v 157 አሳዳጆቼና ጠላቶቼ በዝተዋል፤ እኔ ግን ከሥርዐትህ ፈቀቅ አላልሁም፡፡ +\v 158 ቃህን አልጠበቁም ከዳተኞችን ዐይቼ ተጸየፍኃቸው፡፡ + +\s5 +\v 159 መመሪያህን እንዴት እንደምወድ እይ፤ ያህዌ ሆይ፣ እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ፡፡ +\v 160 የቃልህ ሥረ መሠረት እውነት ነው ጻድቅ የሆነው ሕግህም ዘላለማዊ ነው፡፡ ሳን + +\s5 +\v 161 መመሪያህን እንዴት እንደምወድ እይ፤ ያህዌ ሆይ፣ እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ፡፡ +\v 162 የቃልህ ሥረ መሠረት እውነት ነው ጻድቅ የሆነው ሕግህም ዘላለማዊ ነው፡፡ ሳን + +\s5 +\v 163 ሐሰትን እጠላለሁ፤ እጸየፋለሁ ሕግህን ግን ወደድሁ፡፡ +\v 164 ጻድቅ ስለሆነው ሕግህ በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 165 ሕግህን ለሚወዱ ብዙ ሰላም አላቸው ዕንቅፋትም የለባቸውም፡፡ +\v 166 ያህዌ ሆይ፣ ማዳንህን እጠብቃለሁ ትእዛዞችህንም እፈጽማለሁ፡፡ + +\s5 +\v 167 ትእዛዝህን እጠብቃለሁ በሙሉ ልቤም እወዳቸዋለሁ፡፡ +\v 168 ትእዛዝህንና ሕግህን አከብራለሁ አንተ የምሠራውን ሁሉ ታውቃለህ፡፡ ታው + +\s5 +\v 169 ያህዌ ሆይ፣ እንድትረዳኝ ወደ አንተ ስጮኽ ስማኝ እንደ ቃልህም ማስተዋልን ስጠኝ፡፡ +\v 170 ልመናዬ ወደ አንተ ይድረስ በተስፋ ቃልህም መሠረት አድነኝ፡፡ + +\s5 +\v 171 ሥርዐትህን አስተምረኸኛልና ከንፈሮቼ ምስጋናን አፈለቁ፡፡ +\v 172 ትእዛዞችህ ሁሉ ትክክል ስለሆኑ ስለ ቃልህ እዘምራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 173 መመሪያህን መርጫለሁና እጅህ እኔን ለመርዳት ዝግጁ ይሁን፡፡ +\v 174 ያህዌ ሆይ፣ ማዳንህን ናፈቅሁ ሕግህም ደስታዬ ነው፡፡ + +\s5 +\v 175 አመሰግንህ ዘንድ በሕይወት ልኑር ሕግህም ይርዳኝ፡፡ +\v 176 እንደ ጠፋ በግ ተቅበዘበዝሁ ትእዛዞችህን አልረሳሁምና ባርያህን ፈልገው፡፡ + +\s5 +\c 120 +\p +\v 1 በጨነቀኝ ጊዜ ወደ ያህዌ ተጣራሁ እርሱም መለሰልኝ፡፡ +\v 2 ከሐሰተኛ ከንፈር፣ ከአታላይ ምላስም አድነኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 እናንት አታላዮች እግዚአብሔር እንዴት ይቅጣችሁ፣ ምንስ ቢከፍላችሁ ይሻላል? +\v 4 በተሳለ የጦረኛ ቀስት በግራር ከሰል ፍም ይቀጣችኃል፡፡ + +\s5 +\v 5 የምኖረው በሜሼክ ስለ ሆነ የነበርኩትም በቄዳር ድንኳኖች መካከል ስለ ነበር ወዮልኝ፡፡ +\v 6 ሰላምን ከሚጠሉ ጋር በጣም ረጅም ጊዜ ኖርሁ፡፡ +\v 7 እኔ ሰላም ፈላጊ ነኝ፡፡ በተናገርሁ ጊዜ ግን እነርሱ ጠብ ይፈልጋሉ፡፡ + +\s5 +\c 121 +\p +\v 1 ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ ረዳቴ ከወዴት ይመጣል? +\v 2 ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ ከያህዌ ዘንድ ይመጣል፡፡ + +\s5 +\v 3 እግርህ እንዲንሸራተት አይፈቅድም አንተን የሚጠብቅህም አይተኛም፡፡ +\v 4 እነሆ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፉምም፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ ይጠብቅሃል፤ ያህዌ በቀኝህ በኩል ይከልልሃል፡፡ +\v 6 ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም በሌሊት አይጐዳህም፡፡ + +\s5 +\v 7 ያህዌ ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል እርሱ ሕይወትህንም ይጠብቃል፡፡ +\v 8 ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም ያህዌ በምታደርገው ሁሉ ይጠብቅሃል፡፡ + +\s5 +\c 122 +\p +\v 1 «ወደ ያህዌ ቤት እንሂድ» ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ፡፡ +\v 2 ኢየሩሳሌም ሆይ፣ እግሮቻችን በደጆችሽ ውስጥ ቆመዋል፡፡ +\v 3 ኢየሩሳሌም በጥንቃቄ የተገነባች ከተማ ናት! + +\s5 +\v 4 ለእስራኤል ምስክር ይሆን ዘንድ ነገዶች፣ የያህዌ ነገዶች ወደዚያ ይወጣሉ፡፡ +\v 5 በዚያም የፍርድ ዙፋኖች የዳዊት ቤት ዙፋኖች ተዘርግተዋል፡፡ + +\s5 +\v 6 ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፡፡ «የሚወዱሽ ሰላም ይሁንላቸው፡፡ +\v 7 በቅጥሮችሽ ውስጥ ሰላም ይሁን በምሽጐችሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን፡፡» + +\s5 +\v 8 ስለ ወንድሞቼና ስለ ወዳጆቼ ኢየሩሳሌምን፣ «ሰላም ከአንቺ ጋር ይሁን» እላታለሁ፡፡ +\v 9 ስለ አምላካችን ያህዌ ቤት መልካም እንዲሆንልሽ እሻለሁ፡፡ + +\s5 +\c 123 +\p +\v 1 በሰማያት የምትኖር ሆይ፣ ዐይኖቼን ወደ አንተ እነሣለሁ፡፡ +\v 2 የባርያዎች ዐይን ወደ ጌታቸው እጅ እንደሚመለከት የባርያዪቱም ዐይን ወደ እመቤቷ እጅ እንደሚመለከት ምሕረት እስኪያደርግልን ድረስ የእኛም ዐይን ወደ አምላካችን ወደ ያህዌ ይመለከታሉ፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ እጅግ ተዋርደናልና ማረን፣ አቤቱ ማረን፡፡ +\v 4 በትዕቢተኞች ብዙ ተዋርደናል፣ በትምክሕተኞችም እጅግ ተንቀናል፡፡ + +\s5 +\c 124 +\p +\v 1 «ያህዌ ከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ» ይበል እስራኤል፡፡ +\v 2 ሰዎች በእኛ ላይ በተነሡ ጊዜ ያህዌ ከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ +\v 3 ቁጣቸው በእኛ ላይ በነደደ ጊዜ በሕይወት እያለን በዋጡን ነበር፡፡ + +\s5 +\v 4 ጐርፍ በወሰደን፣ ውሃም በሸፈነን ነበር፡፡ +\v 5 ብርቱ ማዕበልም ባሰጠመን ነበር + +\s5 +\v 6 በጥርሳቸው እንዲቦጫጭቁን ያልፈቀደ ያህዌ ይባረክ +\v 7 ነፍሳችን እንደ ወፍ ከአዳኝ ወጥመድ አመለጠች ወጥመዱ ተሰበረ እኛም አመለጥን፡፡ + +\s5 +\v 8 ሰማይና ምድርን የሠራ ያህዌ ረዳታችን ነው፡፡ + +\s5 +\c 125 +\p +\v 1 በያህዌ የሚተማመኑ ሳትናወጥ ለዘላለም እንደምትኖር የጽዮን ተራራ ናቸው፡፡ +\v 2 ተራሮች ኢየሩሳሌምን እንደ ከበቧት ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ያህዌም በሕዝቡ ዙሪያ ነው፡፡ +\v 3 ጻድቁ ክፉ እንዳያደርግ የዐመፃ በትረ መንግሥት የጻድቃንን ምድር አይግዛ፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌ ሆይ፣ መልካም ለሆኑ፣ ልባቸውም ቀና ለሆኑት መልካም አድርግ፡፡ +\v 5 ወደ ጠማማ መንገዳቸው የሚመለሱትን ግን ያህዌ ከክፉ አድራጊዎች ጋር ያጠፋቸዋል፡፡ ሰላም በእስራኤል ላይ ይሁን፡፡ + +\s5 +\c 126 +\p +\v 1 ያህዌ የጽዮንን ምርኮ በመለሰ ጊዜ ሕልም እንጂ፣ እውን አልመሰለንም፡፡ + +\s5 +\v 2 በዚያ ጊዜ አፋችን በሣቅ፣ አንደበታችንም በዝማሬ ተሞላ፡፡ በዚያ ጊዜ በሕዝቦች መካከል፣ «ያህዌ ታላቅ ነገር አደረገላቸው» ተባለ፡፡ +\v 3 ያህዌ ታላቅ ነገር አደረገልን እኛም እጅግ ደስ አለን፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌ ሆይ፣ በኔጌቭ እንዳሉ ምንጮች ምርኮአችን መልስ፡፡ +\v 5 በእንባ የሚዘሩ በእልልታ ይዘራሉ +\v 6 ዘሩን ተሸክመው እያለቀሱ የተሰማሩ ነዶአቸውን ተሸክመው እልል እያሉ ይመለሳሉ፡፡ + +\s5 +\c 127 +\p +\v 1 ያህዌ ቤትን ካልሠራ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ ያህዌ ከተማን ካልጠበቀ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል፡፡ +\v 2 የዕለት ጉርስ ለማግኘት በመጣር ማለዳ መነሣት፣ አምሽቶም መግባት ከንቱ ነው፡፡ ያህዌ ለወዳጆቹ ተኝተው እያለ የሚያስፈልጋቸውን ይሰጣቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 3 እነሆ ልጆች የያህዌ ስጦታ ናቸው የማሕፀንም ፍሬ የእርሱ ችሮታ ነው፡፡ +\v 4 በወጣትነት የተገኙ ልጆች በጦረኛ እጅ እንዳሉ ፍላጾች ናቸው +\v 5 ኮረጆዎቹን በእነዚህ የሞላ ሰው የተባረከ ነው፡፡ ከጠላቶቹ ጋር በሚሟገትበት ጊዜ አፍሮ አይገባም፡፡ + +\s5 +\c 128 +\p +\v 1 ያህዌን የሚፈሩ ሁሉ በመንገዶቹም የሚሄዱ የተባረኩ ናቸው፡፡ +\v 2 በእጆችህ ሥራ ደስ ይልሃል ትባረካለህ፤ ይሳካልሃልም፡፡ + +\s5 +\v 3 በቤትህ ውስጥ ሚስትህ እንደሚያፈራ ወይን ትሆናለች ልጆችህም በማእድህ ዙሪያ እንደ ወይራ ተክል ይሆናሉ፡ +\v 4 አዎን፣ ያህዌን የሚፈራ እንዲህ ይባረካል፡፡ +\v 5 ያህዌ ከጽዮን ይባርክህ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ የኢየሩሳሌምን ብልጽግና ያሳይህ፡፡ +\v 6 የልጅ ልጆችን ለማየት ያብቃህ እስራኤል ላይ ሰላም ይሁን፡፡ + +\s5 +\c 129 +\p +\v 1 «ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ» ይበል እስራኤል፡፡ +\v 2 በእርግጥ፣ ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ ይሁን እንጂ አላሸነፉኝም፡፡ +\v 3 አራሾች ጀርባዬን አረሱት ትልማቸውንም አስረዘሙት፡፡ + +\s5 +\v 4 እግዚአብሔር ጻድቅ ነው የክፉዎችን ገመድ በጣጥሶ ጣለ፡፡ +\v 5 ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ ይፈሩ ወደ ኃላቸውም ይመለሱ፡፡ + +\s5 +\v 6 ገና ከመብቀሉ እንደሚደርቅ ቤት ጣር ላይ እንዳለ ሣር ይሁኑ፡፡ +\v 7 ደግሞ ለዐጫጁ እጁን ለነዶ ሰብሳቢ እቅፉን እንደማይሞላ ነዶ ይሁኑ፡፡ +\v 8 መንገድ ዐላፊዎችም፣ «የያህዌ በረከት እናንተ ላይ ይሁን፤ በያህዌ ስም ባረክናችሁ አይበሉ፡፡» + +\s5 +\c 130 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ከጥልቅ ወደ አንተ እጮኻለሁ፡፡ +\v 2 ጌታ ሆይ፣ ምሕረትን ፈልጌ ስጮኽ ድምፄን ስማ ጆሮህንም ወደ እኔ አዘንብል፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ አንተ ኃጢአትን ብትከታተል ኖሮ ማን መቆም ይችል ነበር፡፡ +\v 4 ነገር ግን በአንተ ዘንድ ይቅርታ አለ ስለዚህ ልትፈራ ይገባሃል፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌን በትዕግሥት እጠብቃለሁ በቃሉም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ +\v 6 ዘብ አዳሪ ንጋትን እንደሚጠብቅ እኔም ጌታን በትዕግሥት እጠብቃለሁ፡፡ + +\s5 +\v 7 ያህዌ መሓሪ ነው፤ ይቅር ለማለትም ፈቃደኛ ነው እስራኤል ሆይ፣ ያህዌን ተስፋ አድርግ፡፡ +\v 8 እርሱ እስራኤልን ከኃጢአቱ ሁሉ ያድነዋል፡፡ + +\s5 +\c 131 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ልቤ አልታበየም ዐይኔም ከፍ ከፍ አላለም፡፡ ለራሴም ታላላቅ ነገሮችን ተስፋ አላደረግሁም ከእኔ በላይ በሆነ ነገርም አልተጨነቅሁም፡፡ + +\s5 +\v 2 ነገር ግን ነፍሴን ጸጥ፣ ዝም አሰኘኃት ነፍሴ ጡት እንዳስተውት ሕፃን በውስጤ ጸጥ አለች፡፡ +\v 3 እስራኤል ሆይ አሁንና ለዘላለም ያህዌ ተስፋ አድርግ፡፡ + +\s5 +\c 132 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ዳዊትን፣ የተቀበለውንም መከራ ሁሉ አስብ፡፡ +\v 2 እርሱ ለያህዌ ማለ፣ ለያዕቆብም ኃያል አምላክ ቃል ገባ፤ + +\s5 +\v 3 እንዲህም አለ፣ «ወደ ቤቴ አልገባም፤ አልጋዬ ላይ አልወጣም +\v 4 ለዐይኖቼ እንቅልፍን ለሽፋሽፍቶቼም ዕረፍትን አልሰጥም፤ +\v 5 ለያህዌ ስፍራን፣ ለያዕቆብ ኃያል ማደሪያን እስካገኝ ድረስ፡፡ + +\s5 +\v 6 እነሆ፣ በኤፍራታ ሰማነው፣ በይዓሪም አገኘነው፡፡ +\v 7 ወደ ማደሪያው እንግባ እግሮቹ በሚቆሙበት ስፍራ እንስገድ፡፡ +\v 8 ያህዌ ሆይ ተነሥ አንተና የኃይልህ ታቦታ ወደ ማደሪያህ ስፍራ ሂዱ፡፡ + +\s5 +\v 9 ካህናትህ ጽድቅን ይልበሱ ታማኞችህ እልል ይበሉ፡፡ +\v 10 ስለ ባርያህ ስለ ዳዊት ስትል የተቀባኸውን ንጉሥ አትተወው፡፡ + +\s5 +\v 11 ያህዌ ለዳዊት በእውነት ማለ በማይታጠፍ መሐላ እንዲህ አለ «ከልጆችህ አንዱን ዙፋንህ ላይ አስቀምጣለሁ +\v 12 ልጆችህ ኪዳኔን፣ የማስተምራቸውንም ሕጌን ቢጠብቁ፣ ልጆቻቸው ለዘላለም በዙፋንህ ላይ ይቀመጣሉ፡፡» + +\s5 +\v 13 ያህዌ ጽዮንን መርጧልና ማደሪያው እንድትሆን ወዶአልና፡፡ +\v 14 «ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት ፈልጌአታለሁና በእርሷ እኖራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 15 እጅግ አትረፍርፌ እባርካታለሁ ድኾቿን እንጀራ አጠግባለሁ፡፡ +\v 16 ካህናቶቿን ማዳንን አለብሳቸዋለሁ ታማኞቿም እልል ይላሉ፡፡ + +\s5 +\v 17 በዚያ ለዳዊት ቀንድ አበቅላለሁ ለቀባሁትም ሰው መብራት አዘጋጃለሁ፡፡ +\v 18 ጠላቶቹን እፍረት አከናንባቸዋለሁ እርሱ ላይ ግን አክሊሉ ያበራል፡፡ + +\s5 +\c 133 +\p +\v 1 ወንድሞች ተስማምተው በአንድነት ቢኖሩ እንዴት መልካም ነው! ምንኛስ አስደሳች ነው፡፡ + +\s5 +\v 2 በአሮን ራስና ጢም ላይ እንደሚፈስስ እስከ ልብሱን ዐንገት ጌጥ ድረስ እንደሚወርድ ውድ ሽቱ ነው፡፡ +\v 3 ደግሞም በጽዮን ተራራ ላይ እንደሚወርድ እንደ አርሞንዔም ጠል ነው፡፡ ያህዌ በዚያ በረከቱን አዞአልና ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዞአል፡፡ + +\s5 +\c 134 +\p +\v 1 እናንት በሌሊት ቆማችሁ በያህዌ ቤት የምታገለግሉ የያህዌ ባርያዎች ሁላችሁ፣ ያህዌን አመስግኑ፡፡ +\v 2 ወደ መቅደሱ እጃችሁን አንሡና ያህዌን ባርኩ፡፡ + +\s5 +\v 3 ሰማይና ምድርን የሠራ ያህዌ ከጽዮን ይባርካችሁ፡፡ + +\s5 +\c 135 +\p +\v 1 ያህዌን አመስግኑ የያህዌን ስም ወድሱ፤ እናንት የያህዌ አገልጋዮች አመስግኑት፡፡ +\v 2 በያህዌ ቤት በአምላካችንም ቤት አደባባይ የምትቆሙ አመስግኑት፡፡ + +\s5 +\v 3 መልካም ነውና ያህዌን አመስግኑ ደስ የሚያሰኝ ነውና ለስሙ ዘምሩ፡፡ +\v 4 ያህዌ ያዕቆብን ለራሱ፣ እስራኤልም ርስቱ እንዲሆን መርጦአልና፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ ታላቅ መሆኑን፣ ጌታችንም ከአማልክት በላይ መሆን ዐውቃለሁ፡፡ +\v 6 በሰማይም ሆነ በምድር በባሕርና በጥልቅ ውቅያኖስ ያህዌ የወደደውን ያደርጋል፡፡ + +\s5 +\v 7 እርሱ ደመናትን ከሩቅ ቦታ ያመጣል ከዝናብ ጋር መብረቅ እንዲኖር ያደርጋል፡፡ ነፋሳትንም ከማከማቻው ያወጣል፡፡ + +\s5 +\v 8 ከሰው ጀምሮ እስከ እንስሳ የግብፃውያንን በኩር ገደለ፡፡ +\v 9 ግብፅ ሆይ፣ በፈርዖንና በአገልጋዮቹ ሁሉ ላይ፣ በመካከልሽም ምልክቶችንና ድንቆችን አደረገ፡፡ + +\s5 +\v 10 ብዙ ሕዝቦች መታ ኃያላን ነገሥታት ገደለ፡፡ +\v 11 የአሞራውያን ንጉሥ ሴዎንን የባሰን ንጉሥ ዐግን የከነዓንን ነገሥታት ሁሉ ገደለ፡፡ + +\s5 +\v 12 ምድራቸውንም ለሕዝቡ ለእስራኤል ርስት አድርጐ ሰጠ፡፡ +\v 13 ያህዌ ሆይ፣ ስምህ ዘላለማዊ ነው መታሰቢያህም ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል፡፡ + +\s5 +\v 14 ያህዌ ለሕዝቡ ይፈርዳልና ለአገልጋዮቹም ይራራልና፡፡ +\v 15 የአሕዛብ ጣዖቶች ከብርና ከወርቅ በሰው እጅ የተሠሩ ናቸው +\v 16 አፍ አላቸው አይናገሩም ዐይን አላቸው አያዩም፡፡ +\v 17 ጆሮ አላቸው አይሰሙም፤ በአፋቸውም እስትንፋስ የለም፡፡ +\v 18 የሚሠሩዋቸውና የሚታመኑባቸው ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ፡፡ + +\s5 +\v 19 የእስራኤል ልጆች ሆይ፣ ያህዌን ባርኩ የአሮን ልጆች ሆይ፣ ያህዌን ባርኩ፡፡ +\v 20 የሌዊ ልጆች ሆይ፣ ያህዌን ባርኩ ያህዌን የምትፈሩ ሆይ፣ ያህዌን ባርኩ፡፡ +\v 21 በኢየሩሳሌም የሚኖር ያህዌ ከጽዮን ይባረክ ያህዌን አመስግኑ፡፡ + +\s5 +\c 136 +\p +\v 1 ቸር ነውና ያህዌን አመስግኑ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 2 የአማልክትን አምላክ አመስግኑ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 3 የጌቶችን ጌታ አመስግኑ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 4 ብቻውን ታላላቅ ተአምራት ያደረገውን አመስግኑ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 5 በጥበብ ሰማያትን የሠራ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 6 ምድርን ውሃ ላይ የዘረጋ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 7 ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 8 ፀሐይ በቀን እንዲገዛ ያደረገ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 9 ጨረቃና ከዋክብት ሌሊት እንዲገዙ ያደረገ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 10 የግብፅን በኩር የገደለ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 11 እስራኤልን ከመካከላቸው ያወጣ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 12 በብርቱ እጅ፣ በተዘረጋችም ክንድ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 13 ቀይ ባሕርን የከፈለውን አመስግኑ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 14 እስራኤልን በመካከሉ ያሳለፈ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 15 ፈርዖንና ሰራዊቱን ቀይ ባሕር ውስጥ ያሰጠመ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 16 ሕዝቡን በምድረ በዳ የመራውን አመስግኑ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 17 ታላላቅ ነገሥታትን የገደለውን ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 18 ኃያላን ነገሥታትን የገደለ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 19 የአሞራውያን ንጉሥ ሴዎንን ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 20 የባሳንን ንጉሥ ዐግን የገደለ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 21 ምድራቸውን ርስት አድርጐ የሰጠ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 22 ለባርያው ለእስራኤል ርስት አድርጐ የሰጠ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 23 በውርደታች ያሰበን፣ የረዳንም ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\v 24 በጠላቶቻችን ላይ ድል የሰጠን ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 25 ለፍጡር ሁሉ ምግብ የሚሰጥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ +\v 26 የሰማይን አምላክ አመስግኑ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፡፡ + +\s5 +\c 137 +\p +\v 1 በባቢሎን ወንዞች አጠገብ ተቀምጠን ጽዮንን ባሰብናት ጊዜ አለቀስን፡፡ +\v 2 እዚያ በገናዎቻችንን በአኻያ ዛፎች ላይ ሰቀልን፡፡ + +\s5 +\v 3 የማረኩን ሰዎች እንድንዘምርላቸው ጠየቁን ሲያፌዙብን የነበሩት የደስታ ዜማ ፈለጉብን፣ «እስቲ ከጽዮን መዝሙሮች አንዱን ዘምሩልን» አሉን፡፡ +\v 4 የያህዌን መዝሙር እንዴት ብለን በባዕድ ምድር እንዘምራለን? + +\s5 +\v 5 ኢየሩሳሌም ሆይ፣ ብረሳሽ ቀኝ እኔ ይክዳኝ፡፡ +\v 6 አንቺን ሳላስታውስ፣ ደስ ከሚያሰኘኝ ነገር ሁሉ በላይ ሳላደርግሽ ብቀር ምላሴ ከትናጋዬ ትጣበቅ፡፡ + +\s5 +\v 7 ያህዌ ሆይ፣ ኢየሩሳሌም በወደቀችበት ቀን ኤዶማውያን ያደረጉትን አስብ፡፡ እነርሱ፣ «አፍርሷት፣ ጨርሳችሁ አፍርሷት!» አሉ፡፡ + +\s5 +\v 8 የባቢሎን ልጅ ሆይ፣ እኛ ላይ ስላደረግሺው ድርጊት ብዙም ሳይቆይ፣ የእጅሽን የሚሰጥሽ የተባረከ ነው +\v 9 ሕፃናቶችሽን ዐለት ላይ የሚፈጠፍጥ እርሱ የተመሰገነ ነው፡፡ + +\s5 +\c 138 +\p +\v 1 በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ በአማልክትም ፊት በመዝሙር እወድስሃለሁ፡፡ +\v 2 ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ ስለ ምሕረትህና ስለ ታማኝነትህ ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡ ቃልህንና ስምህን ከሁሉ በላይ ከፍ አደረግህ፡፡ + +\s5 +\v 3 በጠራሁህ ቀን መለስህልኝ ነፍሴን በማጽናናት አደፋፈርሃት፡፡ +\v 4 ያህዌ ሆይ፣ የአፍህን ቃል ሲሰሙ የምድር ነገሥታት ሁሉ ያመሰግኑሃል፡፡ + +\s5 +\v 5 የያህዌ ክብር ታላቅ ነውና ስለ ያህዌ ሥራ ይዘምራሉ፡፡ +\v 6 ያህዌ እጅግ ከፍ ያለ ቢሆንም፣ ዝቅ ያሉትንም ይመለከታል ትዕቢተኞችን ግን ገና ከሩቅ ያውቃቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 7 በአደጋ መካከል ብሄድ እንኳ አንተ ሕይወቴን ትጠብቃለህ፡፡ እጅህን ዘርግተህ ከጠላቶቼ ቁጣ ታወጣኛለህ በቀኝ እጅህም ታድነኛለህ፡፡ +\v 8 ያህዌ እስከ መጨረሻ ከእኔ ጋር ነህ ያህዌ ሆይ፣ ምሕረትህ ለዘላለም ነው፡፡ የእጅህን ሥራ ቸል አትበል፡፡ + +\s5 +\c 139 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ መረመርኸኝ፤ ደግሞም ዐወቅኸኝ፡፡ +\v 2 አንተ መቀመጤንና መነሣቴን ታውቃለህ የልቤንም ሐሳብ ገና ከሩቅ ትረዳለህ፡፡ + +\s5 +\v 3 መሄድ መተኛቴን በሚገባ ታውቃለህ መንገዶቼንም ሁሉ ዐውቀሃቸዋል +\v 4 ገና ቃል ከአንደበቴ ሳይወጣ ያህዌ ሆይ፣ ፈጽመህ ታውቃለህ፡፡ +\v 5 አንተ ከኋላም ከፊትም ዙሪያዬን ከለልኸኝ እጅህንም በላዬ አደረግህ፡፡ +\v 6 እንዲህ ያለው ዕውቀት እጅግ ጥልቅ ነው ከእኔም ማስተዋል በላይ ነው፡፡ + +\s5 +\v 7 ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ፡፡ +\v 8 ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ አለህ መኝታዬን በሲኦል ባደርግ በዚያ ትገኛለህ፡፡ + +\s5 +\v 9 በንጋት ክንፍ ተነሥቼ ብበር እስከ ባሕሩ መጨረሻ ብሄድ +\v 10 በዚያም ቢሆን እጅህ ትመራኛለች ቀኝ እጅህም ትይዘኛለች፡፡ + +\s5 +\v 11 ደግሞም፣ «ጨለማው በእርግጥ ይሸፍነኛል በዙሪያዬ ያለውም ብርሃን ሌሊት ይሆናል» ብል +\v 12 ጨለማ እንኳ ለአንተ አይጨልምም ሌሊቱም እንደ ቀን ያበራል በአንተ ጨለማም ሆነ ብርሃን አንድ ናቸው፡፡ + +\s5 +\v 13 አንተ የውስጥ ሰውነቴን ፈጥረሃል በእናቴ ማሕፀን ውስጥ አበጃጅተህ ሠራኸኝ፡፡ +\v 14 ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ ሥራህ እጅግ ድንቅ ነው ነፍሴም ይህን በሚገባ ታውቃለች፡፡ + +\s5 +\v 15 እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ ዐጥንቶቼ ከአንተ አልተደበቁም፡፡ በምድር ጥልቅ ውስጥ በጥበብ በተሠራሁ ጊዜ +\v 16 በእናቴ ማሕፀን እያለሁ አየኸኝ፡፡ ገና አንዳቸውም ወደ መኖር ሳይመጡ ለእኔ የተወሰኑልኝ ዘመኖች በመጽሐፍህ ተጻፉ፡፡ + +\s5 +\v 17 አምላኬ ሆይ፣ ለእኔ ያለህ ሐሳብ እንዴት ግሩም ነው! ቁጥሩስ ምንኛ የበዛ ነው! +\v 18 ልቁጠራቸው ብል ከአሸዋ ቁጥር ይበልጣሉ ተኛሁ ነቃሁም፤ ያም ሆኖ ግን አሁንም ከአንተው ጋር ነኝ፡፡ + +\s5 +\v 19 አምላክ ሆይ፣ ክፉዎችን ብትገድላቸው ምናለበት! ደም የጠማችሁ ዐመፀኞች ከእኔ ራቁ፡፡ +\v 20 እነርሱ በአንተም ላይ ክፉ ይናገራሉ በጠላትነትም ስምህን በክፉ ያጠፋሉ፡፡ + +\s5 +\v 21 ያህዌ ሆይ፣ የሚጠሉህን አልጠላሁምን? በአንተ ላይ የሚነሡትንስ አልተጸየፍሁምን? +\v 22 በፍጹም ጥላቻ ጠልቻቸዋለሁ እነርሱም ባላጋራዎቼ ሆነዋል፡፡ + +\s5 +\v 23 እግዚአብሔር ሆይ፣ መርምረኝ ልቤንም ዕወቅ ፈትነኝ ሐሳቤንም ዕወቅ፡፡ +\v 24 በእኔ ውስጥ የዐመፅ መንገድ ቢኖር እይ በዘላለምም መንገድ ምራኝ፡፡ + +\s5 +\c 140 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ከክፉ ሰዎች አድነኝ ከዐመፀኞችም ጠብቀኝ፡፡ +\v 2 እነርሱ በልባቸው ክፉ ነገር ያውጠነጥናሉ በየዕለቱም ጦርነት ይጭራሉ፡፡ +\v 3 ምላሳቸው እንደ እባብ ይነድፋል የእፉኝትም መርዝ በከንፈራቸው አለ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 4 ያህዌ ሆይ፣ ከክፉዎች እጅ ጠብቀኝ መትተው ሊጥሉኝ ከሚፈልጉ ዐመፀኛ ሰዎች አድነኝ፡፡ +\v 5 ትዕቢተኞች በስውር ወጥመድ ዘርግተውብኛል የመረባቸውን ገመድ ዘረጉብኝ በመንገዴም አሽክላ አኖሩ፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 6 እኔም ያህዌን፣ «አንተ አምላኬ ነህ እንድትምረኝ የማቀርበውን ጩኸት ስማ» እለዋለሁ፡፡ +\v 7 ያህዌ ሆይ፣ እኔን ለማዳን ብርቱ ነህ በጦርነት ቀን ራሴን ከለልህ፡፡ +\v 8 ያህዌ ሆይ፣ የክፉዎች ምኞት አይሳካ ሤራቸውም አይከናወን፡፡ + +\s5 +\v 9 ዙሪያዬን የከበቡኝ ራሳቸውን ቀና ቀና አደረጉ የገዛ ከንፈራቸው ሸፍጥ ይዋጣቸው፡፡ +\v 10 የእሳት ፍም በላያቸው ይውረድ እሳት ውስጥ ጣላቸው ዳግመኛም እንዳይነሡ ማጥ ወዳለበት ጉድጓድ ይውደቁ፡፡ +\v 11 ምላሰኛ በምድሪቱ ጸንቶ አይኑር ዐመፀኛውን ክፋት አሳድዶ ያጥፋውቨ + +\s5 +\v 12 ያህዌ ለተበደሉ እንደሚፈርድ ለችግረኛውም ፍትሕ እንደሚሰጥ ዐውቃለሁ፡፡ +\v 13 ጻድቃን በእውነት ስምህን ያመሰግናሉ ቅኖችም በፊትህ ይኖራሉ፡፡ + +\s5 +\c 141 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ወደ አንተ እጣራለሁ ፈጥነህ ድረስልኝ ወደ አንተ ስጣራ ድምፄን ስማ +\v 2 ጸሎቴ በፊትህ እንደ ዕጣን ይሁንልኝ ወደ አንተ ያነሣሁት እጄም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ይቆጠርልኝ፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ ለአፌ ጠባቂ አኑር የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ +\v 4 ክፉ ለማድረግ ከመመኘትና ከክፉ አድራጊዎች ጋር ከመተባበር፣ የድግሳቸውም ተካፋይ ከመሆን ጠብቀኝ፡፡ + +\s5 +\v 5 ጻድቅ ሰው ቢቀጣኝ ለእኔ በጐነት ነው፤ እርሱ ቢገሥጸኝ ራሴን እንደሚቀባ ዘይት ነው እኔ ራሴም ይህን እንቢ አልልም፡፡ ጸሎቴ ግን ሁሌም በክፉዎች ተግባር ላይ ነው፡፡ +\v 6 መሪዎቻቸው ከገደል ጫፍ ቁልቁል ይወርወሩ ቃሌ እውነት መሆኗንም ይሰማሉ፡፡ +\v 7 ደግሞም፣ «ሰው ምድርን እንደሚያርስና ዐፈሩን እንደሚፈረካክስ፣ እንዲሁ ዐጥንታችን በሲኦል አፋፍ ላይ ተበታተነ» ይላሉ፡፡ + +\s5 +\v 8 ጌታ፣ ያህዌ ሆይ፣ ዐይኖቼ ወደ አንተ ይመለከታሉ መጠጊያዬ አንተ ነህ፤ ከእንግዲህ ነፍሴን አትተዋት፡፡ +\v 9 ከዘረጉብኝ ወጥመድ ከክፉ አድራጊዎችም አሽክላ ጠብቀኝ፡፡ +\v 10 እኔ በደኅና ሳመልጥ ክፉዎች በገዛ ወጥመዳቸው ይውደቁ፡፡ + +\s5 +\c 142 +\p +\v 1 ድምፄን ከፍ አድርጌ እንዲረዳኝ ወደ ያህዌ እጮኻለሁ ድምፄን ከፍ አድርጌ እንዲምረኝ ልመናየን ወደ ያህዌ አቀርባለሁ፡፡ +\v 2 ብሶቴን በፊቱ አፈስሳለሁ ችግሬንም እነግረዋለሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 መንፈሴ በውስጤ ሲዝል አንተ መንገዴን ታውቃለህ፤ መተላለፊያ መንገዴ ላይ በስውር ወጥመድ ዘረጉብኝ፡፡ +\v 4 ወደ ቀኜ ብመለከት የሚያስብልኝ ሰው አጣሁ ማምለጫም የለኝም ለሕይወቴም ደንታ ያለው የለም፡፡ +\v 5 ያህዌ ሆይ፣ ወደ አንተ እጮኻለሁ «አንተ መጠጊያዬ ነህ በሕያዋን ምድር ዕድል ፈንታዬ ነህ» እላለሁ፡፡ + +\s5 +\v 6 እጅግ ተስፋ ቆርጫለሁና ጩኸቴን ስማ ከእኔ ይበልጥ ብርቱ ስለሆኑ ከአሳዶጆቼ አድነኝ፡፡ +\v 7 ስምህን እንዳመሰግን ነፍሴን ከእስር ቤት አውጣት፡፡ ለእኔ ያደረግኸውን መልካም ነገር ሲመለከቱ ጻድቃን በዙሪያዬ ይሰበሰባሉ፡፡ + +\s5 +\c 143 +\p +\v 1 ያህዌ ሆይ፣ ጸሎቴን ስማ ልመናዬንም አድምጥ፡፡ በታማኝነትህና በጽድቅህ ሰምተህ መልስልኝ፡፡ +\v 2 በአንተ ፊት ማንም ጻድቅ አይደለምና ከባርያህ ጋር ወደ ፍርድ አትግባ፡፡ + +\s5 +\v 3 ጠላት ነፍሴን አሳደዳት ገፍትሮም ወደ መሬት ጣለኝ፡፡ ቀደም ብለው እንደ ሞቱ ሰዎች በጨለማ ውስጥ አኑሮኛል፡፡ +\v 4 ስለዚህ መንፈሴ በውስጤ ልቤም ተስፋ ቆረጠ፡፡ + +\s5 +\v 5 የቀድሞውን ዘመን አስታወስሁ ሥራህንም ሁሉ አሰላሰልሁ አንተ ያደረግኸውንም አውጠነጠንሁ፡፡ +\v 6 በጸሎት እጆቼን ወደ አንተ ዘረጋሁ እንደ ደረቀች ምድር ነፍሴ አንተን ተጠማች፡፡ ሴላ + +\s5 +\v 7 ያህዌ ሆይ፣ መንፈሴ ዝሎአልና ፈጥነህ ስማኝ፡፡ ወደ ጉድጓድ እንደሚወርዱ እንዳልሆን ፊትህንም ከእኔ አትሰውር፡፡ +\v 8 በአንተ ታምኛለሁና በማለዳ ምሕረትህን አሰማኝ፡፡ ነፍሴን ወደ አንተ አንሥቻለሁና የምሄድበትን መንገድ አሳየኝ፡፡ + +\s5 +\v 9 ያህዌ ሆይ፣ አንተን መሸሸጊያ አድርጌአለሁና ከጠላቶቼ አድነኝ፡፡ +\v 10 አንተ አምላኬ ነህና ፈቃድህን ማድረግ አስተምረኝ፡፡ ቅዱስ መንፈስህም በጽድቅ ምድር ይምራኝ፡፡ + +\s5 +\v 11 ያህዌ ሆይ፣ ስለ ስምህ በሕይወት ጠብቀኝ በጽድቅህም ነፍሴን ከመከራዋ አውጣት፡፡ +\v 12 ከታማኝነትሀ የተነሣ ጠላቶቼን አጥፋቸው እኔ ባርያህ ነንና የሕይወቴን ጠላቶች ደምስሳቸው፡፡ + +\s5 +\c 144 +\p +\v 1 እጆቼን ለጦርነት ጣቶቼንም ለውጊያ የሚያሠለጥን ዐለቴ ያህዌ ይባረክ፡፡ +\v 2 አንተ መታመኛዬና መጠጊያዬ ነህ ጽኑ ዐምባዬና ታዳጊዬ የምከለልበት ጋሻዬም ነህ ሕዝቦችን ከእግሬ በታች የምታስገዛልኝም አንተ ነህ፡፡ + +\s5 +\v 3 ያህዌ ሆይ፣ ይህን ያህል የምትንከባከበው ሰው ምን ስለሆነ ነው? ይህን ያህል የምታስብለት የሰው ልጅስ ምንድነው? +\v 4 ሰው እንደ እስትንፋስ ነው ዘመኑም እንደ ጥላ ያልፋል፡፡ + +\s5 +\v 5 ያህዌ ሆይ፣ ሰማያትን ሰንጥቀህ ውረድ ይጤሱም ዘንድ ተራሮችን ዳስሳቸው፡፡ +\v 6 የመብረቅ ብልጭታ ልከህ ጠላቶቼን በትናቸው ፍላጻህን ሰድደህ ግራ አጋባቸው፡፡ + +\s5 +\v 7 ከላይ እጅህን ሰደህ ከብዙ ውሆች፣ ከባዕድ ሰዎችም እጅ ታደገኝ፡፡ +\v 8 አንደበታቸው ሐሰት ይናገራል ቀኝ እጃቸውም የቅጥፈት ቀኝ እጅ ናት፡፡ + +\s5 +\v 9 አምላክ ሆይ፣ አዲስ መዝሙር እዘምርልሃለሁ ዐሥር አውታር ባለው በገና ምስጋና አቀርብልሃለሁ፡፡ +\v 10 አንተ ነገሥታትን ድልን ታጐናጽፋቸዋለህ አገልጋይህ ዳዊትንም ከስለታም ሰይፍ ትታደገዋለህ፡፡ +\v 11 አንደበታቸው ሐሰት ከሚናገር ቀኝ እጃቸው የቅጥፈት ቀኝ እጅ ከሆነችው ከባዕዳን እጅ ታደገኝ፡፡ + +\s5 +\v 12 ወንዶች ልጆቻችን በወጣትነታቸው የተሟላ ዕድገት እንዳገኘ ተክል ሴቶች ልጆቻችንም ቤተ መንግሥት ለማስጌጥ እንደ ተቀረጹ የማእዘን ዐምዶች ይሁኑ፡፡ +\v 13 ጐተራዎቻችን በተለያዩ የእህል ዐይነቶች የተሞሉ ይሁኑ፡፡ በመስኮቻችን የተሰማሩ በጐች እስከ ሺህ ይወለዱ፣ እስከ ዐሥር ሺህ ይባዙ፡፡ + +\s5 +\v 14 ከብቶቻችን ወላድ ይሁኑ፡፡ አይጨንግፉ አይጥፉ ቅሮቻችን በማንም አይደፈሩ እኛም በምርኮ አንወሰድ፡፡ በአደባባዮቻችን ጩኸት አይሰማ፡፡ +\v 15 እንዲህ የሚሆንለት ሕዝብ የተባረከ ነው ያህዌ አምላኩ የሆነለት ሕዝብ የተባረከ ነው፡፡ + +\s5 +\c 145 +\p +\v 1 አምላኬና ንጉሤ ሆይ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ ስምህንም ከዘላለም እስከ ዘላለም እባርካለሁ፡፡ +\v 2 በየቀኑ እባርክሃለሁ ስምህንም ከዘላለም እስከ ዘላለም እባርካለሁ፡፡ +\v 3 ያህዌ ምስጋናው ታላቅ ነው ታላቅነቱም አይመረመርም፡፡ + +\s5 +\v 4 አንዱ ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ ሥራህን ያስተላልፋል ድቅ ሥራህንም ያውጃል፡፡ +\v 5 የክብርህን ግርማ፣ የሥራህንም አስደናቂነት አሰላስላለሁ፡፡ + +\s5 +\v 6 ስለ ድንቅ ሥራህ ኃይል ይናገራሉ እኔም ታላቅነትህን ዐውጃለሁ፡፡ +\v 7 የበጐነትህን ብዛት ያወሳሉ ስለ ጽድቅህም ይዘምራሉ፡፡ + +\s5 +\v 8 ያህዌ ቸር ነው፤ ርኅሩኅም ነው ለቁጣ የዘገየ ምሕረቱም የበዛ ነው፡፡ +\v 9 ያህዌ ለሁሉም ቸር ነው ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው፡፡ + +\s5 +\v 10 ያህዌ ሆይ፣ ፍጥረቶችህ ሁሉ ያመሰግኑሃል ቅዱሳንህም ይባርኩሃል፡፡ +\v 11 ቅዱሳንህ የመንግሥትህን ክብር ይናገራሉ ስለ ኃይልህምይነጋገራሉ፡፡ +\v 12 የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ለሰው ልጆች ያሳውቃሉ የመንግሥቱንም ክብር ይናገራሉ፡፡ + +\s5 +\v 13 መንግሥትህ የዘላለም መግሥት ነው ግዛትህም ለትውልድ ሁሉ ጸንቶ ይኖራል፡፡ + +\s5 +\v 14 ያህዌ የሚንገዳገዱትን ሁሉ ይደግፋል የወደቁትንም ሁሉ ያነሣል፡፡ +\v 15 የሁሉም ዐይን አንተን በተስፋ ይጠብቃል በተገቢ ጊዜ ምግባቸውን ትሰጣቸዋለህ፡፡ +\v 16 እጅህን ትዘረጋለህ የሕያዋንን ሁሉ ፍላጐት ታረካለህ፡፡ + +\s5 +\v 17 ያህዌ በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ ነው በሥራውም ሁሉ ቸር ነው፡፡ +\v 18 ያህዌ ለሚጠሩት ሁሉ በእምነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው፡፡ +\v 19 የሚፈሩትን ፍላጐት ይፈጽማል ጩኸታቸውንም ሰምቶ ያድናቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 20 ያህዌ የሚወዱትን ይጠብቃል ዐመፀኞችን ሁሉ ግን ያጠፋል፡፡ +\v 21 አፌ የያህዌን ምስጋና ይናገራል የሰው ልጅ ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ቅዱስ ስሙን ይባርክ፡፡ + +\s5 +\c 146 +\p +\v 1 ያህዌን አመስግኑ ነፍሴ ሆይ፣ ያህዌን ባርኪ፡፡ +\v 2 በሕይወት በምኖርበት ዘመን ሁሉ ለያህዌ እዘምራለሁ፡፡ + +\s5 +\v 3 በገዦች አትተማመኑ ማዳን በማይችል የሰው ልጅም አትመኩ፡፡ +\v 4 የሰው እስትንፋስ ሲያቆም ወደ መሬት ይመለሳል፡፡ ያን ጊዜ ዕቅዱ እንዳልነበረ ይሆናል፡፡ + +\s5 +\v 5 ረዳቱ የያዕቆብ አምላክ ተስፋውም ያህዌ የሆነለት ሰው የተባረከ ነው፡፡ +\v 6 ሰማይና ምድርን፣ ባሕርንና በውስጡ ያሉትንም የፈጠረ ያህዌ + +\s5 +\v 7 ለተጨቆኑት የሚፈርድ፣ ለተራቡ ምግብን የሚሰጥ እርሱ ነው፡፡ ያህዌ እስረኞችን ነጻ ያወጣል፡፡ +\v 8 ያህዌ የዕውራን ዐይን ይከፍታል፡፡ ያህዌ የተዋረዱን ከፍ ያደርጋል፡፡ ያህዌ ጻድቃንን ይወዳል፡፡ + +\s5 +\v 9 ያህዌ መጻተኞን በምድር ይጠብቃል ደኸ አደጐችንና መበለቶችን ይደግፋል፡፡ የክፉዎችን መንገድ ግን ያጠፋል፡፡ +\v 10 ያህዌ ለዘላለም ይነግሣል ጽዮን ሆይ፣ አምላክሽ ለትውልድ ሁሉ ንጉሥ ነው፡፡ ያህዌ ይመስገን፡፡ + +\s5 +\c 147 +\p +\v 1 ያህዌ ይመስገን አምላካችንን በመዝሙር ማመስገን እንዴት መልካም ነው እርሱን ማመስገን ደስ ያሰኛል፤ ተገቢም ነው፡፡ + +\s5 +\v 2 ያህዌ ኢየሩሳሌምን መልሶ ይሠራታል የተበተነውን የእስራኤል ሕዝብ ይሰበስባል፡፡ +\v 3 ልባቸው የተሰበረውን ይፈውሳል ቁስላቸውንም ይጠግናል፡፡ + +\s5 +\v 4 ከዋክብቱን ይቆጥራል ለእያንዳንዳቸውም ስም ይሰጣቸዋል፡፡ +\v 5 ጌታችን ታላቅ፣ ኃይሉን የሚያስፈራ ነው ማስተዋሉም አይመረመርም፡፡ + +\s5 +\v 6 ያህዌ የተጨቆኑትን ያነሣል ክፉዎችን ግን ወደ ምድር ይጥላል፡፡ +\v 7 ለያህዌ በምስጋና ዘምሩ ለአምላካችን በበገና ዘምሩ፡፡ + +\s5 +\v 8 ሰማያትን በደመና ይሸፍናል በተራሮች ሣር እንዲበቅል ለምድር ዝናብ ያዘጋጃል፡፡ +\v 9 ለእንስሳት ምግባቸውን፣ የቁራ ጫጩቶች ሲንጫጩ ምግባቸውን ይሰጣቸዋል፡፡ + +\s5 +\v 10 በፈረስ ኃይል አይደሰትም ደስታውን በሰው ጉልበት ጥንካሬ አያደርግም፡፡ +\v 11 ያህዌ በሚፈሩት፣ በምሕረቱም በሚታመኑ ይደሰታል፡፡ + +\s5 +\v 12 ኢየሩሳሌም ሆይ፣ ያህዌን አመስግኚ ጽዮንም አምላክሽን አወድሺ +\v 13 እርሱ የበሮችሽን መወርወሪያ አጽንቶአልና በመካከልሽ ያሉ ልጆችሽንም ባርኮአል፡፡ +\v 14 በድንበርሽ ውስጥ ብልጽግና አድርጐአል ማለፊያ ስንዴም ያጠግብሻል፡፡ + +\s5 +\v 15 ትእዛዙን ወደ ምድር ይልካል ቃሉም በፍጥነት ይሮጣል፡፡ +\v 16 በረዶውን እንደ ባዘቶ ያነጥፈዋል ጭጋጉንም እንደ ደመና ይበትነዋል፡፡ + +\s5 +\v 17 የበረዶውን ድንጋይ ቁልቁል ይለቃል በውሽንፍሩስ ቅዝቃዜ ፊት ማን መቆም ይችላል? +\v 18 ቃሉን ልኮ ያቀልጠዋል ነፋሱን ያነፍሳል ውሃንም ያፈስሳል፡፡ + +\s5 +\v 19 ቃሉን ለያዕቆብ፣ ሥርዐት ጽድቁንም ለእስራኤል ያውጃል፡፡ +\v 20 ለማንኛውም ሌላ ሕዝብ ይህን አላደረገም እነርሱም ፍርዱን አላወቁም፡፡ ያህዌ ይመስገን፡፡ + +\s5 +\c 148 +\p +\v 1 ያህዌን አመስግኑ በሰማያት ያላችሁ ያህዌን አመስግኑ በከፍታዎች ያላችሁ ያህዌን አመስግኑ፡፡ +\v 2 መላእክቱ ሁሉ አመስግኑ የመላእክቱ ሰራዊት ሁሉ አመስግት፡፡ + +\s5 +\v 3 ፀሐይና ጨረቃ አመስግት የምታበሩ ከዋክብት ሁሉ አመስግኑት፡፡ +\v 4 ሰማየ ሰማያት አመስግኑት ከሰማይ በላይ ያላችሁ ውሆች አመስግኑት፡፡ + +\s5 +\v 5 እርሱ ስላዘዘ ተፈጥረዋልና የያህዌን ስም ያመስግኑ፡፡ +\v 6 ከዘላለም እስከ ዘላለም አጸናቸው የማይሻር ሕግም ደነገገላቸው፡፡ + +\s5 +\v 7 የባሕር ውስጥ ፍጥረትና ጥልቁ ውሃ ሁሉ ያህዌን ከምድር አመስግኑት፡፡ +\v 8 እሳትና በረዶ ዐመዳይና ጭጋግ ትእዛዙንም የሚፈጽም ዐውሎ ነፋስ + +\s5 +\v 9 ተራሮችና ኮረብቶች፣ የፍሬ ዛፎችና ዝግቦች ሁሉ አመስግኑ፡፡ +\v 10 የዱር አራዊት፣ የቤት እንስሳት በምድር የሚርመሰመሱ ፍጥረቶችና ወፎችም ሁሉ + +\s5 +\v 11 የምድር ነገሥታትና ሕዝቦች ሁሉ መሳፍንቶችና የምድር ገዦች ሁሉ ያህዌን አመስግኑ፡፡ +\v 12 ወጣት ወንዶችና ወጣት ሴቶች አረጋውያንና ሕፃናት ያመስግኑት፡፡ + +\s5 +\v 13 የእርሱ ስም ብቻውን ከፍ ከፍ ብሎአልና ክብሩም ከምድርና ከሰማያት በላይ ነውና የያህዌን ስም ያመስግኑ፡፡ +\v 14 እርሱ ለሕዝቡ ቀንድን አስነሥቶአል ለቅዱሳኑ ሁሉ ምስጋና፣ እጅግ ቅርቡ ለሆነው ሕዝቡ ለእስራኤል ልጆች፡፡ ያህዌን አመስግኑ፡፡ + +\s5 +\c 149 +\p +\v 1 ያህዌን አመስግኑ ለያህዌ አዲስ መዝሙር ዘምሩ + +\s5 +\v 2 በቅዱሳን ጉባኤ ምስጋናውን አቅርቡ፡፡ እስራኤል በፈጣሪው ደስ ይበለው የጽዮንም ልጆች በንጉሣቸው ሐሤት ያድርጉ፡፡ +\v 3 ስሙን በሽብሸባ ያመስግኑ በከበሮና በመሰንቆ ይዘምሩለት፡፡ + +\s5 +\v 4 ያህዌ በሕዝቡ ደስ ይለዋል በማዳኑ ትሑታንን ያከብራቸዋል፡፡ +\v 5 ቅዱሳን በድል ደስ ይበላቸው በመኝታቸውም ላይ እልል ይበሉ፡፡ + +\s5 +\v 6 የእግዚአብሔር ምስጋና በአንደበታቸው በሁለት ወገን የተሳለ ሰይፍም በእጃቸው ይሁን፡፡ +\v 7 ይህም በአሕዛብ ላይ በቀልን፣ በሕዝቦችም ላይ ፍርድን ያደርጉ ዘንድ + +\s5 +\v 8 ንጉሦቻቸውን በሰንሰለት መሳፍንቶቻቸውንም በእግር ብረት ያስራሉ፡፡ +\v 9 ይህም በእነርሱ ላይ የተጻፈውን ፍርድ ለመፈጸም ነው፡፡ ይህ ለቅዱሳኑ ሁሉ ክብር ይሆናል፡፡ ያህዌን አመስግኑ፡፡ + +\s5 +\c 150 +\p +\v 1 ያህዌን አመስግኑ እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት +\v 2 ስለ ብርቱ ሥራው አመስግኑት ከአእምሮ በላይ ስለሆነው ታላቅነቱ አመስግኑት፡፡ + +\s5 +\v 3 በመለከት ድምፅ አመስግኑት በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት፡፡ +\v 4 በከበሮና በሽብሸባ አመስግኑ በባለ አውታርና የእስትንፋስ መሣሪያ አመስግኑት፡፡ +\v 5 ከፍ ያለ ድምፅ ባለው ጸናጽል አመስግኑት ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል ወድሱት፡፡ + +\s5 +\v 6 እስትንፋስ ለው ሁሉ ያህዌን ያመስግን፡፡ ያህዌን አመስግኑ፡፡ diff --git a/26-EZK.usfm b/26-EZK.usfm new file mode 100644 index 0000000..60fe7a0 --- /dev/null +++ b/26-EZK.usfm @@ -0,0 +1,2476 @@ +\id EZK +\ide UTF-8 +\h ሕዝቅኤል +\toc1 ሕዝቅኤል +\toc2 ሕዝቅኤል +\toc3 ezk +\mt ሕዝቅኤል + +\s5 +\c 1 +\p +\v 1 በሰላሳኛው ዓመት ክአመቱም በአራተኛው ወር ከወሩም በአምስተኛው ቀን በኬብሮን አጠገብ ከምርኮኞቹ ጋር አብሬ እየኖርኩኝ ሳለሁ ሰማያት ተክፍተው የእግዚአብሔርን ራዕይ አየሁ። +\v 2 ንጉስ ኢዮአኬም በተማረከበት በአምስተኛው ቀን በከለዳዊያን አገር በኬብሮን ወንዝ አጠገብ +\v 3 የእግዚአብሔር ቃል ወደ ካህኑ ወደ ኡዝ ልጅ ወደ ሕዝቅኤል በኃይል መጣ። የእግዚአብሔር እጅ በእኔ ላይ ነበረች። + +\s5 +\v 4 እኔም በውስጡ የእሳት ነበልባል ያለበት ዙሪያውና ውስጡ የሚያበራ ታላቅ ደመና የሚመስል አውሎ ነፋስ ከሰሜን አቅጣጫ ሲመጣ አየሁ፣ በደመናው ውስጥ ያለው እሳት ቀለሙ ቢጫ ነበር። +\v 5 መካከል ላይ የአራት ህያዋን ፍጡራን ምስል ነበር። ፍጥረታቱ የሰው መልክ ነበራቸው፣ +\v 6 ነገር ግን እያንዳንዳቸው አራት አራት ፊቶችና አራት አራት ክንፎች ነበሩዋቸው። + +\s5 +\v 7 እግሮቻቸው ቀጥ ያሉ ነበሩ፣ ነገር ግን የእግሮቻችው ኮቴ እንደ ነሀስ የሚያበራ የጥጃ ኮቴ ያለ ነበር። +\v 8 ከክንፎቻቸው ስር በአራቱም አቅጣጫ የሰው እጅ ነበራቸው። +\v 9 በክንፎቻቸው ተነካክተው ወደ ኋላ ሳይገላመጡ ቀጥ ብለው ወደፊት ይራመዱ ነበር። + +\s5 +\v 10 መልካቸውም በአንድ በኩል የሰው፥ በቀኝ በኩል የአንበሳ፣ በግራ በኩል የበሬና በሌላ በኩል ደግሞ የንስር ነበር። +\v 11 መልካቸው ያንን ይመስል ነበር፣ ክንፎቻቸውም ተዘርግተው ነበር፣ በሁለት ክንፎቻቸው እርስ በርሳቸው ተነካክተው ነበር፣ በሁለት ክንፎቻቸው ደግሞ ሰውነታቸውን ይሸፍኑ ነበር። +\v 12 እያንዳንዳቸው ሳይገላመጡ ወደፊት ይራመዱ ነበር፣ መንፈስ ወደመራቸው ሳይገላመጡ ይሄዱ ነበር። + +\s5 +\v 13 ህያዋን ፍጡራን የከሰል ፍም እሳት ወይም ችቦ ይመስሉ ነበር፣ ከህያዋን ፍጡራኑ ጋር ደማቅ እሳት ይንቀሳቀስ ነበር፣ የመብረቅ ብልጭታዎችም ነበሩ። +\v 14 ህያዋን ፍጡራኑ በዝግታ ወደ ኋላና ወደ ፊት ይንቀሳቀሱ ነበር፣ እንደ መብረቅም ነበሩ። + +\s5 +\v 15 ወዲያውም ወደ ህያዋን ፍጥረታቱ ተመለከትኩ፣ በምድር ላይ ከእያንዳንዱ ፍጡር አጠገብ አንዳንድ መንኮራኩር ነበረ። +\v 16 የመንኮራኩረቹ መልክ የሚከተለውን ይመስል ነበር፡ እንደ ብርሌ ያንጸባርቁ ነበር፣ አራቱም አንድ አይነት ነበሩ፣ አንዱም በአንዱ ላይ የተስካ ይመስል ነበር። + +\s5 +\v 17 መንኮራኩሮቹ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ፍጡራኑ ወደየትኛውም አቅጣጫ ሳይገላመጡ ይሄዱ ነበር። +\v 18 ዙሪያውን በዓይን የተሞላ ስለሆነ የመንኮራኩሮቹ ጠርዝ ርጅምና አስፈሪ ነበር። + +\s5 +\v 19 ህያዋን ፍጡራኑ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ መንኮራኩሮቹ አብረው ይንቀሳቀሱ ነበር፣ ህያዋን ፍጥረታቱ ወደ ላይ ከፍ ሲሉ መንኮራኩሮቹም ከፍ ይሉ ነበር። +\v 20 መንፈስ ወደሚሄድበት ሁሉ ይሄዱ ነበር፣ የህያዋን ፍጡራኑ መንፈስ ስላለባቸው መንኮራኩሮቹ አብረው ወደ ላይ ከፍ ይሉ ነበር። +\v 21 የፍጡራኑ መንፈስ ስላለባቸው ፍጡራኑ ሲሄዱ መንኮራኩሮቹም ከአጠገባቸው ይሄዱ ነበር፣ ሲቆሙ እነርሱም ይቆሙ ነበር፣ ከምድር ወደ ላይ ከፍ ሲሉ እነርሱም ከፍ ይሉ ነበር። + +\s5 +\v 22 ከህያዋን ፍጡራኑ ራስ በላይ ጠፈር የሚምስል ነገር ነበረ፤ ያም ጠፈር የሚመስል ነገር በህያዋን ፍጡራኑ ራስ በላይ እንደ አስፈሪ በረዶ ዙሪያቸውን ነበረ። +\v 23 ከጠፈሩ በታች የእያንዳንዱ ህያው ፍጡር ክንፍ ቀጥ ብሎ ተዘርግቶ የአንደኛው ፍጡር ክንፍ ከሌላው ፍጡር ክንፍ ጋር ተነካክቶ ነበር። እያንዳምዱ ፍጡር ሰውነቱን የሚሸፍንበት ሁለት ክንፍ ነበረው። + +\s5 +\v 24 ህያዋን ፍጡራኑ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ሁሉ የክንፎቻቸው ድምጽ ይሰማኝ ነበር፣ ድምጹም እንደ ውሃ ጎርፍ፣እንደ ህያው አምላክ ድምጽ፣ እንደ ሠራዊት ድምጽ፣ እንደ ዝናብ ውሽንፍር ነበረ! በሚቆሙበት ጊዜ ክንፎቻችውን ያጥፉ ነበር። +\v 25 በሚቆሙበትና ክንፎቻቸውን በሚያጥፉበት ጊዜ ከራሶቻቸው በላይ ካለው ጠፈር ድምጽ ይመጣ ነበር። + +\s5 +\v 26 ከራሶቻቸው በላይ ከሚገኘው ጠፈር በላይ ዕንቁ የሚመስል የዙፋን አምሳያ ነበር፣ በዙፋኑም አምሳያ ላይ ሰው የሚመስል ተቀምጦ ነበር። + +\s5 +\v 27 ከወገብ በላይ በእሳት የጋለ ብረት ከወገቡ በታች ደግሞ እሳት የሚመስል ምስል አየሁ። +\v 28 በዝናብ ጊዜ እንደሚታይ ቀስተ ደመና ይመስል ዙሪያውም ደማቅ ብርሀን ነበረ። ባየሁትም ጊዜ በግንባሬ ተደፋሁ፣ ወዲያውም የሚያናግረኝ ድምጽ ሰማሁ። + +\s5 +\c 2 +\p +\v 1 "የሰው ልጅ ሆይ ተነስና ቁም ክዚያም አነጋግርሃልሁ" አለኝ። +\v 2 እየተናገረኝ ሳለ መንፈስ አንስቶ በእግሮቼ አቆመኝ የናገረኝንም ሰማሁ። +\v 3 "የሰው ልጅ ሆይ አመፀኛ ወደሆኑትና በእኔ ላይ ወዳመፁት ወደ እስራኤል ህዝብ እልክሃለሁ፦ እነርሱና የቀደሙ አባቶቻችው እስከዚች ቀን ድረስ በድለውኛል! + +\s5 +\v 4 ልጆቻቸው የተጨማደደ ፊትና ደንዳና ልብ አላቸው። አንተም እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ትላቸዋለህ። +\v 5 አመጸኛ ቤት ስለሆኑ ወይ ይሰሙሃል አሊያም አይሰሙህም። ነገር ግን ቢያንስ ነቢይ በመካከላቸው እንዳለ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 6 አንተም የሰው ልጅ ሆይ እነርሱንም ሆነ ቃላቸውን አትፍራ። በእሾሆች፣በኩርንችት እና በጊንጦች መካከል ብትቀመጥም አትፍራ። አመጸኛ ቤቶች ስለሆኑ ቃላቸውን አትፍራ ፊታቸውን አይተህ አትደንግጥ። + +\s5 +\v 7 እጅግ አመጸኞች ስለሆኑ ቢሰሙህም ባይሰሙህም ቃልን ትነግራቸዋለህ። +\v 8 ነገር ግን አንተ የሰው ልጅ የምነግርህን ስማ። አንተም እንደአመጸኞቹ ሰዎች አመጸኛ አትሁን። አፍህን ክፈትና የምሰጥህን ብላ። + +\s5 +\v 9 ጽሁፍ የተጻፈበት ጥቅል የያዝ እጅ ወደኔ ሲዘረጋ አየሁ። +\v 10 በፊቴም ዘረጋው ክፊትና ከኋላው ተጽፎበት ነበር፤ በሀዘን፣ በልቅሶና በዋይታ የተሞላ ነበር። + +\s5 +\c 3 +\p +\v 1 የሰው ልጅ ሆይ ያገኘኽውን ብላ ይህን የመጽሀፍ ጥቅል ብላ ሄደህም ለእስራኤል ህዝብ ተናገር። +\v 2 አፌንም ከፈትኩ የመጽሀፉን ጥቅል አጎረሰኝና +\v 3 "የሰው ልጅ ሆይ በሰጠሁህ በዚህ የመጽሀፍ ጥቅል ሆድህን ሙላ" አለኝ። እኔም በላሁት እንደማርም ጣፈጠኝ። + +\s5 +\v 4 ከዚያም "የሰው ልጅ ሆይ ወደ እስራኤል ህዝብ ሄደህ ቃሌን ንገራቸው" አለኝ። +\v 5 ምክንያቱም የተላከው ቋንቋቸው ወደማይታወቅ ወይም አስቸጋሪ ወደሆን ህዝብ አይደለም፦ +\v 6 እንግዳ ቋንቋ ወደሚናገር ታላቅ ህዝብ ወይም የቋንቋቸውን ቃላት መረዳት ወደሚያስቸግር ህዝብ አላኩህም። ወደዚህ ዓይነት ህዝብ ብልክህ ኖሮ ይሰሙህ ነበር። ነገር ግን የእስራኤል ህዝብ እኔን መስማት ስለማይፈልጉ አይሰሙህም። +\v 7 የእስራኤል ህዝብ ሁሉ ግንባረ ጠንካራና አንገተ ደንዳና ናቸው። + +\s5 +\v 8 እነሆ! ፊትህን እንድፊታቸው ግንባርህንም እንደግንባራቸው ጠንካራ አደርገዋለሁ። +\v 9 ግንባርህን ከባልጩት ድንጋይ ይልቅ እንደሚጠነክር እንደ አልማዝ አድርጌዋለ! ስለዚህ የእሴራኤል ህዝብ አመጸኞች ስለሆኑ አትፍራቸው ፊታቸውንም አይተህ አትደንግጥ። + +\s5 +\v 10 ቀጥሎሜ እንዲህ አለኝ "የሰው ልጅ ሆይ የነገርኩህን ቃል ስማ በልብህም ተቀበለው። +\v 11 ከዚያም በምርኮ ወዳሉት ህዝብህ ሂድና ቢሰሙህም ባይሰሙህም 'እግዚአብሔር እንዲህ ይላል' በላቸው።" + +\s5 +\v 12 መንፈስም ከምድር ከፍ አደረግኝ ከኋላዬም የእግዚአብሔር ክብር በማደሪያው ይባረክ የሚል እንደ ምድር መናወጥ ዓይነት ድምጽ ሰማሁ። +\v 13 ወዲያውም የህያው ፍጥርታቱ ክንፎች ሲነካካ የሚፈጠረውን ድምጽ፣ አብረዋቸው ያሉትን መንኮራኩሮች ድምጽ፥ እና የምድር መናወጥ ድምጽ ሰማሁ። + +\s5 +\v 14 መንፈስም አንስቶ ወሰደኝ፤ የእግዚአብሔርም እጅ በእኔ ላይ ከብዶ ስለነበር የምሄደው በምሬትና በጋለ መንፈስ ነበር። +\v 15 ከዚያም በኬብሮን ወንዝ አጠገብ ወደሚኖሩት በቴላቢብ ወደሚገኙት ምርኮኞች ሄጄ በድንጋጤና በመደነቅ ተሞልቼ በመካከላቸው ሰባት ቀን ተቀመጥኩ። + +\s5 +\v 16 ከስባት ቀንም በኋላ እንዲህ ሆነ፥ +\v 17 "የሰው ልጅ ሆይ አንተን ለእስራኤል ህዝብ እንደጠባቂ አድርጌሀለሁ፥ ስለዚህ የአፌን ቃል ስማና የእኔን ማስጠንቀቂያ ንገራቸው! +\v 18 ኃጢአተኛውን 'በእርግጥ ትሞታለህ' ብለህ ንገረው ብዬህ አንተ ግን ባትነግረው ከክፉ መንገዱም እንዲመለስ ባታስጠነቅቀው እርሱ በኃጢአቱ ይሞታል ደሙን ግን ከእጅህ እፈልጋለሁ። +\v 19 ነገር ግን ኃጢአተኛውን ብታስጠነቅቀው እርሱ ግን ከክፋቱና ከመጥፎ ተግባሩ ባይመለስ በኃጢአቱ ይሞታል አንተም ነፍስህን ታድናለህ።" ብሎ እግዚአብሔር ሲናገረኝ ሰማሁ። + +\s5 +\v 20 ደግሞም አንድ ጻድቅ ሰው ጽድቅ ማድረግን ቢተው እኔም በፊቱ መሰናክል ሳስቀምጥ እርሱ በኃጢአቱ ይሞታል። አንተ ስላላስጠነቀከው እርሱ በኃጢአቱ ይሞታል፣ ቀድሞ የሰራውንም የጽድቅ ስራ አላስብለትም፣ ነገር ግን አንተን የሞቱ ተጠያቂ አደርግሀለሁ። +\v 21 ነገር ግን አንድ ጻድቅ ሰው ኃጢአት መስራቱን እንዲያቆም ብታስጠነቅቀው ከማስጠንቀቂያው የተነሳ በእርግጥኝነት በህይወት ይኖራል፣ አንተም የራስህን ህይወት ታድናለህ።" + +\s5 +\v 22 ደግሞም የእግዚአብሔር እጅ በላዬ መጣ፣ እግዚአብሔርም ፣ "ተነሳ! ወደ ሜዳማው ቦታ ሂድ፣ በዚያ የምነግርህ ነገር አለ" አለኝ። +\v 23 እኔም ተነስቼ ወደ ሜዳማው ቦታ ሄድኩ፥ በዚያም በኬብሮን ወንዝ አጠገብ ያየሁት ዓይነት የእግዚአብሔር ክብር ነበረ፣ ስለዚህም በግንባሬ ተደፋሁ። + +\s5 +\v 24 የእግዚአብሔርም መንፈስ መጥቶ በእግሮቼ አቆመኝና እንዲህ ሲል ተናገረኝ "ወደ ቤትህ ሂድና በር ዘግተህ ተቀመጥ፣ +\v 25 ምክንያቱም አሁን የሰው ልጅ ሆይ በመካከላቸው እንዳትንቀሳቀስ በገመድ ያስሩሀል። + +\s5 +\v 26 አመጸኛ ህዝብ ስለሆኑ እንዳትገስፃቸው እኔ ምላስህን ከላንቃህ ጋር አጣብቀዋለሁ አንተም ዲዳ ትሆናለህ። +\v 27 ነገር ግን እኔ ስናገርህ አፍህን እከፍታለሁ አንተም 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል' ትላቸዋለህ፤ አመጸኛ ህዝብ ስለሆኑ የሚሰማ ይሰማሀል የማይሰማ አይሰማህም!" + +\s5 +\c 4 +\p +\v 1 አንተ ግን የሰው ልጅ ሆይ ሸክላ ውሰድና የኢየሩሳሌምን ካርታ ሳልበት። የጦር ከበባ አድርግባት፣ +\v 2 ምሽግም ስራባት፣ ዙሪያውን በአፈር ደልድለው፣ ትልቅ ቅጥር ና የጦር ሰፈሮችን አስቀምጥ ፣ ቅጥር መደርመሻ ግንዶች ዙሪያውን አስቀምጥ። +\v 3 ክዚያም ብረት ምጣድ ለራስህ ውሰድና በአንተና በከትማይቱ መካከል በብርት አጥር ምሳሌ አቁመው። ትከበባለችና ፊትህንም ወደከትማይቱ አዙር ክበባትም! ይህም ለእስራኤል ህዝብ ምልክት ይሆናል። + +\s5 +\v 4 ክዚያም በግራ ጎንህ ተኛና የእስራኤልን ህዝብ ኃጢአትም ተሸከም፤ በእስራኤል ህዝብ ፊት በግራ ጎንህ በተኛህበት ቀን ቁጥር ልክ ኃጢአታቸውን ትሸከማለህ። +\v 5 አንድ ቀን የሚቀጡበትን አንድ አመት እንዲወክል እኔ ራሴ መድቤልሀለሁ፡ 390 ቀናት! በዚህ መልኩ የእስራኤልን ህዝብ ኃጢአት ትሸከማለህ። + +\s5 +\v 6 እነዚህን ቀናት ስትጨርስ በቀኝ ጎንህ ትተኛና የይሁዳን ህዝብ ኃጢአት ለአርባ ቀናት ትሸከማለህ። አንድ ቀን አንድ አመት እንዲወክል መድቤልሀለሁ። +\v 7 እጅህን ክልብስህ ውስጥ አውጥተህ ፊትህን ወደተከበበችው ኢየሩሳሌም ከተማ አድርገህ ትንቢት ትናገርባታለህ። +\v 8 እነሆ! የሜርኮው ዘመን እስኪፈጸም ድረስ ከአንድ ጎን ወደ ሌላ ጎን እንዳትዞር ቀንበርን አድርጌብሀለሁ። + +\s5 +\v 9 ስንዴ፣ገብስ፣ባቄላ፥ ምስር፥ ጤፍና አጃ ወስደህ በአንድ ዕቃ ውስጥ አድርገህ በጎንህ በምትተኛባቸው ቀናት ቁጥር ልክ ዳቦ ትጋግራልህ። ለ390 ቀናት ትመገበዋለህ! +\v 10 በየቀኑ ሃያ ሃያ ሰቅል የሚመዝን ዳቦ ትበላለህ። በየጊዜውም ትመገበዋለህ። +\v 11 አንድ ስድስተኛ ኢን ውሃም ትጠጣለህ። በየጊዜውም ትጠጣዋለህ። + +\s5 +\v 12 እንደ ገብስ ቂጣ አድርገህ ትበላዋለህ፣ የምትጋግረው ግን በሰው ዓይነ ምድር ነው። +\v 13 እግዚአቤሔር "በበተንኳቸው አህዛብ መካከል የእስራኤል ህዝብ የሚመገቡት ዳቦ ርኩስ ይሆናል።" ይላል። + +\s5 +\v 14 እኔም "ወየው ጌታ እግዚአብሔር ሆይ ረክሼ አላውቅም! የሞተ ወይም በአውሬ የተገደለ በልቼ አላውቅም፣ የረከሰ ሥጋም ወደ አፌ ገብቶ አያውቅም!" አልኩኝ። +\v 15 እርሱም "እነሆ በሰው ዓይነ ምድር ፋንታ የከብት ፍግ ስጥቼሀለሁ ዳቦውን በእርሱ መጋገር ትችላለህ" አለኝ። + +\s5 +\v 16 ደግሞም "የስው ልጅ ሆይ! ከኢየሩሳሌም የእንጀራን በትር እሰብራለሁ፣ ህዝቡም እንጀራን በጭንቅ ውሃም በስስት ይጠጣሉ። +\v 17 የምግብና የውሃ እጥረት ስለሚኖር ሰው ወንድሙን በድንጋጤ ይመለከተዋል፣ ከኃጢአታቸው የተነሳ ይመነምናሉ።" አለኝ። + +\s5 +\c 5 +\p +\v 1 "ከዚያም የሰው ልጅ ሆይ ጎራዴን እንደጢም መላጫ ተጠቀመህ ራስህንም ጢምህንም ተላጨው፣ በመቀጠልም ሚዛን ተጠቅመህ ጠጉሩን ትከፍለዋለህ። +\v 2 የምርኮው ዘመን ሲያበቃ የጠጉሩን አንድ ሶስተኛ በከተማው መካከል በእሳት ታቃጥለዋለህ። አንድ ሶስተኛውንም ወስደህ በክተማይቱ ዙሪያ አስቀምጠህ በሰይፍ ትመታዋለህ። ከዚያም አንድ ሶስተኛውን ወደ ነፋስ ትበትነዋለህ፣ እኔም ህዝቡን አሳድድ ዘንድ ሰይፌን እመዛለሁ። + +\s5 +\v 3 ነገር ግን ጥቂት ጠጉሮችን ወስደህ በጋቢህ ጫፍ ላይ ትቋጥረዋለህ። +\v 4 ክዚያም በርከት ያለ ጠጉር ወስደህ ወደ እሳቱ መሀል ጥለህ በእሳቱ አቃጥለው፤ በእሳት ውስጥ ይቃጠል፤ ከዚያም ውስጥ እሳት ወደ እስራኤል ህዝብ ሁሉ ይወጣል።" + +\s5 +\v 5 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፣ "ይህች በሌሎች አገሮች ዙሪያዋን እንድትዋሰን ያደረኳት፣ በአህዛብ መካከል ያለች ኢየሩሳሌም ናት። +\v 6 ነግር ግን ከሌሎች አህዛብ ይልቅ ከኃጢእታቸው የተነሳ ትዕዛዛቴን አቃለዋል፣ በዙሪያቸው ካሉ አገሮች ይልቅ ህጌን ተላልፈዋል። ፍርዴን አቃለዋል በህጌም አልኖሩም!" + +\s5 +\v 7 ስለዚህም ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፣ "በዙሪያቹ ካሉ አገሮች ይልቅ አመጸኞች ስለሆናችሁና በህጌ ስላልኖራችሁ ተግባራችሁም እንድትዕዛዛቴ ስላልሆነ ይባስ ብሎ የምታደርጉት ሁሉ በዙሪያችሁ እንዳሉት አግሮች ትዕዛዝ ስለሆነ ።" +\v 8 ስለዚህም ይላል ጌታ እግዚአብሔር "እነሆ! እኔ እራሴ በእናንተ ላይ እነሳለሁ! አህዛብ ሁሉ ያዩ ዘንድ ፍርዴን በመካከልሽ አመጣለሁ። + +\s5 +\v 9 ከጸያፍ ተግሮችሽ የተነሳ አድርጌ የማላውቀውን ደግሜም የማላደርገውን ነገር በአንቺ ላይ አደርጋለሁ። +\v 10 ስለዚህም በመካከልሽ አባቶች ልጆቻችውን ልጆችም አባቶቻቸውን ይበላሉ፣ ፍርድንም አመጣብሻለሁና የተርፉትን በየአቅጣጫው እበትናቸዋለሁ! + +\s5 +\v 11 ስለዚህም በራሴ እምላለሁ፦ ይህ የጌታ የእግዚአብሄር አዋጅ ነው- ቤተመቅደሴን በሚያስጠሉ ነግሮችና በሚያጸይፉ ተግባራት ሞልታችሁታልና ከቁጥር አጎድላችኋለሁ፤ ፊቴን አልመልስልሽም፣ አልራራልሽምም። +\v 12 አንድ ሶስተኛችው ህዝብ በመቅሰፍት ይሞታል በመካከልሽም በረሀብ ያልቃሉ፣ አንድ ሶስተኛው ደግሞ በከበቡሽ ጠላቶች ሰይፍ ይገደላሉ። ቀሪውን አንድ ሶስተኛ ደግሞ በየአቅጣጫው እበትናቸዋለሁ አሳድዳቸውም ዘንድ ሰይፌን ከሰገባው እመዛለሁ። + +\s5 +\v 13 ከዚያም ቁጣዬ ይፈጸማል፣ በእነርሱም ላይ የነበረኝ ንዴት ይበርዳል። በእነርሱ ላይ የነበረኝ ንዴቴ በተፈጸመ ጊዜ እኔ እግዚአብሄር በቁጣዬ እንደተናገርኳቸው ያውቃሉ። +\v 14 ዙሪያሽን በከበቡሽ አህዛብና በአላፊ አግዳሚው ሁሉ የተዋረድሽና አሳፋሪ አድርግሻለሁ። + +\s5 +\v 15 ስለዚህ ኢየሩሳሌም በሌሎች የምትወገዝና መቀለጃ በዙሪያዋ ላሉ አህዛብ ቁጣና ድንጋጤ ትሆናልች። ፍርዴን በንዴትና በቁጣ በጽኑ ተግሳጽም አመጣባችኋለሁ- እኔ እግዚአብሔር ይህን ተናግሬአለሁ። +\v 16 የርሀብን አስከፊ ቀስቶች እሰድባችኋለሁ፣ ያም እናንተን የማጠፋበት መሳሪያ ይሆናል። ርሀብን አበዛለሁ የእንጀራ በትራችሁንም እሰብራለሁ። +\v 17 ልጆች አልባ እንድትሆኑ ርሀብና አደጋን እልክባችኋለሁ። መቅሰፍትና ደም በመካከላችሁ ያልፋል ሰይፍንም አመጣባችኋለሁ -- እኔ እግዚአብሄር ይህን ተናግሬአልሁ!" + +\s5 +\c 6 +\p +\v 1 የእግዚአብሄር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ ፊትህን ወደ እስራኤል ተራሮች አዙርና ትንቢት ተናገር። +\v 3 እንዲህም በላቸው 'የእስራኤል ተራሮች ሆይ የጌታ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ! ጌታ እግዚአብሔር ለተራሮች፣ ለኮረብቶች፣ ለሸንተረሮችና ለሸለቆዎች እንዲህ ይላል፡ እነሆ ሰይፍን አመጣባችኋለሁ ከፍታችሁን ሁሉ አጠፋለሁ። + +\s5 +\v 4 መሰዊያዎቻችሁ ባድማ ይሆናሉ የዕጣን መሰዊያዎቻችሁም ይደመሰሳሉ የሞቱ ሰዎቻችሁን ሬሳዎች በጣዖቶቻቸው ፊት እጥላለሁ። +\v 5 የእስራኤልን ህዝብ ሬሳዎችን በጣዖቶቻችው ፊት አጋድማለሁ፣ አጥንቶቻችሁንም በመሰዊያዎቻችሁ ዙሪያ እበትናለሁ። + +\s5 +\v 6 መሰዊያዎቻችሁ የተጣሉና ባድማ እንዲሆኑ የምትኖሩባቸው ከተሞች ሁሉ የተጣሉ የማምለኪያ ኮረብቶቻቸው ሁሉ ባድማ ይሆናሉ፣ እንዳልነበሩም ሆነው ይጠፋሉ፤ የዕጣን መሰዊያዎቻችሁ ይወገዳሉ ሥራቼሁ ሁሉ ተጠርጎ ይጠፋል። +\v 7 የሰዎች ሬሳ በመካከላችሁ ይወድቃል ያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ታውቃላችሁ! + +\s5 +\v 8 ነገር ግን ቅሬታዎችን አስቀራለሁ፣ እናንተ በየአገሩ ስትበተኑ ከአህዛብ መካከል ከሰይፍ የሚያመልጡ ይኖራሉ። +\v 9 እነዚያ ያመለጡትም በምርኮ አገር ሆነው ከእኔ ዘወር ካለው አመንዝራ ልባቸውና ወደ ጣዖታቶቻቸው ከሚያየው አመንዝራ ዓይናቸው የተነሳ ምን ያህል እንዳዝንኩ ስለእኔ ያስባሉ። ባደረጉት ክፋትና ርኩሰት መጸጸታቸው ከፊታቸው ይነበባል። +\v 10 ስለዚህም እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ያውቃሉ። ይህን ክፉ ነገር አመጣባቸዋለሁ ብዬ አስቀድሜ የተናገርኩት በዓላማ ነው። + +\s5 +\v 11 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡ ከፈጸሙት አስነዋሪ ተግባር የተነሳ የእስራኤል ህዝብ በሰይፍ፣ በረህብና በቸነፈር ይጠፋሉና በእጅህ እያጨበጭችብክ በእግርህም መሬቱን እየመታህ "ወዮ" እያልክ ጩህ! +\v 12 በሩቅ ያለው በቸነፈር በቅርብ ያለው በሰይፍ ይጠፋሉ። ከዚያ የተረፉት ደግሞ በርሀብ ያልቃሉ፤ በዚህ መንገድ ቁጣዬን በእነርሱ ላይ እፈጽማለሁ። + +\s5 +\v 13 በጣዖቶቻቸው መካከል፣ በመሰዊያዎቻቸው ዙሪያ፣ ከፍ ባሉ ተራሮቼ አናት ላይ፣ እንዲሁም በለመለመ ዛፍ ሁሉና በግዙፍ ዋርካ ስር- ለጣዖቶቻቸው በሚያጤኑበት ሥፍራ ሁሉ የተገደሉ ሰዎቻቸው ተጥለው ሲያዩ ያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ያውቃሉ። +\v 14 በገዛ እጄ እመታችኋለሁ የሚኖሩብትን ስፍራ ሁሉ ከምድረ በዳ እስከ ዲብላህ ድረስ ምድሪቱን የተጣለችና ባድማ አደርጋታለሁ።" + +\s5 +\c 7 +\p +\v 1 የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፣ +\v 2 "አንተ የሰው ልጅ ሆይ -- ጌታ እግዚአብሔር ለእስራኤል ምድር የሚለው እንዲህ ነው፣ 'መጨረሻ! በምድሪቱ አራቱም ማዕዘን መጨረሻ መጥቷል! + +\s5 +\v 3 ቁጣዬን ስለላኩባችሁ መጨረሻችሁ ቀርቧል፣ እኔም እንደመንገዳችሁ እፈርድባችኋለሁ፤ ክፉ ሥራችሁን ሁሉ በእናንተ ላይ እመልስባችኋለሁ። +\v 4 በርህራሄ አላያችሁም ምህረትም አላደርግላችሁም፤ ነገር ግን መንግዳችሁን እመልስባችኋለሁ፣ ጥፋታችሁ በመካከላችሁ ይሆናል፥ በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ታውቃላችሁ! + +\s5 +\v 5 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡ መዓት! በመዓት ላይ መዓት! እነሆ እየመጣ ነው! +\v 6 መጨረሻ በእርግጥ እየመጣ ነው፤ መጨረሻው ወደ እናንተ እየተራመደ ነው! እነሆ እየመጣ ነው! +\v 7 በምድሪቱ በምትኖሩት ላይ ፍርድ እየመጣ ነው። ጊዜው ደርሷል፤ የጥፋት ቀን ቀርቧል፤ ተራሮች ከእንግዲህ ለደስታ አይሆኑም። + +\s5 +\v 8 በቅርቡ እንደ መንገዳችሁ በምፈረድባችሁ ጊዜና ክፋታችሁን በመለስኩባችሁ ጊዜ መዓቴን አፈስባችኋለሁ ቁጣዬም በላያችሁ ይሆናል። +\v 9 ዓይኔ አይራራላችሁም ምህረትም አላደርግላችሁም። እንዳደርጋችሁብኝ አደርግባችኋለሁ፤ የምቀጣችሁ እኔ እንደሆንኩ ታውቁ ዘንድ ክፋታችሁም በመካከላችሁ ይሆናል። + +\s5 +\v 10 እነሆ ቀኑ እየደረሰ ነው። ጥፋት ወጥቷል። በትሩ በትዕቢት አበባ ፈክቷል። +\v 11 አመጽ ወደ ኃጢአት በትርነት አድጓል-- አንዳቸውም፣ ከህዝባቸውም ማንም፣ የትኛውም ሀብታቸው፣ የትኛው ጠቃሚ ነገራቸው አይተርፍም። + +\s5 +\v 12 ቀኑ እየመጣ ነው፤ ቀኑ እየቀረበ ነው። ቁጣዬ በህዝቡ ሁሉ ላይ ስለሆነ ንብረት የገዛ አይደሰት፣ የሸጠም አይዘን! +\v 13 ምክንያቱም በህይወት ዘመናቸው ሁሉ ሻጭ የሸጠውን አያስመልስም፣ ራዕዩ ለመላው ህዝብ ነው። በኃጢአቱ የሚጸና አይበረታምና አይመለሱም። + +\s5 +\v 14 መለከት ነፉ የሚያስፈልገውን ሁሉ አዘጋጁ ነገር ግን ቁጣዬ በህዝቡ ሁሉ ላይ ነውና ለጦርነት የከተተ አንድም የለም! +\v 15 በውጭ ሰይፍ በውስጥ ደግሞ ረሀብና ቸነፈር አለ። በእርሻ ቦታ ያሉ በስይፌ ይወድቃሉ፥ ረሀብና ቸነፈር ደግሞ በከተማ ያሉትን ይፈጃል። +\v 16 ነገር ግን ከእነርሱ ጥቂቶች ተርፈው ወደ ተራሮች ይሄዳሉ። ሁሉም ስለኃጢአታቸው እያንዳንዱም ስለስንፍናው እንደ ደሸለቆ እርግብ ያለቅሳሉ። + +\s5 +\v 17 እጅ ሁሉ ይቀልጣል ጉልበትም ሁሉ እንደ ውሀ ይደክማል፣ +\v 18 ማቅም ይለብሳሉ ድንጋጤም ይከባቸዋል፤ ፊት ሁሉ በእፍረት ይሸፈናል ራስም ሁሉ ጠጉር አልባ ይሆናል። +\v 19 ብራቸውን በጎዳናዎቹ ላይ ይጥላሉ ወርቃቸውም እንደ ጕድፍ ይሆናል በእግዚአብሔር መዓት ቀን ብራቸውና ወርቃቸው ያድናቸው ዘንድ አይችልም። እርሱ የኃጢአታቸው ዕንቅፋት ሆኖአልና ሰውነታቸውን አያጠግቡም ሆዳቸውንም አይሞሉም + +\s5 +\v 20 የክብሩ ጌጦችንም በማንአለብኝነት ወስደው ክፋታቸውንና የፈጸሙትን አመጻ የሚያሳዩ የምንዝርና ምስሎችን አበጁ፣ ስለዚህ እኔ እነዚህን ምስሎች ርኩስ እድርጌባቸዋለሁ። +\v 21 በባዕድም እጅ ለንጥቂያ፥ በምድር ኃጢአተኞችም እጅ ለብዝበዛ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ እነርሱም ያረክሱአቸዋል። +\v 22 የተቀድሰውን ቦታዬን ባረከሱ ጊዜ ፊቴንም አዞርባቸዋለሁ፥ ወንበዴዎችም ይገቡባታል ያረክሱትማል። + +\s5 +\v 23 ምድሪቱ ደም ባመጣው ፍርድ፥ ከተማዪቱም በግፍ ተሞልታለችና ሰንሰለት ሥራ። +\v 24 ስለዚህም ከአሕዛብ ዘንድ ከሁሉ የሚከፉትን አመጣለሁ ቤቶቻቸውንም ይወርሳሉ፣ መቅደሶቻቸው ስለሚረክሱ የኃያላንንም ትዕቢት ወደ ፍጻሜ አመጣለሁ። +\v 25 ፍርሀት ይመጣል! ሰላምን ይሻሉ ነገር ግን ምንም ሰላም አይገኝም። + +\s5 +\v 26 ድንጋጤ በድንጋጤ ላይ ወሬም በወሬ ላይ ይመጣል! ከነቢዩም ዘንድ ራዕይን ይሻሉ ነገር ግን ከካህኑም ዘንድ ህግ፥ ከሽማግሌዎችም ዘንድ ምክር ይጠፋል። +\v 27 ንጉሡም ያለቅሳል፥ ልዑሉም ውርደትን ይለብሳል፥ የምድሪቱም ሕዝብ እጆቼ በፍርሀት ይንቀጥቀጣሉ። እንደ መንገዳቸውም መጠን ይህን አደርግባቸዋለሁ! እኔ እግዚአብሔር እንድሆንኩ እስኪያውቁ ድረስ በፍርዳቸውም መጠን እፈርድባቸዋለሁ ። + +\s5 +\c 8 +\p +\v 1 በስድስተኛውም ዓመት በስድስተኛው ወር ከወሩም በአምስተኛው ቀን በቤቴ ተቀምጬ ሳለሁ የይሁዳም ሽማግሌዎች በፊቴ ተቀምጠው ሳሉ፥ በዚያ የጌታ የእግዚአብሔር እጅ እንደገና በእኔ ላይ ወደቀች። +\v 2 እኔም አየሁ፥ እነሆም፥ የሰው አምሳያ ነበረ ከወገቡም በታች እሳት ይመስል ነበረ፥ ከወገቡም በላይ የቀለጠ ብረት የሚመስል የሚያብለጨልጭ ነበር። + +\s5 +\v 3 ከዚያም እጅ የሚመስል ነገር ዘረጋ በራስ ጠጕሬም ያዘኝ፤ መንፈስም በምድርና በሰማይ መካከል አነሣኝ፥ በእግዚአብሔርም ራእይ ወደ ኢየሩሳሌም ወደ ሰሜን ወደሚመለከተው ወደ ውስጠኛው አደባባይ በር መግቢያ አመጣኝ በዚያም ቅንዓት የሚያነሣሣ የቅንዓት ጣዖት ተተክሎ ነበር። +\v 4 እነሆም፥ በቈላው እንዳየሁት ራእይ አይነት የእስራኤል አምላክ ክብር በዚያ ነበረ። + +\s5 +\v 5 እርሱም፦ "የሰው ልጅ ሆይ፥ ዓይንህን ወደ ሰሜን አንሣ አለኝ።" ዓይኔንም ወደ ሰሜን መንገድ አነሣሁ እነሆም፥ በመሠዊያው በር በሰሜን በኩል መግቢያው ላይ የቅንዓት ጣዖት ነበረ። +\v 6 የእግዚአብሔርም መንፈስ፦ "የሰው ልጅ ሆይ፥ አየህ የሚያደርጉትን? ይህ ከመቅደሴ ያርቁኝ ዘንድ የእስራኤል ቤት በዚህ የሚያደርጉት ታላቁን ርኵሰት ነው! ግን ዞረህ ስታይ ከዚህ የበለጠ ታላቅ ርኵሰት ታያለህ አለኝ!" + +\s5 +\v 7 ወደ አደባባዩም መግቢያ አመጣኝ ፥ በግንቡ ውስጥ ቀዳዳ እንዳለ አየሁ። +\v 8 እርሱም፦ "የሰው ልጅ ሆይ፥ ግንቡን ንደለው አለኝ ግንቡንም በነደልሁት ጊዜ መግቢያ በር አገኘሁ። +\v 9 እርሱም፦ "ግባና የሚያደርጉትን የከፋ ርኵሰት እይ አለኝ። + +\s5 +\v 10 እኔም ገባሁና እነሆ፥ በግንቡ ዙሪያ ላይ የሚሳብና አስቀያሚ አውሬ ምስል አየሁ! በግንቡም ዙሪያ የእስራኤል ቤት ጣዖታት ሁሉ ተስለው አየሁ። +\v 11 ሰባ እስራኤል ቤት ሽማግሌዎች በዚያ ቆመው ነበር፥ በመካከላቸውም የሳፋን ልጅ ያእዛንያ ቆሞ ነበር፥ በምስሎቹም ፊት ቆመው ነበር ። እያንዳንዱ ሰው በእጁ ጥናውን ይዞ ነበር፥ የዕጣኑም ጢስ ሽቱ ይወጣ ነበር። + +\s5 +\v 12 እርሱም፦ "የሰው ልጅ ሆይ፥ የእስራኤል ቤት ሽማግሌዎች በጨለማ የሚያደርጉትን አየህ? 'እግዚአብሔር አያየንም እግዚአብሔር ምድሪቱን ትቶአታል' ብለው ሁሉም ሰው ይህን የሚያድርገው በየራሱ ስውር ቦታ ከጣዖቱ ጋር ሆኖ ነው። +\v 13 እርሱም፦ "ደግሞ ወደኋላ ዙርና እያደረጉ ያለውን ከዚህ የበለጠውን ሌላ ታላቅ ርኵሰት እይ" አለኝ። + +\s5 +\v 14 ከዚያም ወደ በሰሜን አቅወጣጫ ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤት በር መግቢያ አመጣኝ፣ እነሆም! ሴቶች ለተሙዝ እያለቀሱ በዚያ ተቀምጠው ነበር። +\v 15 እርሱም፦ "የሰው ልጅ ሆይ፥ ይህን ታያለህ? ደግሞ ተመልሰህ ከዚህ የበለጠ ርኵሰት ታያለህ አለኝ። + +\s5 +\v 16 ደግሞም ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ውስጠኛው አደባባይ አመጣኝ፥ እነሆም፥ በእግዚአብሔር መቅደስ መግቢያ በወለሉና በመሠዊያው መካከል ሀያ አምስት የሚያህሉ ሰዎች ጀርባቸው ወደ እግዚአብሔር መቅደስ ፊታቸውም ወደ ምሥራቅ ሆኖ ሸሚሽ ለተሰኘው ጣዖት ይሰግዱ ነበር። + +\s5 +\v 17 እርሱም፦ የሰው ልጅ ሆይ፥ ይህን ታያለህ? በዚህ የሚያደርጉት ይህ ርኵሰት ለይሁዳ ቤት እንድ ቀላል ነገር ነውን? ምድሪቱን በግፍ ሞልተዋታል ያስቈጡኝም ዘንድ ተመልሰዋል፥ ቅርንጫፎችንም ወደ አፍንጫዎቻቸው አቅርበዋል። +\v 18 ስለዚህ እኔ ደግሞ በመካከላቸው እንቀሳቀሳለሁ ዓይኔ አይራራም ፣አላዝንላቸውም። ወደ ጆሮዬም በታላቅ ድምፅ ቢጮኹ አልሰማቸውም አለኝ። + +\s5 +\c 9 +\p +\v 1 ከዚያም "ጠባቂዎች የሚያጠፋ መሣሪያን በእጃቸው ይዘው ወደ ከተማይቱ ይቅረቡ" ብሎ በታላቅ ድምፅ በጆሮዬ ጮኸ። +\v 2 እነሆም፥ እያንዳንዳቸው አጥፊውን መሣሪያ በእጃቸው ይዘው ስድስት ሰዎች በሰሜን አቅጣጫ ካለው ከላይኛው በር በኩል መጡ፣ በመካከላቸውም የበፍታ ልብስ የለበሰ የጸሐፊም ቀለም ቀንድ በወገቡ የያዘ አንድ ሰው ነበረ። እነርሱም ገብተው በናሱ መሠዊያ አጠገብ ቆሙ። + +\s5 +\v 3 የእስራኤልም አምላክ ክብር በበላዩ ከነበረበት ከኪሩብ ላይ ተነሥቶ ወደ ቤቱ መድረክ ሄደ። በፍታም የለበሰውን የጸሐፊውንም ቀለም ቀንድ በወገቡ የያዘውን ሰው ጠራ። +\v 4 እግዚአብሔርም "በኢየሩሳሌም ከተማ መካከል እለፍ፥ በመካከልዋም ስለ ተሠራው ርኵሰት ሁሉ በሚያለቅሱና በሚተክዙ ሰዎች ግምባር ላይ ምልክት አድርግ" አለው። + +\s5 +\v 5 እኔም እየሰማሁ ለሌሎቹ "እርሱን ተከትላችሁ በከተማይቱ መካከል እለፉ ግደሉም! ዓይናችሁ አይራራ አትዘኑም +\v 6 ሽማግሌውንና ጐበዙን ቈንጆይቱንም ሕፃናቶቹንና ሴቶቹን ፈጽማችሁ ግደሉ! ነገር ግን ምልክቱ ወዳለበት ሰው ሁሉ አትቅረቡ። ከመቅደሴም ጀምሩ!" አላቸው። በቤቱም አንጻር ባሉ ሽማግሌዎች ጀመሩ። + +\s5 +\v 7 እርሱም "ቀጥሉ! ቤቱን አርክሱ፥ አደባባዮቹንም በሬሳ" አላቸው። እነርሱም ወጥተው በከተማይቱ ላይ ጥቃት ፈጸሙ። +\v 8 ጥቃቱን እየፈጸሙ ሳሉ እኔ ብቻዬን እንደቀረሁ ሳይ በግምባሬ ተደፍቼ "ጌታ እግዚአብሔር ሆይ ወዮ! መዓትህን በኢየሩሳሌም ላይ ስታፈስስ የእስራኤልን ቅሬታ ሁሉ ታጠፋለህን?" ብዬ ጮኽሁ። + +\s5 +\v 9 እርሱም፦ "'እግዚአብሔር ምድሪቱን ትቶአታል እግዚአብሔርም አያይም!' እያሉ የእስራኤልና የይሁዳ ቤት ኃጢአት እጅግ በዝቶአል ምድሪቱም ደም፥ ከተማይቱም ዓመፅን ተሞልታለች ። +\v 10 እኔም ደግሞ ዓይኔ አትራራላቸውም አላዝንምም። ይልቁኑ መንገዳቸውን በራሳቸው ላይ እመልሳለሁ" አለኝ። +\v 11 እነሆም፥ በፍታ የለበሰው የቀለም ቀንድም በወገቡ የያዘው ሰው ተመልሶ መጣና "ያዘዝኸኝን አድርጌአለሁ" የሚል ሪፖርት አቀረበ። + +\s5 +\c 10 +\p +\v 1 ከዚያም በኪሩቤል ራስ ላይ ወደ ነበረው ጠፈር ተመለከትኩ። በላያቸው እንደ ሰንፔር ድንጋይ ያለ እንደ ዙፋን የሚመስል መልክ ተገለጠ። +\v 2 እግዚአብሔርም በፍታም የለበሰውን ሰው "በመንኰራኵሮች መካከል ከኪሩብ በታች ግባ፥ ከኪሩቤልም መካከል ካለው እሳት ፍም እጆችህን ሙላ በከተማይቱም ላይ በትነው" አለው። ሰውዬውም እያየሁት ገባ። + +\s5 +\v 3 ሰውዬውም ሲገባ ኪሩቤል በቤቱ ቀኝ በኩል ቆመው ነበር፥ ደመናም ውስጠኛውን አደባባይ ሞላው። +\v 4 የእግዚአብሔር ክብርም ከኪሩቤል ወጥቶ በቤቱ መድረክ ላይ ቆመ፤ ቤቱም በደመናው ተሞላ፥ አደባባዩም በእግዚአብሔር ክብር ፀዳል ተሞላ። +\v 5 ሁሉንም የሚችል አምላክ እንደሚናገረው ያለ ጽምፅ እንዲሁ የኪሩቤል ክንፎችን ድምፅ ክውጭው አደባባይ ሰማሁ። + +\s5 +\v 6 እግዚአብሔርም በፍታ የለበሰውን ሰው "ከመንኰራኵሮች ከኪሩቤል መካከል እሳት ውሰድ" ብሎ ባዘዘው ጊዜ ሰውዬው ገብቶ በአንደኛው መንኰራኵር አጠገብ ቆመ። +\v 7 ኪሩብም ከኪሩቤል መካከል እጁን በኪሩቤል መካከል ወዳለው እሳት ዘርግቶ ከዚያ ወሰደ፥ በፍታም በለበሰው ሰው እጅ አኖረው እርሱም ይዞ ወጣ። +\v 8 በኪሩቤልም ከክንፎቻቸው በታች የሰው እጅን መሳይ አየሁ። + +\s5 +\v 9 እኔም አየሁ፥ እነሆም፥ በኪሩቤል አጠገብ አራት መንኰራኵሮች ነበሩ አንዱ መንኰራኵር በአንዱ ኪሩብ፥ አንዱ መንኰራኵር በአንዱ ኪሩብ አጠገብ ነበረ። የመንኰራኵሮቹም መልክ እንደ ቢረሌ ድንጋይ ነበረ። +\v 10 የአራቱም መልክ አንድ ይመስል ነበር፥ መልካቸውም በመንኰራኵር ውስጥ እንዳለ መንኰራኵር ነበረ። +\v 11 ሲንቀሳቀሱም ወደየትኛውም አቅጣጫ ይሄዱ ነበር፤ ፊት ለፊት ስለሚሄዱ ሲሄዱ አይገላመጡም ነበር። ሲሄዱም አይገላመጡም ነበር። + +\s5 +\v 12 ሰውነታቸው ሁሉ ማለትም ጀርባቸው፣ እጃቸውና ክንፋቸው በዓይን ተሞልቶ ነበር፣ አራቱ መንኰራኵሮችም ዙሪያቸውን በዓይኖች ተሞልተው ነበር። +\v 13 መንኰራኵሮችም እኔ እየሰማሁ "ተሽከርካሪዎች" ተብለው ተጠሩ። +\v 14 ለእያንዳንዱም አራት አራት ፊት ነበሩት አንደኛው ፊት የኪሩብ ፊት፥ ሁለተኛውም የሰው ፊት፥ ሦስተኛው የአንበሳ ፊት፥ አራተኛውም የንስር ፊት ነበረ። + +\s5 +\v 15 ከዚያም ኪሩቤል ማለትም በኮቦር ወንዝ ያየኋቸው ህያዋን ፍጥረታት ከፍ ከፍ አሉ +\v 16 ።ኪሩቤል በተንቀሳቀሱ ጊዜ ሁሉ መንኰራኵሮቹ በአጠገባቸው ይሄዱ ነበር፤ ኪሩቤልም ከምድር ከፍ ከፍ ይሉ ዘንድ ክንፎቻቸውን ሲዘረጉ መንኰራኵሮች ደግሞ ከአጠገባቸው ፈቀቅ አይሉም ነበር። +\v 17 የህያዋኑ ፍጥረታት መንፈስ በመንኰራኵሮች ውስጥ ስለነበረ ኪሩቤል ሲቆሙ መንኮራኩሮችመ ይቆሙ ነበር፥ ከፍ ከፍ ሲሉም መንኮራኩሮቹም ከእነርሱ ጋር ከፍ ከፍ ይሉ ነበር። + +\s5 +\v 18 የእግዚአብሔርም ክብር ከቤቱ መድረክ ላይ ወጥቶ በኪሩቤል ላይ ቆመ። +\v 19 ኪሩቤልም ክንፎቻቸውን ዘረጉ እኔም እያየሁ ከምድር ከፍ ከፍ አሉ በወጡም ጊዜ መንኰራኵሮች በአጠገባቸው እንደዚያው አደረጉ። በእግዚአብሔርም ቤት በምሥራቁ በር መግቢያ ቆሙ፥ የእስራኤልም አምላክ ክብር በላያቸው ወረደ። + +\s5 +\v 20 እነኚህም በኮበር ወንዝ ከእስራኤል አምላክ በታች ያየኋቸው ህያዋን ፍጥረታት ስለነበሩ ኪሩቤልም እንደ ነበሩ አውቄ ነበር። +\v 21 ለእያንዳንዱ አራት አራት ፊትና አራት አራት ክንፍ ነበሩት፥ የሰውም እጅ አምሳያ ከክንፎቻቸው በታች ነበረ። +\v 22 ፊቶቻቸውም በኮቦር ወንዝ በራዕይ ያየኋቸውን ፊቶች ይመስሉ ነበር ፣ እያንዳንዱም አቅንቶ ወደ ፊት ይሄድ ነበር። + +\s5 +\c 11 +\p +\v 1 መንፈስም አነሣኝ ወደ ምስራቅ መውጫ ወደሚመለከት ወደ እግዚአብሔር ቤት ምሥራቅ በር አመጣኝ። እነሆም፥ በበሩ መግቢያ ሀያ አምስት ሰዎች ነበሩ፥ በመካከላቸውም የሕዝቡን አለቆች የዓዙርን ልጅ ያእዛንያንና የበናያስ ልጅ ፈላጥያን አየሁ። + +\s5 +\v 2 እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፣ "የሰው ልጅ ሆይ፥ እነዚህ ክፋትን የሚያስቡ በዚህችም ከተማ ክፉን ምክር የሚመክሩ ሰዎች ናቸው። +\v 3 እነርሱም 'ቤቶችን የምንሠራበት ዘመን አይደለም። ይህች ከተማ ድስት እኛም ሥጋ ነን' ብለዋል። +\v 4 ስለዚህ፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት ተናገርባቸው፣ ትንቢት ተናገር። + +\s5 +\v 5 የእግዚአብሔርም መንፈስ በኔ ላይ ሆኖ እንዲህ አለኝ፥ "እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ብለህ ተናገር። የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ይህን ነገር ተናግራችኋል፥ እኔም የልባችሁን አሳብ አውቃለሁ። +\v 6 በዚህች ከተማ ውስጥ ብዙ ሰዎችን ገድላችኋል ጎዳናዎችዋንም በሬሳዎቻቸው ሞልታችኋል። +\v 7 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በአየሩሳሌም ከተማ መካከልም ሬሳዎቻቸው ያኖራችኋቸው የገደላቹኋቸው ሰዎች ሥጋው ሲሆኑ፥ ይህችም ከተማ ድስቱ ናት። እናንተን ግን ከከተማዋ መካከል ተነቅላችሁ ትወጣላችሁ። + +\s5 +\v 8 ሰይፍን ፈርታችኋል እኔም ሰይፍን አመጣባችኋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ +\v 9 ከከተማይቱ መካከል አወጣችኋለሁ፥ በእንግዶችም እጅ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፥ በላያችሁም ፍርድ አመጣባችኋለሁ። +\v 10 በሰይፍ ትወድቃላችሁ በእስራኤልም ድንበር ውስጥ እፈርድባችኋለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 11 ይህች ከተማ የማብሰያ ድስት አትሆንላችሁም እናንተም በመካከልዋ ሥጋ አትሆኑም፣ እኔም በእስራኤል ድንበር ውስጥ እፈርድባችኋለሁ። +\v 12 እኔም በትዕዛዙ ያልሄዳችሁለት ፍርዱንም ያላደረግችሁለት እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። ይልቁኑ በዙሪያችሁ እንደሚኖሩት እንደ አሕዛብ ሕግ አድርጋችኋል። + +\s5 +\v 13 እንዲህም ሆነ ትንቢትም በተናገርሁ ጊዜ የበናያስ ልጅ ፈላጥያ ሞተ፣ እኔም በግምባሬ ተደፍቼ "ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ወዮ! በውኑ የእስራኤልን ቅሬታ ፈጽመህ ታጠፋለህን?" ብዬ በታላቅ ድምፅ ጮኽሁ። + +\s5 +\v 14 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ +\v 15 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ወንድሞችህ! አዎ ወንድሞችህ! ዘመዶችህ በኢየሩሳሌምም የሚኖሩ ሁሉ! 'እነርሱ ከእግዚአብሔር የራቁ ናቸው! ይህች ምድር ርስት ሆና ለእኛ ተሰጥታለች' የሚሉአቸው ናቸው። + +\s5 +\v 16 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በላቸው፣ 'ምንም እንኳ እኔ በሩቅ ወዳሉ አሕዛብ ባርቃቸውና ወደ አገሮችም ብበትናቸውም በሄዱባቸው አገሮች ለጥቂት ጊዜ ቤተ መቅደስ ሆኜላቸዋለሁ' ። +\v 17 ስለዚህም ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በላቸው 'ከአሕዛብ ዘንድ አከማቻችኋለሁ ከተበተናችሁባቸውም አገሮች እሰበስባችኋለሁ፥ የእስራኤልንም ምድር እሰጣችኋለሁ። +\v 18 ወደዚያም ይመጣሉ፥ ጸያፉንና ርኩሱንም ነገር ሁሉ ከዚያች ምድር ያስወግዳሉ። + +\s5 +\v 19 ወደኔ ሲቀርቡ አንድ ልብ እሰጣቸዋለሁ፥ በውስጣቸውም አዲስ መንፈስ አስቀምጣለሁ፤ +\v 20 ከሥጋቸውም ውስጥ ድንጋዩን ልብ አውጥቼ የሥጋን ልብ እሰጣቸዋለሁ፣ ይህም በትእዛዜም እንዲሄዱና ፍርዴንም እንዲጠብቁና እንዲያደርጉት ነው። በዚያን ጊዜ እነርሱ ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ። +\v 21 በልባቸው ወደ ጸያፍና ርኩስ ነገሮቻቸው በሚሄዱት ላይ መንገዳቸውን ወደራሳቸው እመልሳለሁ። ይህ የእግዚአብሔር አዋጅ ነው። " + +\s5 +\v 22 ኪሩቤልም ክንፎቻቸውንና በአጠገባቸው የነበሩትን መንኰራኵሮች ከፍ አደረጉ፣ የእስራኤልም አምላክ ክብር በላያቸው ላይ ነበረ። +\v 23 የእግዚአብሔርም ክብር ከከተማይቱ ውስጥ ተነሥቶ በከተማይቱ ምሥራቅ በኩል ባለው ተራራ ላይ ቆመ። + +\s5 +\v 24 መንፈስም አነሣኝ፥ ከእግዚአብሔርም ዘንድ በሆነ ራእይ ምርኮኞቹ ወዳሉበት ወደ ከላውዴዎን ምድር አመጣኝ። ያየሁትም ራእይ ከእኔ ተለየ። +\v 25 ከዚያም እግዚአብሔር ያሳየኝን ነገር ሁሉ ለምርኮኞች ነገርኳቸው። + +\s5 +\c 12 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፣ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ የምትኖረውዓመጸኞች ከመሆናቸው የተነሳ አይን እያላቸው በማያዩ ጆሮ እያላቸው በማይሰሙ በዓመፀኛ ሰዎች መካከል ነው! + +\s5 +\v 3 አንተ ግን የሰው ልጅ ሆይ፥ ለስደት ተዘጋጅ ምክንያቱም በፊታቸውም በጠራራ ፀሀይ ከስፍራህ ወደ ሌላ ስፍራ ተማርከህ እንድትሄድ አደርጋለ። ምናልባት ይህን ሲያዩ ዓመፀኛ ቤት እንደ ሆኑ ያስተውሉ ይሆናል። + +\s5 +\v 4 እቃዎችህን ሰብስበህ በቀን በፊታቸው ለስደት ተዘጋጅ፤ በማታም ጊዜ በፊታቸው ልክ ስደተኞች እንደሚያደርጉት ሂድ። +\v 5 እያዩህም ግንቡን ፈንቅለውና በእዚያ በኩል ውጣ። +\v 6 እያዩህም እቃዎችህን በጫንቃህ ላይ ተሸከምና በጨለማ ውጣ። ለእስራኤልም ህዝብ ምልክት አድርጌሃለሁና ምድሪቱን እንዳታይ ፊትህን ሸፍን። + +\s5 +\v 7 እንዳዘዘኝም አደረግሁ። በቀንም የስደት እቃዬን ወስጄ ማታ ላይ ግንቡን በእጄ ፈነቀልኩና በጨለማ አወጣቼ እያዩኝ በጫንቃዬ ላይ ተሸከምሁት። + +\s5 +\v 8 በነጋታውም የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 9 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ዓመፀኛው የእስራኤል ቤት 'የምታደርገው ምንድር ነው?' ብለው ጠየቁህን? +\v 10 አንተም ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል 'ይህ ትንቢታዊ ጉዳይ በኢየሩሳሌም የሚኖረውን አለቃና በመካከላቸውም የሚኖሩትን የእስራኤል ቤትን ሁሉ የሚመለከት ነው' በላቸው። + +\s5 +\v 11 ደግሞም፦ እኔ ምልክታችሁ ነኝ እኔ እንዳደረግሁ እንዲሁ ይደረግባቸዋል፥ እነርሱም በስደት ወደ ምርኮ ይሄዳሉ በላቸው። +\v 12 በመካከላቸውም የሚኖረው አለቃ ንብረቱን በጫንቃው ላይ ተሸክሞ ግንቡን ፈንቅሎ በጨለማ ይወጣል። ንብረታቸውን ለማውጣት ግንቡን ይፈነቅላሉ። አለቃውም በዓይኑ ምድሪቱን እንዳያይ ፊቱን ይሸፍናል። +\v 13 መረቤንም በእርሱ ላይ እዘረጋለሁ በወጥመዴም ይያዛል፥ ወደ ከለዳውያንም ምድር ወደ ባቢሎን አመጣዋለሁ ሆኖም አያያትም በዚያም ይሞታል። + +\s5 +\v 14 ሊረዱትም በዙሪያው ያሉትን ሁሉና ወታደሮቹን ሁሉ በየእቅጣጫው እበትናቸዋለሁ፣ከኋላቸውም ሰይፍ እልክባቸዋለሁ። +\v 15 በአሕዛብም መካከል በበተንኋቸው ጊዜ፥ በአገሮችም በዘራኋቸው ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። +\v 16 ነገር ግን በሚሄዱባቸውም አሕዛብ መካከል ርኵሰታቸውን ሁሉ እንዲመዘግቡ ከሰይፍና ከራብ ከቸነፈርም ጥቂቶች ሰዎችን ከእነርሱ አተርፋለሁ፣ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 17 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፣ +\v 18 "የሰው ልጅ ሆይ፥ እንጀራህን በመረበሽ ብላ ውኃህንም በመንቀጥቀጥና በኀዘን ጠጣ። + +\s5 +\v 19 ለምድሪቱም ሕዝብ 'ጌታ እግዚአብሔር ስለኢየሩሳሌም ነዋሪዎችና ስለ እስራኤል ምድር እንዲህ ይላል 'ክሚኖሩባት ሰዎች አመጽ የተንሳ ምድሪቱ ሞላዋ ስለምትጠፋ እንጀራቸውን በመረበሽ ወኃቸውንም በድንጋጤ ይጠጣሉ። +\v 20 ሰዎች የሚኖሩባቸው ከተሞች ባድማ ይሆናሉ ምድሪቱም ውድማ ትሆናለች እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ በላቸው። + +\s5 +\v 21 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ, +\v 22 "የሰው ልጅ ሆይ፥ በእስራኤል ምድር የሚነገረው'ዘመኑ ረዝሞአል ራእዩም ሁሉ ጠፍቶአል' የሚለው ምሳሌ ምንድር ነው? +\v 23 ስለዚህ እንዲህ በላቸው 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ክዚህ በኋላ የእስራኤል ህዝብ እንዳይጠቀሙበት ይህን ምሳሌ አስቀረዋለሁ ።' ከዚያም እንዲህ በላቸው "ዘመኑ ቀርቦአል እያንዳንዱ ራዕይም ይናገራል!' + +\s5 +\v 24 ምክንያቱም ከዚህ በኋላ በእስራኤል ቤት መካከል ከንቱ ራእይና ውሸተኛ ምዋርት አይሆንም። +\v 25 እኔ እግዚአብሔር ነኝና! እናገራለሁ የተናገርኩትንም ቃል እፈጽማለሁ። ነገሩ ከእንግዲህ አይዘገይም። እናንተ ዓመፀኛ ቤት ሆይ፥ በዘመናችሁ ቃሌን እናገራለሁ እፈጽመውማለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።" + +\s5 +\v 26 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል እንደገና መጣ፣ +\v 27 "የሰው ልጅ ሆይ፥ እነሆ፥ የእስራኤል ቤት 'ይህ ያየው ራእይ ገና ስለወደፊቱ ነው ስለሩቅ ዘመንም ትንቢት ይናገራል' ብለዋል። +\v 28 ስለዚህ እንዲህ በላቸው 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የምናገረው ቃል ይፈጸማል እንጂ ከዚህ በኋላ አይዘገይም' ይህ የእግዚአብሔር አዋጅ ነው!" + +\s5 +\c 13 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል እንደገና ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት በሚናገሩ በእስራኤል ነቢያት ላይ ትንቢት ተናገር፥ ከገዛ ልባቸውም ትንቢት የሚናገሩትን 'የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ! +\v 3 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ምንምን ሳያዩ የገዛ መንፈሳቸውን ለሚከተሉ ለሰነፎች ነቢያት ወዮላቸው! +\v 4 እስራኤል ሆይ፥ ነቢያትህ በምድረ በዳ እንደሚኖሩ ቀበሮች ናቸው። + +\s5 +\v 5 ፥ በእግዚአብሔርም ቀን በሰልፍ ትቆሙ ዘንድ ልትጠግኑት ወደ ፈረሰው ቅጥር አልወጣችሁም ። +\v 6 እግዚአብሔር ሳይልካቸው "እግዚአብሔር እንዲህና እንዲህ ይላል" የሚሉ ሰዎች ውሸተኛ ትንቢትንና ውሸተኛ ራዕይን አይተዋል። ያም ሆኖ ግን ቃላቸው እንደሚፈጸም ተስፋ ያደርጋሉ። +\v 7 እኔም ሳልናገር "እግዚአብሔር እንዲህ ብሎአል" የምትሉ እናንተ ከንቱ ራእይን ያያችሁ ውሸተኛንም ትንቢትን መናገራቼሁ አይደለምን? + +\s5 +\v 8 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ውሸተኛ ራእይንም ስላያችሁ ውሸት ስለተናገራችሁ ጌታ እግዚአብሔር በእናንተ ላይ የሚናገረው ይህ ነው፡ +\v 9 እጄም ከንቱ ራእይን በሚያዩ፥ የውሸት ትንቢት በሚናገሩ ነቢያት ላይ ይሆናል። እነርሱም በሕዝቤ ጉባኤ ውስጥ አይገኙም፥ በእስራኤልም ቤት መዝገብ ላይ አይጻፉም፥ ወደ እስራኤልም ምድር አይገቡም እኔም ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ! + +\s5 +\v 10 በዚህም ምክንያት ሰላም ሳይኖር "ሰላም ነው!" እያሉ ሕዝቤን መረን ሰደዋል፣ ገለባ በሌለበት ጭቃ የተመረገ ቅጥር ይገነባሉ። +\v 11 ቅጥሩን ገለባ በሌለበት ጭቃ ለሚመርጉት ሰዎች እንዲህ በላቸው 'ቅጥሩ ይወድቃል፤ የሚያሰጥም ዝናብ ይዘንባል፥ ቅጥሩኔ ለማፍረስ ታላቅም የበረዶ ድንጋይ እልካለሁ፥ እንዲያደቀውም ዐውሎ ነፋስን እልካለሁ። +\v 12 እነሆ፥ ግንቡ በወደቀ ጊዜ። የመረጋችሁት ጭቃ ወዴት አለ? አይሉአችሁምን? + +\s5 +\v 13 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል 'በመዓቴ ዐውሎ ነፋስ አመጣለሁ ፥ በቍጣዬም ዶፍ ዝናብ ይዘንባል! በመዓቴም ታላቅ የበረዶ ድንጋይ ፈጽሞ ያወድመዋል። +\v 14 ገለባም በሌለበት ጭቃ የመረጋችሁትን ቅጥር አፈርሳለሁ ወደ ምድርም እጥለዋለሁ፥ መሠረቱም ይታያል። እርሱም ይናዳል እናንተም በመካከሉ ትጠፋላችሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 15 በመዓቴም ግንቡንና ገለባ በሌለው ጭቃ የመረጉትን ሰዎችአጠፋለሁ። ግንቡም ሆነ መራጊዎቹ የሉም እላችኋለሁ። +\v 16 እነርሱም ስለ ኢየሩሳሌም ትንቢት የሚናገሩ የሰላምን ራእይ የሚያዩላት የእስራኤል ነቢያት ናቸው። ሰላምም የለም፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር" + +\s5 +\v 17 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ከገዛ ልባቸው ትንቢት በሚናገሩ በሕዝብህ ሴቶች ልጆች ላይ ፊትህን አድርግ ትንቢትም ተናገርባቸው፥ +\v 18 እንዲህም በል፣ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ነፍስን ለማጥመድ በመላ እጆቸው የጥንቆላ መከዳ ለሚሰፉ ለራሶቻቸውም የተለያየ መጠን ያላቸው ሽፋን ለሚሠሩ ሴቶች ወዮላቸው! የሕዝቤንም ነፍስ ብታጠምዱ በውኑ ነፍሳችሁን ታድናላችሁን? + +\s5 +\v 19 ውሸታችሁን ለሚሰሙት ሕዝቤ እየዋሻችሁ ለጭብጥ ገብስና ለቍራሽ እንጀራ ብላችሁ መሞት የማይገባቸውን ለመግደል በሕይወትም መኖር የማይገባቸውን በሕይወት በማኖር በሕዝቤ ፊትአርክሳችሁኛል። + +\s5 +\v 20 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ፦እነሆ፥ እኔ ነፍሳትን እንደ ወፍ በምታጠምዱባት በአስማት መተቶቻችሁ ላይ ነኝ፥ ከክንዳችሁም ወስጄ እቀደዋለሁ፥ እንደ ወፍም ያጠመዳችኋቸውን ህዝብ ነጻ አወጣለሁ። +\v 21 ሽፋኖቻችሁንም እቀድዳለሁ ሕዝቤንም ከእጃችሁ አድናለሁ፥ ከዚያም ወዲያ በእጃችሁ አይጠመዱም እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 22 እኔም እንዲያዝን የማልፈልገውን የጻድቁን ልብ በውሸታችሁ አሳዝናችኋልና፥ በተቃራኒው ደግሞ ከክፉ መንገዱ ተመልሶ በሕይወት እንዳይኖር የኃጢአተኛውን ተግባር አበረታታችኋልና +\v 23 ሕዝቤን ከእጃችሁ ስለማድን ክእንግዲህ ከንቱን ራእይ አታዩም የውሸት ትንቢትም አትናገሩም፥ ምክንያቱም እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\c 14 +\p +\v 1 ከእስራኤልም ሽማግሌዎች መካከል የተወሰኑ ሰዎች ወደ እኔ መጥተው በፊቴ ተቀመጡ። +\v 2 ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 3 የሰው ልጅ ሆይ፥ እነዚህ ሰዎች ጣዖቶቻቸውን በልባቸው አኑረዋል የበደላቸውንም መቅሠፍት በፊታቸው አቁመዋል ታዲያ እኔ ከእነርሱ ጥያቄ መቀበል አለብኝ? + +\s5 +\v 4 ስለዚህ፦ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ፦ ከእስራኤል ቤት ጣዖቶቹን በልቡ የሚያኖር፥ የበደሉንም መቅሠፍት በፊቱ የሚያቆም ሰው ሁሉ ወደ ነቢዩ በመጣ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ጣዖታቱ ብዛት እመልስለታለሁ። +\v 5 ይህንንም የማደርገው ሁሉም በጣዖቶቻቸው ምክንያት ከእኔ በጣም በራቀው በልባቸው የእስራኤልን ቤት እንደገና ለመመለስ ነው!' ብለህ ንገራቸው። + +\s5 +\v 6 ስለዚህ ለእስራኤል ቤት እንዲህ በል፣ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ንስሐ ግቡ ከጣዖቶቻችሁም ተመለሱ፥ ፊታችሁንም ከርኵሰታችሁ ሁሉ መልሱ። + +\s5 +\v 7 ከእስራኤልም ቤት፥ በእስራኤልም ዘንድ ከሚቀመጡ መጻተኞች ማንም፥ ከእኔ ተለይቶ ጣዖቶቹን በልቡ ያኖረ፥ የበደሉንም መቅሠፍት በፊቱ ያቆም ሰው ሁሉ፥ ጥያቄ ይዞ ወደ ነቢዩ ቢመጣ ፥ እኔ እግዚአብሔር እራሴ እመልስለታለሁ! +\v 8 ፊቴንም እዞርበታለሁ ከሕዝቤም መካከል አጠፋውና መቀጣጫና ምሳሌም አደርገዋለሁ ፣ በዚያን ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ! + +\s5 +\v 9 ነቢዩም ስቶ ሳለ መልዕክትን ቢናገር፥ እኔ እግዚአብሔር ያንን ነቢይ አስተዋለሁ፥ እጄንም በእርሱ ላይ እዘረጋለሁ ከሕዝቤም ከእስራኤል መካከል አጠፋዋለሁ። +\v 10 ኃጢአታቸውን ይሸከማሉ፤ የነቢዩ ኃጢአት መልዕክት ፍለጋ ወደእርሱ የሄደ ሰው ኃጢአት አንድ ይሆናል። +\v 11 በዚህም ምክንያት ከዚህ በኋላ የእስራኤል ቤት ከእኔ ርቀው አይቅበዘበዙም በኃጢአታቸውም ሁሉ አይረክሱም። እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።" + +\s5 +\v 12 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 13 የሰው ልጅ ሆይ፥ ምድር በማመፅ በእኔ ላይ ኃጢአት ብትሠራ፥ እኔም እጄን ብዘረጋባት የእንጀራዋንም በትር ብሰብር ራብን ብሰድድባት ሰውንና እንስሳውንም ከእርስዋ ባጠፋ፥ +\v 14 እነዚህም ሦስት ሰዎች፥ ኖኅ፣ ዳንኤልና ኢዮብም፥ በመካከልዋ ቢገኙ እነርሱ በጽድቃቸው ሊያዱኑ የሚችሉት የገዛ ነፍሳቸውን ብቻ ነበር፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 15 ክፉዎቹን አራዊት በምድር ባሳልፍ እነርሱም ልጆችዋን ቢያጠፉ ስለ አራዊትም ማንም እንዳያልፍባት ባድማ ብትሆን፥ +\v 16 እነዚህም ሦስት ሰዎች ቢኖሩባት፥ እኔ ሕያው ነኝና እነርሱ ብቻቸውን ይድናሉ እንጂ ወንዶችንና ሴቶች ልጆቻቸውን አያድኑም፥ ምድሪቱም ባድማ ትሆናለች፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 17 ወይም በዚያች ምድር ላይ ሰይፍ አምጥቼ። ሰይፍ ሆይ፥ በምድሪቱ ላይ እለፊ ብል፥ ሰውንና እንስሳውንም ከእርስዋ ባጠፋ፥ +\v 18 እነዚህም ሦስት ሰዎች ቢኖሩባት፥ እኔ ሕያው ነኝና እነርሱ ብቻቸውን ይድናሉ እንጂ ወንዶችንና ሴቶች ልጆቻቸውን አያድኑም፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 19 ወይም በዚያች ምድር ላይ ቸነፈር ብሰድድ ሰውንና እንስሳውንም ከእርስዋ ለማጥፋት መዓቴን በደም ባፈስስባት፥ +\v 20 ኖኅና ዳንኤል ኢዮብም ቢኖሩባት፥ እኔ ሕያው ነኝና በጽድቃቸው ነፍሳቸውን ብቻ ያድናሉ እንጂ ወንዶችንና ሴቶች ልጆቻቸውን አያድኑም፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 21 ጌታ እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል። ይልቁንስ ሰውንና እንስሳን ከእርስዋ አጠፋ ዘንድ በኢየሩሳሌም ላይ አራቱን ክፉ ፍርዶቼን፥ ሰይፍንና ራብን ክፉዎችንም አውሬዎች ቸነፈርንም፥ በመስደድ ነገሮች እንዲከፉ አደርጋለሁ። + +\s5 +\v 22 ነገር ግን፥ እነሆ! ከወንዶችና ሴቶች ልጆች ጋር የሚያመልጡ ቅሬታዎች ይተርፉላታል። እነሆ! ወደ እናንተ ይወጣሉ እናንተም መንገዳቸውንና ሥራቸውን ታያላችሁ በኢየሩሳሌምም ላይ ስላመጣሁት ቅጣት በምድሪቱም ላይ ስላመጣሁባት ነገር ሁሉ ትጽናናላችሁ ። +\v 23 መንገዳቸውንና ሥራቸውን ባያችሁ ጊዜ ያጽናኑአችኋል ያደረግሁባትንም ሁሉ በከንቱ እንዳላደረግሁባት ታውቃላችሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\c 15 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ የወይን ግንድ፥ በዱር ዛፎች መካከል ካለ ቅርንጫፎቼ ካሉት ማንኛውም ዛፍ ብልጫው ምንድር ነው? +\v 3 በውኑ ሥራ የሚሠራበትን እንጨት ከወይን ግንድ ይወስዳሉን? ወይስ ሰዎች ዕቃ የሚንጠለጠልበትን ችካል ከእርሱ ይወስዳሉን? +\v 4 እነሆ፥ ለመቃጠል በእሳት ላይ ቢጣል ፥ እሳቱም ሁለቱን ጫፎቹንና በልቶአል፥ መካከሉንም ቢያቃጥለው በውኑ ለሥራ ይጠቅማልን? + +\s5 +\v 5 እነሆ፥ ደህና ሳለ ለሥራ ካልጠቀመ፥ ይልቁንስ እሳት ከበላው እርሱም ከተቃጠለ በኋላ ለምንም አይጠቅምም! +\v 6 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በዱር ዛፎች መካከል ካሉት ዛፎች ይልቅ የወይን ግንዱን እሳት ይበላው ዘንድ እንደ ሰጠሁት፥ እንዲሁ በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን አሳልፌ እሰጣለሁ። + +\s5 +\v 7 ፊቴንም በእነርሱ ላይ አደርጋለሁ ከእሳትም ይወጣሉ፥ እሳት ግን ይበላቸዋል ፊቴንም በእነርሱ ላይ ባደረግሁ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። +\v 8 ዓመፅን አድርገዋልና ምድሪቱን ባድማ አደርጋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር!" + +\s5 +\c 16 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ ለኢየሩሳሌም ርኵሰትዋን አስታውቃት፥ +\v 3 እንዲህም በል፣ "ጌታ እግዚአብሔር ለኢየሩሳሌም እንዲህ ይላል፡ ዘርሽና ትውልድሽ ከከነዓን ምድር ነው አባትሽ አሞራዊ ነበረ እናትሽም ኬጢያዊት ነበረች። + +\s5 +\v 4 በተወለድሽ ጊዜ እናትሽ እትብትሽን አልቆረጠችም ፣ በውኃ አላጠበችሽም ወይም በጨው አላሸችሽም፣ በጨርቅም አልጠቀለለችሽም። +\v 5 ከእነዚህ ነገሮች አንዱን እንኳ ሊያደርግልሽ ማንም አልራራልሽም! በተወለድሽበት ቀን በሜዳ ላይ ተጣልሽ። + +\s5 +\v 6 እኔ ግን በአንቺ ዘንድ ባለፍሁ ጊዜ በደምሽም ውስጥ ተለውሰሽ አየሁ፤ ስለዚህም በደምሽ እንዳለሽ "በሕይወት ኑሪ!" አልሁሽ። +\v 7 በእርሻ ላይ እንዳለ ቡቃያ አሳደግሁሽ። አንቺም አደግሽ ታላቅም ሆንሽ፥ በእጅጉም አጌጥሽ። ጡቶችሽም አጐጠጐጡ ጠጕርሽም አደገ፥ ነገር ግን ዕርቃንሽን ሆነሽ፥ ተራቍተሽም ነበር። + +\s5 +\v 8 እንደገና በአንቺ ዘንድ ባለፍሁና ባየሁሽ ጊዜ፥ እነሆ፥ ጊዜሽ የፍቅር ጊዜ ነበረ እኔም መጐናጸፊያዬን በላይሽ ዘርግቼ እራቁትነትሽን ሸፈንኩ።ከዚያም ማልሁልሽ ከአንቺም ጋር ቃል ኪዳን ገባሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፥ አንቺም ለእኔ ሆንሽ። + +\s5 +\v 9 በውኃም አጠብሁሽ ከደምሽም አጠራሁሽ በዘይትም ቀባሁሽ። +\v 10 በወርቅ የተንቆጠቆጠ ልብስም አለበስሁሽ ከቆዳ የተሰራ ጫማ አደረግሁልሽ፤ በጥሩ በፍታ አስታጠቅሁሽ በሐርም ከደንሁሽ። +\v 11 በጌጥም አስጌጥሁሽ በእጅሽም ላይ አንባር በአንገትሽም ላይ ድሪ አደረግሁልሽ። +\v 12 በአፍንጫሽም ቀለበት በጆሮሽም ጕትቻ በራስሽም ላይ የክብር አክሊል አደረግሁ። + +\s5 +\v 13 በወርቅና በብር አጌጥሽ፤ ልብስሽም ጥሩ በፍታና ሐር ወርቀ ዘቦም ነበረ፤ አንቺም መልካምን ዱቄትና ማርን ዘይትንም በላሽ እጅግ በጣም ውብ ነበርሽ ከዚያም ንግሥት ሆንሽ። +\v 14 ባንቺ ላይ ካኖርኋት ከክብሬ የተነሣ ውበትሽ ፍጹም ነበረና ዝናሽ በአሕዛብ መካከል ወጣ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 15 ነገር ግን በውበትሽ ታምነሻል ስለ ዝናሽም አመንዝረሻል ምንዝርናሽንም ከመንገድ አላፊ ሁሉ ጋር አበዛሽ። የእነርሱም ንብረት ሆንሽ! +\v 16 ከልብስሽም ወስደሽ በኮረብቶች ላይ በዝንጕርጕር ልብስ ያስጌጥሻቸውን መስገጆች ለራስሽ ሠራሽ በዚያም ገለሞትሽ። እንዲህም ያለ ነገር ከአሁን በፊት አልነበረም፥ ከእንግዲህም ወዲያ አይሆንም። + +\s5 +\v 17 ከሰጠሁሽም ከወርቄና ከብሬ የተሠራውን የክብርሽን ዕቃ ወስደሽ የወንድ ምስሎች ለራስሽ አድርገሻል አመንዝረሽባቸውማል። +\v 18 ወርቀዘቦውን ልብስሽንም ወስደሽ ደረብሽላቸው፥ ዘይቴንና ዕጣኔንም በፊታቸው አኖርሽ። +\v 19 የሰጠሁሽንም እንጀራዬን ያበላሁሽንም መልካሙን ዱቄትና ዘይቱን ማሩንም ጣፋጭ ሽታ አድርገሽ በፊታቸው አኖርሽ፥ ይህ በእርግጥ ሆኖአል! ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 20 ለእኔም የወለድሻቸውን ወንዶችና ሴቶች ልጆችሽን ወስደሽ መብል ይሆኑ ዘንድ ለጣዖታቱ ሠዋሽላቸው። በውኑ የግልሙትና ተግባርሽ እንደ ቀላል የሚታይ ነገር ነውን? +\v 21 ልጆቼን አረድሽ ለእነርሱም የሚቃጠል መስዋዕት አድርገሽ አቀረብሽ +\v 22 በዚህ ሁሉ የርኵሰትና የግልሙትና ተግባርሽ ወቅት ዕርቃንሽን ተራቍተሽ በደምሽም ተለውሰሽ የነበርሽበትን የሕፃንነትሽን ወራት አላሰብሽም። + +\s5 +\v 23 ወዮ! ወዮልሽ! ይላል ጌታ እግዚአብሔር +\v 24 ከክፋትሽም ሁሉ በኋላ የጣዖት ማምለኪያ ስፍራ፥ በየአደባባዩም አጸዶችን ሠራሽ። + +\s5 +\v 25 በየመንገዱ ራስ ከፍ የማምለኪያ አጸዶችን ሠራሽ፥ ለመንገድ አላፊም ሁሉ እግርሽን በመግለጥና በርካታ የግልሙትና ተግባራት በመፈጸም ውበትሽን አረከስሽ ። +\v 26 እጅግ የሴሰኝነት ፍላጎት ካላቸው ከጐረቤቶችሽ ከግብጻውያን ጋር አመነዘርሽ፥ እኔንም ታስቈጭ ዘንድ ግልሙትናሽን አበዛሽ። + +\s5 +\v 27 ስለዚህ፥ በእጄ አደቅሻለሁ እህልንም ከአንቺ ዘንድ አጠፋለሁ። ለሚጠሉሽም ከክፉ ምኞትሽ የተነሣ ለውርደት ለሚዳርጉሽ ለፍልስጥኤም ሴቶች ልጆች ፈቃድ አሳልፌ ሰጥቼሻለሁ። +\v 28 አልጠግብ ብለሽ ከአሦራውያን ጋር ደግሞ ገለሞትሽ። ያም ሆኖ ግን አሁንም አልበቃሽም። +\v 29 እስከ ነጋዴዎች ምድር እስከ ከላውዴዎን ድረስ ግልሙትናሽን አበዛሽ። አሁንም ግን ገና አልጠገብሽም። + +\s5 +\v 30 የማታፍረውን የጋለሞታን ሥራ ሁሉ ሠርተሻልና ልብሽ ምንኛ ደካማ ነው? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ +\v 31 በየመንገዱ ራስ የምንዝርናሽን ስፍራ ሠርተሻል በየአደባባዩም ከፍ ያለውን ቦታሽን አድርገሻል። ዋጋዋን እንደምትንቅ እንደ ጋለሞታ አልሆንሽም። + +\s5 +\v 32 አንቺ ዘማዊ ሴት በባልሽ ፋንታ ሌሎች እንግዳ ሰዎች ተቀበልሽ። +\v 33 ሰዎች ለጋለሞቶች ሁሉ ዋጋ ገንዘብ ይከፍላሉ አንቺ ግን ለውሽሞችሽ ገንዘብ ትከፍያለሽ፥ ከአንቺም ጋር ለማመንዘር ከአካባቢው ሁሉ ወድ እንቺ እንዲምጡ ማባበያ ትሰጫቸዋለሽ። +\v 34 ግልሙትናሽ ከሌሎች ሴቶች ፈጽሞ የተለየ ነው፥ ምክንያቱም ማንም ከአንቺ ጋር ልትኛ ብሎ የሚጠይቅሽ የለም። ይልቁኑ አንቺ ትከፍያቸዋለሽ እንጂ የሚክፍልሽ የለም። + +\s5 +\v 35 ስለዚህ፥ ጋለሞታ ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ! +\v 36 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ከውሽሞችሽና ከአጽያፊ ጣዖታትሽ ጋር ባደረግሽው ግልሙትና አማካኝነት ክፉ ምኞትሽን በማፍሰስሽና ኀፍረተ ሥጋሽንም በመግለጥሽ እንዲሁም ለጣዖታትሽ በሰጠሻቸው በልጆችሽ ደም ምክንያት፥ +\v 37 እነሆ፥ ከእነርሱ ጋር ደስ ያለሽን የወደድሻቸውንም ውሽሞችሽና የጠላሻቸው ሁሉ ከሁሉም አቅጣጫ በአንቺ ላይ እንዲነሱ እሰበስባቸዋለሁ። እራቁትነትሽን እንዲያዩ በፊታቸው ኀፍረተ ሥጋሽን እገልጣለሁ። + +\s5 +\v 38 ስለምንዝርናሽና ደም ማፍሰስሽ እቀጣሻለሁ፥ በቁጣዬና በቅንዓቴ ደም መፋሰስን አመጣብሻለሁ። +\v 39 በእጃቸውም አሳልፌ እሰጥሻለሁ፥ የምንዝርናሽንም ስፍራ ያፈርሳሉ ከፍ ያለውንም ቦታሽን ይገለብጣሉ ልብስሽንም ይገፉሻል የክብርሽንም ጌጥ ይወስዳሉ፥ ዕርቃንሽን አድርገው ዕራቁትሽን ይተዉሻል። + +\s5 +\v 40 ህዝብንም ያስነሱብሻል በድንጋይም ይወግሩሻል፥ በሰይፋቸውም ይሰነጥቁሻል። +\v 41 ቤቶችሽንም በእሳት ያቃጥላሉ በብዙም ሴቶች ፊት ብዙ ቅጣቶችን ይፈጽሙብሻል፥ ግልሙትናሽንም አስተውሻለሁ፥ ከእንግዲህ ለእነርሱ ዋጋ አትሰጭም! +\v 42 መዓቴንም በአንቺ ላይ እጨርሳለሁ ቅንዓቴም ከአንቺ ይርቃል፥ እኔም እረካለሁ፣ከዚያ በኋላም አልቈጣም። + +\s5 +\v 43 በእንዚህ ነገርች ሁሉ ስታስቆጪኝ የሕፃንነትሽን ወራት አላሰብሽምና፥ ስለዚህ፥ እነሆ፥ እኔ እራሴ ለፈጸምሽው ጥፋት ቅጣትን በአንቺ ላይ አመጣለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፥ ከዚህ በኋላ በአስነዋሪ መንገድሽ በክፋት አትሄጂም። + +\s5 +\v 44 እነሆ፥ በምሳሌ የሚናገር ሁሉ፥ "ልክ እንደ እናቲቱ ሴት ልጂቱ እንደዛው ናት" እያለ ምሳሌ ይመስልብሻል። +\v 45 አንቺ ባልዋንና ልጆችዋን የጠላች የእናትሽ ልጅ ነሽ፤ ደግሞም ባሎቻቸውንና ልጆቻቸውን የጠሉ የእኅቶችሽ እኅት ነሽ። እናታችሁ ኬጢያዊት ነበረች አባታችሁም አሞራዊ ነበረ። + +\s5 +\v 46 ታላቂቱም እኅትሽ ከሴቶች ልጆችዋ ጋር በስተ ሰሜን የምትኖረው ሰማርያ ናት ታናሺቱም እኅትሽ ከሴቶች ልጆችዋ ጋር በስተ ምዕራብ የምትኖረው ሰዶም ናት። + +\s5 +\v 47 አንቺ ግን በመንገዳቸው አልሄድሽም እንደ ርኵሰታቸውም አላደረግሽም የእነርሱ ድርጊት ለአንቺ ጥቂት ነበረና። ይልቁኑ በመንገድሽ ሁሉ ከእነርሱ የከፋሽ ሆንሽ። +\v 48 በህያውነቴ እምላለሁ አንቺና ሴቶች ልጆችሽ ያደርጋችሁትን ክፋት ያህል ሰዶምና ሴቶች ልጆችዋ አላደረጉም! ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\v 49 እነሆ፥ የእኅትሽ የሰዶም ኃጢአት ይህ ነበረ፡ በሥራ ፈትነት የበረታች፣ ስለምንም ነገር የማይሰማት ግድ የለሽት ነበረች። የችግረኛውንና የድሀውንም እጅ አላበረታችም ። +\v 50 ትዕቢተኛ ነበረች በፊቴም ርኩስ ነገርችን አደረገች፣ እንዳየሽውም አጠፋኋቸው። + +\s5 +\v 51 ሰማርያም የኃጢአትሽን እኵሌታ እንኳ አልሠራችም ፤ አንቺ ግን ከእኅቶችሽ ይልቅ ርኵሰትሽን አበዛሽ፥ በሠራሽውም ርኵሰት ሁሉ እህቶችሽ ካንቺ እንድሚሻሉ አሳየሽ። +\v 52 አሁንም ለእኅቶችሽ ስለ ፈረድሽ እፍረትሽን ተሸከሚ ከእነርሱ የባሰ ኃጢአት ሠርተሻልና ከአንቺ ይልቅ የተሻሉ ሆነው ታይተዋል። እህቶችሽ ካንቺ እንድሚሻሉ በማሳየትሽ እፈሪ ። + +\s5 +\v 53 የሰዶምና የሴቶች ልጆችዋን ምርኮ፥ የሰማርያንና የሴቶች ልጆችዋንም ምርኮ እመልሳለሁ፤ ነገር ግን የአንቺ ምርኮ በእነርሱ መካከል ይሆናል። +\v 54 በእዚህም ነገሮች ቀመር እፍረትሽን ታሳዪአለሽ ስለ አደረግሽውም ሁሉ ታፍሪያለሽ፣ በዚህም ምክንያት ለእነርሱ መጽናኛ ትሆኚያለሽ። +\v 55 እኅቶችሽም ሰዶምና ሴቶች ልጆችዋ ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው ይመለሳሉ፥ ሰማርያና ሴቶች ልጆችዋም ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው ይመለሳሉ። ከዚያም አንቺና ሴቶች ልጆችሽ ወደ ቀድሞ ሁኔታችሁ ትመለሳላችሁ። + +\s5 +\v 56 ኩሩ በነበርሽ ጊዜ ስለ እኅትሽ ሰዶም ተናግረሽ አታውቂም ነበር፥ +\v 57 ክፋትሽ ከመገለጡ በፊትማለት ነው። አሁን ግን ለኤዶም ሴቶች ልጆችና በጎረቤቶችዋ ላሉ የፍሊስጤማውያን ልጆች ሁሉ፥ የውርደት ምሳሌ ሆነሻል። ሰው ሁሉ ይንቅሻል። +\v 58 ምንዝርነትሽንና ርኵስነትሽን ይገለጣል ፥ ይላል እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 59 ጌታ እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል። ቃል ኪዳንን ለማፍረስ መሐላን በሚንቅ ሁሉ ላይ የማደርገውን በአንቺም ላይ አደርጋለሁ። + +\s5 +\v 60 ነገር ግን በሕፃንነትሽ ወራት ከአንቺ ጋር ያደረግሁትን ቃል ኪዳኔን እኔ እራሴ አስባለሁ የዘላለምንም ቃል ኪዳን ከአንቺ ጋር እገባለሁ። +\v 61 እኅቶችሽንም ታላቂቱንና ታናሺቱን በተቀበልሽ ጊዜ መንገድሽን ታስቢያለሽ ታፍሪማለሽ። ለአንቺም ልጆች ይሆኑ ዘንድ እሰጣቸዋለሁ፥ ይህን የማደርገው ግን ስለ ቃል ኪዳንሽ አይደለም። + +\s5 +\v 62 ቃል ኪዳኔን ከአንቺ ጋር አጸናለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቂያለሽ! +\v 63 በዚህም ምክንያት ስላደረግሽውም ሁሉ ይቅር ባልሁሽ ጊዜ፥ ያደርግሽውን ሁሉ አስበሽ ታፍሪያለሽ ከዚያም ወዲያ ለምናገር አፍሽን አትከፍቺም፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\c 17 +\p +\v 1 የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፣ +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ በእንቈቅልሽ አጫውት እንዲህም ብለህ ለእስራኤል ቤት ምሳሌ ንገራቸው ፥ +\v 3 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ታላቅ ክንፍ ረጅምም ማርገብገቢያ ያለው ላባም የተሞላ፥ መልከ ዝንጕርጕር ታላቅ ንስር ወደ ሊባኖስ መጣ፥ የዛፍ ቅርንጫፍን ጫፍ ወሰደ። +\v 4 የቅርንጫፉን ጫፍ ወደ ከነዓንም ምድር ወሰደው በነጋዶችም ከተማ ተከለው። + +\s5 +\v 5 ከዚያም ምድር ዘር ወሰደ በፍሬያማ እርሻም ተከለው። በብዙም ውኃ አጠገብ እንደ አኻያ ዛፍ አኖረው። +\v 6 በበቀለም ጊዜ ቁመቱ ያጠረ አረጉም ወደ እርሱ የሚመለስ ሥሩም በበታቹ የነበረ ሰፊ ወይን ሆነ። + +\s5 +\v 7 ታላቅ ክንፍና ብዙ ላባም ያለው ሌላ ታላቅ ንስር ነበረ። እነሆም፥ ውሀ ያጠጣው ዘንድ ይህ ወይን ሥሩን ወደ እርሱ አዘነበለ አረጉንም ከተተከለበት ከመደቡ ወደ እርሱ ሰደደ። +\v 8 አረግም ያወጣ ፍሬም ያፈራ የከበረም ወይን እንዲሆን በመልካም ላይ በብዙም ውኃ አጠገብ ተተክሎ ነበር። + +\s5 +\v 9 ለህዝቡም እንዲህ በል፥ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በውኑ ይከናወንለት ይሆንን? ይደርቅስ ዘንድ፥ አዲስ የበቀለውስ ቅጠሉ ይጠወልግ ዘንድ ሥሩን አይነቅለውምን? ፍሬውንስ አይለቅመውምን? የትኛውም ጠንካራ ክንድ ወይም ብዙ ህዝብ ሥሩን ሊነቅል አይችልም። +\v 10 እነሆ፥ ከተተከል በኋላስ ይከናወንለት ይሆንን? የምሥራቅ ነፋስ ባገኘው ጊዜ ፈጽሞ አይደርቅምን? በተተከለበት መደብ ላይ ይደርቃል። + +\s5 +\v 11 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 12 "ለዓመፀኛ ቤት፥ 'የዚህ ነገር ትርጓሜ ምን እንደ ሆነ አታውቁምን? እነሆ፥ የባቢሎን ንጉሥ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፥ ንጉሥዋንና መኳንንቶችዋንም ማረከ፥ ወደ እርሱም ወደ ባቢሎን ወሰዳቸው። + +\s5 +\v 13 ከንጉሳዊያን ዘር የሆነውን ወስዶ ቃል ኪዳን ከእርሱ ጋር አደረገ አማለውም። የምድሪቱንም ኃያላን ወሰደ +\v 14 ይኸውም ቃል ኪዳኑን በመጠበቅ እንድትጸና እንጂ መንግሥቱ እንድትዋረድና ከፍ እንዳትል ነው። + +\s5 +\v 15 የኢየሩሳሌም ንጉስ ግን በእርሱ ላይ ሸፈተ ፈረሶችንና ብዙንም ሕዝብ ይሰጡት ዘንድ መልእክተኞችን ወደ ግብጽ ላከ። በውኑ ይከናወንለት ይሆንን? ይህንስ ያደረገ ያመልጣልን? ቃል ኪዳንንስ አፍርሶ ያመልጣልን? +\v 16 በህያውነቴ እምላለሁ! ባነገሠውና መሐላውን በናቀበቱ፥ ቃል ኪዳኑንም ባፈረሰበቱ ንጉሥ ምድር ይሞታል። በባቢሎን መካከል ይሞታል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 17 የባቢሎን ሠራዊት ብዙዎችን ነፍሳት ለማስወገድ አፈርን በደለደሉ ምሽግም በሠሩ ጊዜ፥ ፈርዖን ከብዙ ሠራዊቱና ከታላቁ ጉባኤው ጋር የኢየሩሳሌምን ንጉሥ በሰልፍ አይረዳውም። +\v 18 ይህም የሚሆነው መሐላውን ንቆ ቃል ኪዳኑንን በማፍረሱ ነው። ለቃል ኪዳን እጁን ዘርጋ፥ ነገር ግን እነዚህን ነገሮች አደረገ። ስለዚህ አያመልጥም። + +\s5 +\v 19 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በህያውነቴ እምላለሁ የናቀው መሐላዬን ያፈረሰስ ቃል ኪዳኔን አይደለምን? ስለዚህ ቅጣትን በርሱ ላይ አመጣለሁ! +\v 20 መረቤንም በእርሱ ላይ እዘረጋለሁ በማጥመጃ መረቤም ይያዛል። ወደ ባቢሎንም አመጣዋለሁ በእኔም ላይ ስላደረገው ዓመፅ በዚያ በእርሱ ላይ እፈርዳለሁ። +\v 21 ጭፍሮቹም ሁሉ በሰይፍ ይወድቃሉ፥ የቀሩትም ሁሉ በየአቅጣጫው ይበታተናሉ። እኔም እግዚአብሔር እንደሆንኩ ይህም እንደሚሆን እንደ ተናገርሁ ታውቃላችሁ!' + +\s5 +\v 22 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፥ 'እኔ እራሴ ከረጅሙ ዝግባ ጫፍ ላይ ቀንበጥን እወስዳለሁ ከለምለም ቅርንጫፎቹ አርቄ እተክለዋለሁ። ቀንጥቤ እኔ እራሴ በረጅምና በታላቅ ተራራ ላይ እተክለዋለሁ! +\v 23 ከፍ ባለው በእስራኤል ተራራ ላይ እተክለዋለሁ፥ ቅርንጫፎችም ያወጣል ፍሬም ያፈራል የከበረም ዝግባ ይሆናል በበታቹም በክንፍ የሚበርሩ ወፎች ሁሉ ያርፋሉ፥ በቅርንጫፎቹም ጥላ ውስጥ ጎጆአቸውን ይሰራሉ። + +\s5 +\v 24 በዚያን ጊዜ የዱር ዛፎች ሁሉ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ያውቃሉ። ረጅሙን ዛፍ ዝቅ አደርጋለሁ፥ አጭሩንም ዛፍ ከፍ አድርጋለሁ! የለመለመውንም ዛፍ አደርቃለሁ፥ የደረቀውንም ዛፍ አለመልማለሁ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ይህ እንደሚሆን ተናግሬአለሁ እኔም አድርጌዋለሁ። + +\s5 +\c 18 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 "ስለ እስራኤል ምድር፥ 'አባቶች መራራ የወይን ፍሬ በሉ፥ የልጆችም ጥርሶች ጠረሱ' ብላችሁ የምትመስሉት ምሳሌ ምንድር ነው? + +\s5 +\v 3 በህያውነቴ እምላለሁ እንግዲህ ወዲህ ይህን ምሳሌ በእስራኤል የምትናገሩብት ሁኔታ አይኖርም ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 4 እነሆ፥ ነፍስ ሁሉ የእኔ ነው! የአባት ነፍስ የእኔ እንደ ሆነች የልጅም ነፍስ የእኔ ናት! ኃጢአት የሚሰራ ሰው ይሞታል! + +\s5 +\v 5 ሰውም ጻድቅ ቢሆን ፍርድንና ቅን ነገርን ቢያደርግ፥ +\v 6 በተራራም ላይ ባሉ የጣዖት አምልኮ ስፍራ ባይበላ ዓይኞቹንም ወደ እስራኤል ቤት ጣዖታት ባያነሣ የባልንጀራውንም ሚስት ባያረክስ በወር አበባ ላይ ወዳለች ሴት ባይቀርብ + +\s5 +\v 7 ሰውንም ባያስጨንቅ ለባለ ዕዳም መያዣውን ቢመልስ የሌባ ተቀባይ ባይሆን ከእንጀራውም ለተራበ ቢሰጥ የተራቈተውንም ቢያለብስ + +\s5 +\v 8 በአራጣ ባያበድር፥ የማይገባ ትርፍን ባይወስድ፥ ፍትህን ቢያደርግ፥ በሰውና በሰው መካከልም መተማመንን ቢፈጥር +\v 9 በትእዛዜም ቢሄድ፥ እውነትንም ለማድረግ ፍርዴን ቢጠብቅ፥ ይህ ሰው ጻድቅ ነው፤ ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል! ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 10 እርሱም ቀማኛና ደም አፍሳሽ ልጅ ከዚህም ሁሉ አንዳቸውን የሚያደርገውን ቢወልድ፥ +\v 11 እርሱም ጻድቅ አባቱ የሠራውን ሁሉ ባይሠራ በተራራምላይ ባሉ የጣዖት አምልኮ ስፍራ ላይ ቢበላ የባልንጀራውንም ሚስት ቢያረክስ፥ + +\s5 +\v 12 ድሀውንና ችግረኛውንም ቢያስጨንቅ ቢቀማም መያዣውንም ባይመልስ ዓይኖቹንም ወደ ጣዖታት ቢያነሣ ወይም ርኩስን ነገር ቢያደርግ፥ +\v 13 በአራጣ ቢያበድር፥ የማይገባ ትርፍ ቢወስድ፥ በውኑ እርሱ በሕይወት ይኖራልን? በሕይወት አይኖርም! ይህን ርኵሰት ሁሉ አድርጎአልና ፈጽሞ ይሞታል ደሙም በላዩ ላይ ይሆናል። + +\s5 +\v 14 እነሆም፥ ልጅ ቢወልድ፥ እርሱም አባቱ የሠራውን ኃጢአት አይቶ ቢፈራ እንዲህም ባይሠራ፥ +\v 15 በተራራ ባሉ የጣዖት አምልኮ ስፍራዎች ላይ ባይበላ ዓይኖቹንም ወደ እስራኤል ቤት ጣዖታት ባያነሣ የባልንጀራውንም ሚስት ባያረክስ፥ + +\s5 +\v 16 ሰውንም ባያስጨንቅ መያዣውን ባይወስድ ባይቀማም ከእንጀራውም ለተራበ ቢሰጥ ለተራቈተውም ልብስን ቢያለብስ፥ +\v 17 እጁንም ድሀን ከመበደል ቢመልስ፥ በአራጣ ባያበድር የማይገባ ትርፍንም ባይወስድ፤ ፍርዴንም ቢያደርግ በትእዛዜም ቢሄድ፥ እርሱ ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል እንጂ በአባቱ ኃጢአት አይሞትም። + +\s5 +\v 18 አባቱ ግን ፈጽሞ በድሎአልና፥ ወንድሙንም ዘርፏልና፥ በሕዝቡም መካከል ክፉን ነገር አድርጎአልና እነሆ፥ እርሱ በበደሉ ይሞታል። + +\s5 +\v 19 እናንተ ግን፥ 'ልጅ የአባቱን ኃጢአት ስለ ምን አይሸከምም? ትላላችሁ። ልጅ ፍርድንና ቅን ነገርን ባደረገ ትእዛዜንም ሁሉ በጠበቀና ባደረገ ጊዜ ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል! +\v 20 ኃጢአትን ያደረገ ሰው ይሞታል። ልጅ የአባቱን ኃጢአት አይሸከምም፥ አባትም የልጁን ኃጢአት አይሸከምም። የጻድቁ ጽድቅ በራሱ ላይ ይሆናል፥ የኃጢአተኛውም ኃጢአት በራሱ ላይ ይሆናል። + +\s5 +\v 21 ኃጢአተኛውም ካደረጋት ኃጢአት ሁሉ ቢመለስ ትእዛዜንም ሁሉ ቢጠብቅ ፍርድንና ቅን ነገርንም ቢያደርግ ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል እንጂ አይሞትም። +\v 22 የበደለው በደል ሁሉ አይታሰብበትም በሠራው ጽድቅ በሕይወት ይኖራል። + +\s5 +\v 23 በውኑ ከመንገዱስ ቢመለስና በሕይወት ቢኖር እንጂ በኃጢአተኛ ሞት እደሰታለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር + +\s5 +\v 24 ጻድቁ ግን ከጽድቁ ቢመለስ ኃጢአትንም ቢሠራ ኃጢአተኛውም እንደሚያደርገው ርኵሰት ሁሉ ቢያደርግ፥ በሕይወት ይኖራልን? የሠራት ጽድቅ ሁሉ አትታሰብለትም ባደረገው ዓመፅና በሠራት ኃጢአት በዚያች ይሞታል። + +\s5 +\v 25 እናንተ ግን፥ 'የጌታ መንገድ የቀናች አይደለችም' ትላላችሁ። የእስራኤል ቤት ሆይ፥ እንግዲህ ስሙ! በውኑ መንገዴ የቀናች አይደለችምን? ይልቅስ የእናንተ መንገድ ያልቀናች አይደለችምን? +\v 26 ጻድቁ ከጽድቁ ቢመለስ፥ ኃጢአትንም በሠራ ጊዜ፥ በዚያም ቢሞት፥ እርሱ ባደረገው በደል ይሞታል። + +\s5 +\v 27 ኃጢአተኛውም ከሠራው ኃጢአት ቢመለስ ፍርድንና ቅን ነገርንም ቢያደርግ ነፍሱን ያድናል። +\v 28 አስቦ ከሠራው በደል ሁሉ ተመልሶአልና ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል እንጂ አይሞትም። + +\s5 +\v 29 ነገር ግን የእስራኤል ቤት፥ 'የጌታ መንገድ የቀናች አይደለችም!' ይላል። የእስራኤል ቤት ሆይ፥ መንገዴ የቀናች ያልሆነው እንዴት ነው? የእናንተ መንገድስ የቀናች የሆነችው እንዴት ነው? +\v 30 የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ስለዚህ በመካከላችሁ በእያንዳንዱ ሰው እንደ መንገዱ እፈርድበታለሁ! ይላል ጌታ እግዚአብሔር። ንስሐ ግቡ ኃጢአትም ዕንቅፋት እንዳይሆንባችሁ ከኃጢአታችሁ ሁሉ ተመለሱ። + +\s5 +\v 31 የበደላችሁትን በደል ሁሉ ከእናንተ ጣሉ አዲስ ልብና አዲስ መንፈስም ለእናንተ አድርጉ። የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ስለ ምን ትሞታላችሁ? +\v 32 የምዋቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ። + +\s5 +\c 19 +\p +\v 1 አንተም በእስራኤል አለቆች ላይ ይህን ሙሾ አሙሽ፥ እንዲህም በል፥ +\v 2 'እናትህ ማን ነበረች? አንበሳ ነበረች ከአንበሳ ደቦል ጋር ተጋደመች ግልገሎችዋን አሳደገች። +\v 3 ከግልገሎችዋም አንዱን ደቦል አንበሳ እንዲሆንና ጠላቶቹን የሚቆራርጥ እንዲሆን አሳደገችው። ሰዎችንም በላ። +\v 4 አሕዛብም ወሬውን ሰሙ እርሱም በወጥመዳቸው ተያዘ፥ በሰንሰለትም አድርገው ወደ ግብጽ ምድር ወሰዱት። + +\s5 +\v 5 እርስዋም ይመለሳል ብላ ብትጠብቅም ተስፋዋ እንደ ጠፋ ባየች ጊዜ፥ ከግልገሎችዋ ሌላን ወስዳ ደቦል አንበሳ እንዲሆን አሳደገችው። +\v 6 ደቦል አንበሳውም በአንበሶች መካከል ተመላለሰ ደቦል አንበሳም ሆነ ንጥቂያም ተማረ፥ ሰዎችንም በላ። +\v 7 መበለቶቻቸውን አስነወረ፥ ከተሞቻቸውንም አፈረሰ ከግሣቱም ድምፅ የተነሣ ምድሪቱና በሞላ ሰው አልባ ሆነች። + +\s5 +\v 8 አሕዛብም ከየአገሩ ሁሉ ተሰበሰቡ፤ መረባቸውንም በእርሱ ላይ ዘረጉ በወጥመዳቸውም ተያዘ። +\v 9 በሰንሰለትም አድርገው በሳጥን አድርገው ወደ ባቢሎን ንጉሥ አመጡት። ድምፁም በእስራኤል ተራሮች ላይ ከዚያ ወዲያ እንዳይሰማ ወደ አምባ አመጡት። + +\s5 +\v 10 እናትህ በውኃ አጠገብ በደምህ ውስጥ እንደ ተተከለች ወይን ነበረች። ከውኃም ብዛት የተነሣ ፍሬያማና በቅርንጫፍ የትሞላች ነበረች ። +\v 11 ለእርስዋም ብርቱዎች በትሮች ነበሩአት እነርሱም ለነገሥታት በትሮች ነበሩ። ቁመቷም በዛፎች ቅርንጫፎች መካከል ከፍ አለ። + +\s5 +\v 12 ነገር ግን በመዓት ተነቀለች ወደ መሬትም ተጣለች የምሥራቅም ነፋስም ፍሬዋን አደረቀ። ብርቱዎች ቅርንጫፎቿተሰበሩና ደረቁ፥ እሳትም በላቻው። +\v 13 አሁን በምድረ በዳ፥ በደረቅና ውሀ በሌለው መሬት ተተክላለች። + +\s5 +\v 14 ከቅርንጫፎቿ እሳት ወጥቶ ፍሬዋ በላ፥ ጠንካራ ቅርንጫፍ የለባትም የነገሥታትም በትር ሊሆን የሚችልም የለም።' ይህ ሙሾ ነው፥ የልቅሶ ዝማሬም ይሆናል። + +\s5 +\c 20 +\p +\v 1 እንዲህም ሆነ በሰባተኛው ዓመት በአምስተኛው ወር ከወሩም በአሥረኛው ቀን የእስራኤል ሽማግሌዎች እግዚአብሔርን ሊጠይቁ መጥተው በፊቴ ተቀመጡ። + +\s5 +\v 2 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 3 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ለእስራኤል ሽማግሌዎች ተናገር፥ እንዲህም በላቸው። 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔን ትጠይቁ ዘንድ መጥታችኋልን? በህያውነቴ እምላለሁ በእናንተ አልጠየቅም! ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 4 ትፈርድባቸዋለህን? የሰው ልጅ ሆይ፥ በውኑ ትፈርድባቸዋለህን? የአባቶቻቸውን ርኵሰት አስታውቃቸው! +\v 5 እንዲህም በላቸው፥ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እስራኤልን በመረጥሁበት ለያዕቆብም ቤት ዘር እጄን አንስቼ በማልሁበት ቀን በግብጽም ምድር በተገለጥሁላቸውና። እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ ብዬ በማልሁላቸው ጊዜ፥ +\v 6 በዚያ ቀን ከግብጽ ምድር በጥንቃቄ ወደመረጥኩላቸው፥ ወተትና ማር ወደምታፈስሰው፥ የምድርም ሁሉ ጌጥ ወደምትሆን ምድር እንደማወጣቸው ማልሁላቸው! + +\s5 +\v 7 እኔም፥ "ከእናንተ እያንዳንዱ ርኩስ ነገርንና የግብጽን ጣዖታት ከዓይኑ ፊት ያስወግድ። ራሳችሁን አታርክሱ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ።" አልኋቸው። + +\s5 +\v 8 እነርሱ ግን ዐመፁብኝ ሊሰሙኝም አልወደዱም። እያንዳንዱ ርኩስ ነገሮችን ከአይኑ ፊት አላስወገደም የግብጽንም ጣዖታት አልተወም በዚህም ጊዜ። በግብጽ ምድር መካከል ቍጣዬን ልፈጽምባቸው መዓቴንም ላፈስባቸው ወሰንኩ። +\v 9 ነገር ግን በመካከላቸው በሚኖሩበት ህዝብ መካከል እንዳይረክስ ስለ ስሜ ሰራሁ። ከግብጽ ምድር በማውጣት ራሴን በአይናቸው ፊት ገለጥኩላቸው። + +\s5 +\v 10 ከግብጽም ምድር አወጣኋቸው ወደ ምድረ በዳም አመጣኋቸው። +\v 11 ሰው ቢያደርገው በሕይወት የሚኖርበትን ሥርዓቴንም ሰጠኋቸው፥ ፍርዴንም አስታወቅኋቸው። +\v 12 ለራሴ የለየኋቸው እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቁ ዘንድ፥ በእኔና በእነርሱ መካከል ምልክት እንዲሆን ሰንበታቴን ሰጠኋቸው። + +\s5 +\v 13 ነገር ግን የእስራኤል ቤት በምድረ በዳ ዐመፁብኝ። በትዕዛዜም አልሄዱም፤ ይልቁኑ ሰው ቢያደርገው በሕይወት የሚኖርበትንም ፍርዴን ጣሉ። ሰንበታቴንም ፈጽመው አረከሱ፥ ስለዚህም አጠፋቸው ዘንድ ቍጣዬን በምድረ በዳ አፈስስባቸዋለሁ አልሁ። +\v 14 ነገር ግን በፊታቸው ባወጣኋቸው በአሕዛብ ፊት ስሜ እንዳይረክስ ብዬ ስለ ስሜ ሠራሁ። + +\s5 +\v 15 ወተትና ማርም ወደምታፈስሰው የምድር ሁሉ ጌጥ ወደምትሆን ልሰጣቸው ወዳሰብኩት ምድር አላመጣቸውም ብዬ በምድረ በዳ ማልሁባቸው። +\v 16 ይህን የማልኩት ልባቸው ጣዖቶቻቸውን ስለተከተሉ፥ ፍርዴንም ስለጣሉ ፥ በሥርዓቴም ስላልሄዱ፥ ሰንበታቴንም ስላረከሱ ነው። +\v 17 ነገር ግን ዓይኔ ራራችላቸው እኔም አላጠፋኋቸውም፥ በምድረ በዳም ፈጽሜ አልፈጀኋቸውም። + +\s5 +\v 18 ለወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸው በምድረ በዳ እንዲህ አልኋቸው፥ "በአባቶቻችሁ ሥርዓት አትሂዱ፤ ወጋቸውንም አትጠብቁ በጣዖቶቻቸውም አትርከሱ። +\v 19 እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ! በትእዛዜ ሂዱ ፍርዴንም ጠብቁ አድርጓትም! +\v 20 በእናንተና በእኔ መካከል ምልክት እንዲሆኑና እኔም እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደ ሆንሁ እንድታውቁ ሰንበታቴን ጠብቁ።" + +\s5 +\v 21 ነገር ግን ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸው ዐመፁብኝ። በሥርዓቴም አልሄዱም ወይም ሰው ቢፈጽመው በሕይወት የሚኖርባትን ፍርዴን አልጠበቁም። ሰንበታቴንም አረከሱ ስለዚህም በምድረ በዳ መዓቴን ላፈስባቸው ቍጣዬንም ልፈጽምባቸው ወሰንክ። +\v 22 ነገር ግን እጄን መለስሁ፥ በፊታቸውም ባወጣኋቸው በአሕዛብ ፊት ስሜ እንዳይረክስ ብዬ ስለ ስሜ ሠራሁ። + +\s5 +\v 23 ደግሞም ወደ አሕዛብ ልበትናቸው ፥ በአገሮችም መካከልም ለነቀፋ ላደርጋቸው በምድረ በዳ እጄን አንስቼ ማልሁባቸው። ፍርዴን አላደረጉምና +\v 24 ሥርዓቴንም ጥሰዋልና ሰንበታቴንም አርክሰዋልና ዓይናቸውም የአባቶቻቸውን ጣዖታቶች ተከትለዋልና ይህን ላደርግባቸው ወሰንኩ። + +\s5 +\v 25 ደግሞም መልካም ያልሆነውን ሥርዓት በሕይወት የማይኖሩበትንም ህግ ሰጠኋቸው። +\v 26 እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ እንዲያውቁ አጠፋቸው ዘንድ፥ ማኅፀን የሚከፍተውን በኩር ሁሉ በእሳት ባሳለፉ ጊዜ፥ በመባቸው አረከስኋቸው። + +\s5 +\v 27 ስለዚህ፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ለእስራኤል ቤት ተናገር፥ እንዲህም በላቸው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡ በዚህም ደግሞ አባቶቻችሁ ባደረጉት ዓመፅ አስቈጡኝ። +\v 28 እሰጣቸውም ዘንድ ወደ ማልሁላቸው ምድር ባገባኋቸው ጊዜ፥ በኮረብታ ላይ ያለውን የጣዖት ማምለኪያ ሁሉና ቅጠልማውንም ዛፍ ባዩ ጊዜ፥ በዚያ መሥዋዕታቸውን ሠዉ በዚያም የሚያስቈጣኝን ቍርባናቸውን አቀረቡ። በዚያም ደግሞ ጣፋጩን ሽታቸውን አደረጉ በዚያም የመጠጥ ቍርባናቸውን አፈሰሱ። +\v 29 እኔም፥ "እናንተ ወደ እርሱ የምትሄዱበት ኮረብታማ ሥፍራ ምንድር ነው?" አልኋቸው። እስከ ዛሬም ድረስ ስሙ ባማ ተብሎ ተጠርቶአል። + +\s5 +\v 30 ስለዚህ ለእስራኤል ቤት እንዲህ በላቸው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እንደ አባቶቻችሁ ልማድ ለምን ትረክሳላችሁ? ለምን እንደአመንዝራ የሚያጸይፍ ተግባር ታከናውናላችሁ? +\v 31 ቍርባናችሁን ስታቀርቡ፥ ልጆቻችሁንም በእሳት ስታሳልፉ፥ እስከ ዛሬ ድረስ በጣዖቶቻችሁ ትረክሳላችሁ። ታዲያ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ከእናንተስ ዘንድ እጠየቃለሁን? በህያውነቴ እምላለሁ ከእናንተ ዘንድ አልጠየቅም-ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 32 እናንተ "እንጨትና ድንጋይ እንድሚያመልኩት ወገኖች እንደ ሌሎች አሕዛብ እንሁን" ብላችሁ ያሰባችሁት ሀሳብ ይፈጸማል። + +\s5 +\v 33 በህያውነቴ እምላለሁ በበረታች እጅና በተዘረጋች ክንድ በእናንተ ላይ በፈሰሰችም መዓት እነግሥባችኋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር! +\v 34 ከአሕዛብም ዘንድ አወጣችኋለሁ ከተበተናችሁባትም አገር ሁሉ በበረታች እጅና በተዘረጋች ክንድ በፈሰሰችም መዓት እሰበስባችኋለሁ። +\v 35 ወደ አሕዛብም ምድረ በዳ አመጣችኋለሁ በዚያም ፊት ለፊት ከእናንተ ጋር እፋረዳለሁ። + +\s5 +\v 36 በግብጽ ምድረ በዳ በአባቶቻችሁ ላይ እንደፈረድኩ እንዲሁ በእናንተ ላይ እፋረዳለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 37 ከበሬም በታች አሳልፋችኋለሁ ወደ ቃል ኪዳንም እስራት አገባችኋለሁ፤ +\v 38 ከእናንተም መካከል ዓመፀኞችንና የበደሉኝን እለያለሁ። በእንግድነት ከኖሩባትም ምድር አወጣቸዋለሁ፥ ወደ እስራኤል ምድር ግን አይገቡም። እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ! + +\s5 +\v 39 ጌታ እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል። እናንተ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ እያንዳንዳችሁ ወደየጣዖቶቻችሁ ሂዱ፥ ከዚህም በኋላ እኔኔ መስማት ካልፈለጋችሁ እነርሱን አምልኩ። ነገር ግን ከእንግዲህ ወዲህ በቍርባናችሁና በጣዖቶቻችሁ ቅዱሱን ስሜን አታረክሱም። + +\s5 +\v 40 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል- በቅዱሱ ተራራዬ፥ ከፍ ባለው በእስራኤል ተራራ ላይ፥ በዚያ የእስራኤል ቤት ሁሉ ሁላቸው በምድራቸው ያመልኩኛል። በዚያም ቍርባናችሁን በኵራታችሁንም የቀደሳችሁትንም ነገር ሁሉ በደስታ እቀበላለሁ። +\v 41 ከአሕዛብም ዘንድ ባወጣኋችሁ ጊዜ ከተበተናችሁባትም አገር ሁሉ በሰበሰብኋችሁ ጊዜ እንደ ጣፋጭ ሽታ እቀበላችኋለሁ፥ በአሕዛብም ፊት እቀደስባችኋለሁ። + +\s5 +\v 42 ለአባቶቻችሁም እሰጣት ዘንድ ወደ ማልሁላቸው ምድር ወደ እስራኤል አገር ባገባኋችሁ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። +\v 43 በዚያም የረከሳችሁባትን መንገዳችሁንና ሥራችሁን ሁሉ ታስባላችሁ ስለ ሠራችሁትም ክፋት ሁሉ ራሳችሁን ትጸየፋላችሁ። +\v 44 ስለዚህም የእስራኤል ቤት ሆይ፥ እንደ ክፉ መንገዳችሁና እንደ ርኩስ ሥራችሁ ሳይሆን ስለ ስሜ ብዬ ይህን ባደረኩላችሁ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\v 45 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 46 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን ወደ ደቡብ አቅና በደቡብ ላይ ተናገር፤ በኔጌብ ዱር ላይ ትንቢት ተናገር +\v 47 ለኔጌብም ዱር፥ 'የእግዚአብሔርን ቃል ስማ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በአንተ ውስጥ እሳት አነድዳለሁ። በውስጥህም ያለውን የለመለመውንና የደረቀውን ዛፍ ሁሉ ይበላል። የሚንበለበለው እሳትም አይጠፋም፤ ከደቡብም ጀምሮ እስከ ሰሜን ድረስ ያለው ገጽታ ሁሉ ይቃጠላል። + +\s5 +\v 48 እሳቱን ስለኩሰውና ሳይጠፋ በሚነድበት ጊዜ ሥጋ ለባሽ ሁሉ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ያያል።'" +\v 49 እኔም፥ "ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ወዮ! እነርሱ ስለ እኔ፥ "ይሄ ምሳሌን ብቻ ተናጋሪ አይደለም እንዴ?" ይላሉ አልሁ። + +\s5 +\c 21 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን ወደ ኢየሩሳሌም አቅና በመቅደሶችም ላይ ተናገር፤ በእስራኤልም ምድር ላይ ትንቢት ተናገር። +\v 3 ለእስራኤልም ምድር እንዲህ በል፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በእናንተ ላይ ነኝ፥ ሰይፌንም ከሰገባው እመዝዘዋለሁ፥ ጻድቁንና ክፉውንም ከእናንተ ዘንድ አጠፋለሁ። + +\s5 +\v 4 እኔም ጻድቁንና ክፉውን ከእናንተ ዘንድ ስለማጠፋ፥ ሰይፌ ከደቡብ ጀምሮ እስከ ሰሜን ድረስ ባለ በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ ከሰገባው ይመዘዛል። +\v 5 ሥጋ ለባሹም ሁሉ እኔ እግዚአብሔር ሰይፌን ከሰገባው እንደ መዘዝሁ ያውቃል፥ ስይፌም ከእንግዲህ አይመለስም! + +\s5 +\v 6 ስለዚህም፥ አንተ የሰው ልጅ ሆይ፥ አልቅስ ወገብህን በማጕበጥ በፊታቸው ምርር ብለህ አልቅስ። +\v 7 እነርሱም 'ስለ ምን ታለቅሳለህ?' ብለው ይጠይቁሀል፥ አንተም እንዲህ ትላቸዋለህ፥ 'ስለሚምጣው ክፉ ዜና ነው፥ ምክንያቱም ልብ ሁሉ ይቀልጣል፥ እጆችም ሁሉ ይዝላሉ፥ ነፍስም ሁሉ ትደክማለች፥ ጉልበትም እንደ ውኃ ይፈስሳል። እነሆ፥ ይመጣል ይፈጸምማል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር'" + +\s5 +\v 8 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 9 የሰው ልጅ ሆይ፥ 'እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ብለህ ትንቢት ተናገር ሰይፍ! ሰይፍ! የተሳለና የተወለወለ ሰይፍ በል። + +\s5 +\v 10 ለታላቅ ግድያ ተስሎአል! እንደመብረቅም እንዲያብረቀርቅ ይወለወላል! በልጄን በትረ መንግስት ደስ ሊለን ይገባልን? የሚመጣው ስይፍ የዚህ አይነቱን በትር ይጠላል። +\v 11 ሰይፉም እንዲወለወልና በእጅ እንዲያዝ ይሰጣል! ሰይፉ የትሳል ነው! ለገዳይም ሊስጥ ተወልውሎ ተዘጋጅቷል!' + +\s5 +\v 12 የሰው ልጅ ሆይ፥ ሰይፉ እየመጣ ያለው በሕዝቤ ላይ ነውና፥ ለሰይፉም የሚሰጡት የእስራኤል አለቆች ሁሉ ናቸውና ለእርዳታ ተጣራ፥ አልቅስ! ሕዝቤ ነበሩና ስለዚህ ጭንህን በምሬት ጽፋ! +\v 13 ፈተና ደርሶአል፥ በትረ መንግስት ቢጸና ምን ዋጋ አለው? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 14 ስለዚህ፥ አንተ የሰው ልጅ፥ ትንቢት ተናገር፥ እጅህን አጨብጭብ ሰይፍ ለሶስተኛ ጊዜ ጥቃት ይፈጽማልና! ለሚታረዱ የተዘጋጅ ስይፍ! ሰውነታቸውን ሁሉ ሊወጋ ለሚታረዱ ለብዙዎች ሰዎች የተመደበ ሰይፍ ነው! + +\s5 +\v 15 ልባቸው እንዲቀልጥ መሰናክላቸውም እንዲበዛ የሚገድለውን ሰይፍ በበሮቻቸው ሁሉ ላይ አድርጌአለሁ! ወዮ! እንድመብረቅ ሆኗል እንዲገድልም ነጻ ተለቋል። +\v 16 ሰይፍ ሆይ ተዘጋጅ! ስለትህ ወደፈቀደው ወደ ቅኝም ወደ ግራም ምታ። +\v 17 እኔ ደግሞ በእጄ አጨበጭባለሁ መዓቴንም እፈጽማለሁ! እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ።" + +\s5 +\v 18 የእግዚአብሔርም ቃል እንደገና ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 19 "አንተም የሰው ልጅ ሆይ፥ የባቢሎን ንጉሥ ሰይፍ ይመጣ ዘንድ ሁለት መንገዶችን አድርግ። ሁለቱም መንገዶች ከአንድ ምድር ይነሳሉ፥ የመንገድ ምልክቱም አንደኛው መንገድ ወደ ከተማ እንድሚወስድ ያሳያል። +\v 20 አንዱ መንገድ የባቢሎን ጦር ወደ አሞናዊያን ከተማ ወድ ረባት እንድሚወስድ አመልክት። ሌላኛው መንገድ ወደ ይሁዳ ወደ ተመሸገች ወደ ኢየሩሳሌም እንድሚወስድ አመልክት። + +\s5 +\v 21 የባቢሎን ንጉሥ የጥንቆላ ምሪት ለማግኘት በመንታ መንገድ መታጠፊያ ላይ ይቆማል። ፍላጾችን ይወዘውዛል፥ ከጣዖታቱም ምሪት ይጠይቃል። ጉበትም ይመለከታል። +\v 22 የቅጥሩን ማፍረሻ ያደርግ ዘንድ፥ አፍንም በጩኸት ይከፍት ዘንድ፥ በውካታም ድምፅን ከፍ ያደርግ ዘንድ፥ የቅጥሩን ማፍረሻ በበሮች ላይ ያደርግ ዘንድ፥ አፈርን ይደለድል ዘንድ፥ ምሽግም ይሠራ ዘንድ የኢየሩሳሌም ዕጣ በቀኝ እጁ ውስጥ ነበረ። +\v 23 በኢየሩሳሌም ላሉ ለባቢሎናዊያን መሐላን ማሉ ዓይን ፊት የሐሰት ምዋርት ይመስላል፥ ነገር ግን ንጉሱ እንዲያዙ ለማድረግ ስምምነታችሁን አፍርሳችኋል ብሎ ይከሳቸዋል። + +\s5 +\v 24 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ኃጢአታችሁን እንዳስብ ስላደርጋችሁኝ መተላለፋችሁ ይገለጣል! ኃጢአታችሁም በሥራችሁ ሁሉ ይታያል! በዚህም ምክንያት በጠላቶቻችሁ እጅ እንደተያዛችሁ ስውን ሁሉ ታሳስባላችሁ! + +\s5 +\v 25 አንተም የምትቀጣበት ቀን የደረስብህ ፥ አመጻ የማድረጊያ ዘመን ያበቃብህ፥ አመጸኛና ክፉ የእስራኤል አለቃ ሆይ፥ +\v 26 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ መጠምጠሚያውን አውልቅ፥ ዘውዱንም ከራስህ ላይ አንሳ! ከእንግዲ ነገሮች እንደነበሩ አይቀጥሉም! የተዋረደውን ከፍ አድርግ፥ ከፍ ያለውንም አዋርድ። +\v 27 ባድማ፥ ባድማ፥ ሁሉንም ባድማ አደርጋለሁ! የሚገባው ሰው እስኪመጣና ለእርሱ እስከምሰጠው ድረስ ንግስና ከእንግዲህ አይኖርም። + +\s5 +\v 28 አንተም የሰው ልጅ ሆይ፥ 'ጌታ እግዚአብሔር ስለሚመጣባቸው ውርደት ለአሞን ልጆች እንዲህ ይላል፡ ሰይፍ፥ ሰይፍ ተመዟል! ለማጥፋትና ለመግደል ተስሏል፤ እንደመብረቅም ያብለጨልጫል! +\v 29 ነቢያት ባዶ ራዕይ እያዩልህና ምዋርት እያሟረቱልህ ሳለ ይህ ሰይፍ ሊገደሉ ባሉት የሚቀጡበት ቀን በደረሰባቸው የእመጽ ዘመናቸው ባበቃባቸው ሰዎች አንገት ላይ ያርፋል። + +\s5 +\v 30 ሰይፉን ወደ ሰገባውም መልሰው። በተፈጠርህበት ስፍራ በተወለድህባትም ምድር እፈርድብሃለሁ! +\v 31 ቍጣዬንም አፈስስብሃለሁ! የመዓቴም እሳት አናፋብሃለሁ፥ በማጥፋት ለተካኑ ለጨካኞች ሰዎች እጅ አሳልፌ እሰጥሃለሁ! + +\s5 +\v 32 ለእሳት ማገዶ ትሆናለህ! ደምህም በምድሪቱ መካከል ይፈሳል፥ መታሰቢያም አይኖርህም፥ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና። + +\s5 +\c 22 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 "አንተም የሰው ልጅ ሆይ፥ ትፈርዳለህን? ደም በምታፈስስ ከተማ ላይ ትፈርዳለህን? ርኵሰትዋን ሁሉ አስታውቃት። +\v 3 እንዲህም ልትላት ይገባል፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡ ይህች ጊዜዋ እንዲደርስ በመካከልዋ ደምን የምታፈስ፤ እንድትረክስም ጣዖታትን የምታደርግ ከተማ ናት! + +\s5 +\v 4 ስላፈሰስሽው ደም በደለኛ ነሽ ፥ ባደረግሽውም ጣዖታት ረክሰሻል! ቀንሽን አቀረብሽ ዘመንሽንም አሳጠርሽ። ስለዚህ ለአሕዛብ መሰደቢያ ለአገሮችም ሁሉ መሳለቂያ አደርግሻለሁ። +\v 5 አንቺ ስምሽ የረከሰ ግራ መጋባት የሞላብሽ ሆይ፥ በቅርብም በሩቅም ያሉ ይሳለቁብሻል። + +\s5 +\v 6 እነሆ፥ የእስራኤል አለቆች እያንዳንዳቸው በኃይላቸው መጠን ደም ያፈስሱ ዘንድ በአንቺ ውስጥ ነበሩ። +\v 7 በውስጥሽ አባቶችንና እናቶችም አቃለሉ፥ በመካከልሽ በመጻተኛው ላይ በደልን አደረጉ። በአንቺ ውስጥ ድሀ አደጉንና መበለቲቱን አስጨነቁ። +\v 8 ቅዱሳቴንም ናቅሽ ሰንበታቴንም አረከስሽ! +\v 9 ደምን ያፈስሱ ዘንድ ቀማኞች ሰዎች በአንቺ ውስጥ ነበሩ በተራሮችም ላይ በሉ። በመካከልሽ ክፋትን አደረጉ። + +\s5 +\v 10 በአንቺ ውስጥ የአባቶቻቸውን ኀፍረተ ሥጋ ገለጡ በአንቺም ውስጥ በወር አበባ ላይ ያለችን ሴት አዋረዱ። +\v 11 በባልንጀራቸው ሚስቶች ጋር ርኵሰትን ያደርጉ፥ የልጆቻአውን ሚስቶች ያረከሱ፥ የገዛ አባቶቻቸውን ሴት ልጆች እህቶቻችውን ያስነወሩ፥ እንዲህ ያሉ ስዎች ሁሉ በአንቺ ውስጥ አሉ። +\v 12 በአንቺ ውስጥ ደምን ለማፍሰስ ጉቦን ይቀብላሉ። አንቺም አራጣና አላስፈላጊ ትርፍ ወስደሻል፥ ጎረቤቶችሽን በጭቆና ጎዳሻቸው ፥ እኔንም ረሳሽኝ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\v 13 ስለዚህ፥ እነሆ፥ ያለቅንነት የሰበሰብሽውን ሀብት በመካከልሽ ያለውን ደም ማፍስስ በእጄ እቀጣለሁ። +\v 14 በውኑ እኔ ይህን በማደርግብሽ ወራት ልብሽ ይታገሣልን? ወይስ እጅሽ ትጸናለችን? እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ አደርገውማለሁ። +\v 15 ወደ አሕዛብም እበትንሻለሁ ወደ አገሮችም እዘራሻለሁ። በዚህ መንገድ ርኵሰትሽን ከአንቺ ዘንድ አጠፋለሁ። +\v 16 በአሕዛብም ፊት አንቺ የረከሽ ትሆኚያለሽ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቂአለሽ። + +\s5 +\v 17 ቀጥሎም የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 18 የሰው ልጅ ሆይ፥ የእስራኤል ቤት ለእኔ እንደ ዝቃጭ ሆኑብኝ። እነርሱ ሁሉ በእንቺ ውስጥ የመዳብና የቆርቆሮ ፥ የብረትና የእርሳስ ተረፍ ምርት ናቸው። እነርሱ በማቅለጫ ውስጥ የብር ዝቃጭ ናቸው። +\v 19 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሁላችሁ ዝቃጭ ሆናችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ በኢየሩሳሌም ውስጥ እሰበስባችኋለሁ። + +\s5 +\v 20 እንዲያቀልጡት እሳት ያናፉበት ዘንድ ብርንና መዳብን ብረትንና እርሳስን ቈርቈሮንም በከውር እንደሚሰበስቡ፥ እንዲሁ አቀልጣችኋለሁ። ስለዚህ በቍጣዬና በመዓቴ እሰበስባችኋለሁ፥ በዚያም ውስጥ እጨምራችኋለሁ እሳትም አናፋባችኋለሁ አቀልጣችሁማለሁ። +\v 21 ስለዚህም አሰበስባችሁማለሁ የመዓቴንም እሳት አናፋባችኋለሁ በውስጡም ትቀልጣላችሁ። +\v 22 ብርም በማቅለጫ ውስጥ እንደሚቀልጥ፥ እንዲሁ በውስጧ ትቀልጣላችሁ እኔም እግዚአብሔር መዓቴን እንዳፈሰስሁባችሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 23 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 24 የሰው ልጅ ሆይ እንዲህ በላት 'አንቺ ያልነጻሽ ምድር ነሽ። በቍጣ ቀን ዝናብ የለም! +\v 25 በውስጥዋ ያሉ ነቢያት እንደሚጮኽና እንደሚናጠቅ አንበሳ አንድ ሆነው ተማምለው ህይወት ያጠፋሉ፥ ከፍ ያለ ብልጥግና ይወስዳሉ! በውስጥዋም መበለቶችን ያበዛሉ! + +\s5 +\v 26 ካህናቶችዋም ሕጌን አቃለዋል ቅድሳቴንም አርክሰዋል። ቅዱስ በሆነና ቅዱስ ባልሆነ መካከልም አይለዩም፥ በንጹሕና በርኩስ መካከል ያለውን ልዩነት አያስተምሩም። ፊታቸውንም ከሰንበታቴ መለሱ እኔም በመካከላቸው ረከስሁ። +\v 27 በውስጥዋ ያሉ አለቆችዋ እንደሚናጠቁ ተኵላዎች ናቸው። የስስትን ትርፍ ለማግኘት ሲሉ ደምን ያፈሳሉ ህይወትንም ያጠፋሉ። +\v 28 እግዚአብሔርም ሳይናገር ነቢያቶችዋ፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል" እያሉ ከንቱን ራእይ በማየት የሐሰትንም ምዋርት ለእነርሱ በማምዋረት ያለ ገለባ በጭቃ ይመርጓቸዋል። + +\s5 +\v 29 የምድሪቱም ሕዝብ በማስፈራራት ግፍ አደረጉ ዘረፋ ፈጸሙ፥ ድሆችንና ችግረኞችን አስጨነቁ፥ ያለ ፍትህ መጻተኛውንም በደሉ። + +\s5 +\v 30 ቅጥርን የሚጠግንን፥ ምድሪቱንም እንዳላጠፋት በፈረሰበት በኩል በፊቴ የሚቆምላትን ሰው በመካከላቸው ፈለግሁ፥ ነገር ግን አንድም ሰው አላገኘሁም። +\v 31 ስለዚህ ቍጣዬን አፈስባቸዋልሁ፥ በመዓቴም እሳት አጠፋቸዋለሁ መንገዳቸውንም በራሳቸው ላይ እመልሳለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።" + +\s5 +\c 23 +\p +\v 1 የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ የአንዲት እናት ልጆች የሆኑ ሁለት ሴቶች ነበሩ። +\v 3 በግብጽ አገር በኰረዳነታቸው ዕድሜ አመነዘሩ በዚያ ገለሞቱ። በዚያ ጡቶቻቸው ምዋሸሹ በዚያም የድንግልናቸው ጡቶች ተዳበሱ። +\v 4 ስማቸውም የታላቂቱ ኦሖላ የታናሽ እኅትዋም ኦሖሊባ ነበረ። ለእኔም ሆኑ ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለዱ። ኦሖላ ሰማርያ ናት ኦሖሊባ ደግሞ ኢየሩሳሌም ናት። + +\s5 +\v 5 ኦሖላም የእኔ ሆና እያለ ገለሞተችብኝ፤ ውሽሞችዋንም ኃያላኑን ጎረቤቶችዋን አሦራውያንን በሴሰኝነት ተከተለቻቸው። +\v 6 እነርሱም ሰማያዊ ሐር የለበሱ አለቆችና ሹማምቶች፥ መልከ መልካሞች ጐበዛዝት፥ በፈረስ ላይ የሚቀመጡ ፈረሰኞች ነበሩ። +\v 7 ስለዚህ ራሷን ለተመረጡ ለአሦር ሰዎች ሁሉ ለግልሙትና ሰጠቻቸው ፥ በሴሰኝነት በተከተለቻቸውም ጣዖቶቻቸው ሁሉ ረከሰች። + +\s5 +\v 8 በግብጽም የነበረውን ግልሙትናዋን አልተወችም በዚያ በኰረዳነትዋ ጊዜ ከእርስዋ ጋር ተኝተው ነበር፥ የድንግልናዋንም ጡቶች ዳብሰው ነበር፥ ግልሙትናቸውንም አፍስሰውባት ነበር። +\v 9 ስለዚህ በፍቅር በተከተለቻቸው በውሽሞችዋ በአሦራውያን እጅ አሳልፌ ሰጠኋት። +\v 10 እነርሱም ኅፍረተ ሥጋዋን ገለጡ ወንዶችና ሴቶች ልጆችዋንም ማርከው ወሰዱ፥ እርስዋንም በሰይፍ ገደሉ በሌሎች ሴቶች ዘንድ መተረቻ ሆነች ስለዚህም ፈረዱባት። + +\s5 +\v 11 እኅትዋም ኦሖሊባ ይህን አየች ሆኖም ከእርስዋ ይልቅ በሴሰኝነቷ በረታች፥ ግልሙትናዋም ከእኅትዋ ግልሙትና ይልቅ በዛ። +\v 12 አለቆችንና ሹማምቶችን ጎረቤቶችዋን ጌጠኛ ልብስ የለበሱትን በፈረሶች ላይ የሚቀመጡትን ፈረሰኞች፥ ሁሉም መልከ መልካሞችን ጐበዛዝት አሦራውያንን በሴሰኝነት ተከተለቻቸው። +\v 13 የረከሰችም እንደ ሆነች አየሁ። የሁለቱም አእህትማማቾች ሁኔታ አንድ ነው። + +\s5 +\v 14 ግልሙትናዋንም አበዛች! በቀይ ቀለምም የተሳለውን የከለዳውያንን ስዕል፥ በግድግዳ ላይ የተሳሉትን ሰዎች አየች። +\v 15 በወገባቸው ዝናር የታጠቁ ራሳቸውንም በቀለማዊ መጠምጠሚያ የጠመጠሙ ነበሩ! ሁሉም የከለዳዊያን ተወላጆችና የሠረገላ አዛዦች ይመስሉ ነበር። + +\s5 +\v 16 ባየቻቸውም ጊዜ ለክፉ ተመኘቻቸው፥ ወደ ከላውዴዎን ምድር ወደ እነርሱ መልእክተኞችን ላከች። +\v 17 የባቢሎንም ሰዎች ወደ እርስዋ ወደ ሴሰኝነት መኝታ መጡ በግልሙትናቸውም አረከሱአት እርስዋም ከእነርሱ ጋር ረከሰች በውርደትም ከእነርሱ ተለየች። + +\s5 +\v 18 ግልሙትናዋንም ገለጠች ኅፍረተ ሥጋዋንም አሳየች ነፍሴም ከእኅትዋ እንደ ተለየች እንዲሁ ነፍሴ ከእርስዋ ተለየች። +\v 19 ነገር ግን በግብጽ ምድር የገለሞተችበትን የኰረዳነትዋን ዘመን በማሰላሰል ግልሙትናዋን አበዛች። + +\s5 +\v 20 የወንድ ብልቶቻቸው እንደ አህዮች የወንድ ዘራቸውም እንደ ፈረሶች ዘር የሆነውን ውሽሞቿን በሴሰኝነት ተከተለቻቸው። +\v 21 ስለ ኰረዳነትሽ ምክንያት ግብጻውያን ጡቶችሽን የዳበሱበትን ጊዜ የኰረዳነትሽን ሴሰኝነት ተመኘሽ። + +\s5 +\v 22 ስለዚህ፥ ኦሖሊባ ሆይ፥ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል 'የተለየሻቸውን ውሽሞችሽን አስነሣብሻለሁ! ከሁሉም አቅጣጫ በአንቺ ላይ አመጣቸዋለሁ! +\v 23 እነርሱም የባቢሎን ሰዎች ከለዳውያንም ሁሉ፥ ፋቁድ፥ ሱሔ፥ ቆዓ፥ ከእነርሱም ጋር አሦራውያን ሁሉ፥ መልከ መልካሞች ጐበዛዝት፥ አለቆችና ሹማምቶች ሁሉ፥ መሳፍንቶችና አማካሪዎች ሁሉ፥ በፈረስ ላይ የተቀመጡ ናቸው። + +\s5 +\v 24 በመሣሪያና በሰረገላ በመንኰራኵርም በብዙ ሠራዊትም ይመጡብሻል! ታላላቅና አነስተኛ ጋሻና ራስ ቍርም ይዘው በዙሪያሽ ይዘጋጁብሻል! እንዲቀጡሽ እድልን እሰጣቸዋለሁ፥ በተግባራቸውም ይቀጡሻል! +\v 25 ቅንዓቴንም በአንቺ ላይ ስለማደርግ በመዓትም ስለሚገናኙሽ አፍንጫሽንና ጆሮሽንም ከአንቺ ይቈርጣሉ፥ ከአንቺም የቀረ በሰይፍ ይወድቃል ወንዶችና ሴቶች ልጆችሽንም ማርከው ይወስዳሉ፥ ከአንቺም የቀረውን እሳት ትበላቸዋለች! + +\s5 +\v 26 ልብስሽንም ይገፍፉሻል ጌጣጌጥሽንም ይወስዳሉ! +\v 27 አሳፋሪ ባህሪሽን፥ ከግብጽ ምድር ያመጣሽውን ግልሙትናሽንም ከአንቺ አስወግዳለሁ። ዓይንሽንም ወደ እነርሱ በናፍቆት አታነሺም ግብጽንም ከዚያ ወዲያ አታስቢም። + +\s5 +\v 28 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፥ 'እነሆ፥ በጠላሻቸው እጅ፥ በተለየሻቸውም እጅ አሳልፌ እሰጥሻለሁ! +\v 29 እነርሱም በጥላቻ ይገናኙሻል፥ ንብረትሽን ሁሉ ይወስዳሉ፥ ዕራቁትሽንና ዕርቃንሽን ይተዉሻል። የግልሙትናሽም ነውር፥ ሴሰኝነትሽና ግልሙትናሽም ሁሉ ይገለጣል። + +\s5 +\v 30 ከአሕዛብ ጋር ስላመነዘርሽ በጣዖቶቻቸውም ስለ ረከስሽ ይህ ነገር ይደርስብሻል። +\v 31 በእኅትሽ መንገድ ሄደሻል ስለዚህ የቅጣት ጽዋዋን በእጅሽ እሰጥሻለሁ። + +\s5 +\v 32 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ 'የጠለቀውንና የሰፋውን ብዙም የሚይዘውን የእኅትሽን ጽዋ ትጠጪአለሽ መሳቂያና መሳለቂያም ትሆኛለሽ! + +\s5 +\v 33 በእኅትሽ በሰማርያ ጽዋ፥ በድንጋጤና በጥፋት ጽዋ፥ በስካርና በውርደት ትሞያለሽ! +\v 34 ትጠጪዋለሽ ትጨልጪውማለሽ መጠጫውንም ትሰባብሪዋለሽ በስብርባሪውም ጡትሽንም ትሸነትሪዋለሽ እኔ ተናግሬአለሁና፥ ይላል እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 35 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ 'ረስተሽኛልና፥ ወደ ኋላሽም ጥለሽኛልና አንቺ ደግሞ የሴሰኝነትሽንና የግልሙትናሽን ውጤት ተሸከሚ። + +\s5 +\v 36 እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ በኦሖላና በኦሖሊባ ትፈርዳለህን? እንግዲያውስ አሳፋሪ ተግባራቸውን አስታውቃቸው +\v 37 አመንዝረዋልና፥ ደምም በእጃቸው አለና! ከጣዖቶቻቸውም ጋር አመንዝረዋልና፥ ለእኔም የወለዱአቸውን ልጆቻቸውን ለእሳት መቃጠል አሳልፈዋቸዋልና። + +\s5 +\v 38 ይህን በእኔ ላይ ማድረጋቸውን ቀጥለዋል፡ በዚያ ቀን መቅደሴን አርክሰዋል ሰንበታቴንም ሽረዋል! +\v 39 ልጆቻቸውንም ለጣዖቶቻቸው በሠዉበት በዚያው ቀን ያረክሱት ዘንድ ወደ መቅደሴ ገቡ! እነሆም፥ በቤቴ ውስጥ ያደረጉት ይህ ነው። + +\s5 +\v 40 ደግሞ ከሩቅም ወደሚመጡ ሰዎች መልእክተኛ ልከሻቸዋል። እነርሱም መጥተዋል! እነሆም መጡ፥ አንቺም ታጠብሽና ዓይኖችሽን ትኩለሽ አጊጠሽም ጠብቅሻቸው። +\v 41 ከፊት ለፊቱ ገብታ በተዘጋጀበት በክብር አልጋ ላይ ተቀመጥሽ፥ ዕጣኔንና ዘይቴንም አኖርሽበት። + +\s5 +\v 42 በጭንቀት የተሞላ የህዝብ ድምፅ በአንቺ ዘንድ ነበረ፥ ሰካራሞችም ከሌሎች ምናምንቴ ሰዎች ጋር ከምድረ በዳ መጡ። በእጅሽም ላይ አንባር በራስሽም ላይ የተዋበ አክሊል አደረጉ። + +\s5 +\v 43 እኔም በምንዝር ስለሻገተችው ፥ 'አሁን ከእርስዋ ጋር ያመነዝራሉ እርስዋም ከእነርሱ ጋር ታመነዝራለች' አልሁ።' +\v 44 ወደ ጋለሞታም እንደሚገቡ ወደ እርስዋ ገቡ እንዲሁ ይሴስኑ ዘንድ በግልሙትና በደለኛ ወደሆኑት ወደ ኦሖላና ወደ ኦሖሊባ ገቡ። +\v 45 ሴቶቹ አመንዝሮች ናቸውና፥ በእጃቸውም ደም አለና ጻጽቃን ሰዎች ለአመንዝሮቹና ለደም አፍሳሾቹ የተመደበውን ቅጣት ያስተላልፉባቸዋል። + +\s5 +\v 46 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ታላቅ ጦር አመጣባቸዋለሁ፥ ለመበተንና ለመበዝበዝም አሳልፌ አሰጣቸዋለሁ። +\v 47 ሠራዊቱም በድንጋይ ይወግሩአቸዋል በሰይፋቸውም ይቈርጡአቸዋል። ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውንም ይገድላሉ፥ ቤቶቻቸውንም በእሳት ያቃጥላሉ። + +\s5 +\v 48 ከእንግዲህ ሴቶች ሁሉ የሴሰኝነት ተግባር እንዳይፈጽሙ ሴሰኝነትን ከምድሪቱ ላይ አጠፋለሁ። +\v 49 ሴሰኝነታችሁንም በላያችሁ ላይ ይመልሳሉ። እናንተም ኃጢአታችሁንና ጣዖቶቻችሁን ትሸከማላችሁ በዚህ መንገድ እኔ ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\c 24 +\p +\v 1 በዘጠነኛው ዓመት በአሥረኛው ወር ከወሩም በአሥረኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ በዚህ ቀን የባቢሎን ንጉሥ ኢየሩሳሌምን ከቧልና የዚህን ቀን፥ የዛሬን ቀን ስም ጻፍ ። + +\s5 +\v 3 ለዓመፀኛውም ቤት ምሳሌን ተናገር እንዲህም በላቸው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ድስቱን ጣድ! ጣደው! ውኃም ጨምርባት! +\v 4 የምግብ ፍራፍሬዎችን በውስጡ ጨምር፥ ጭኑንና ወርቹን በእርስዋ ውስጥ ሰብስብ፥ የተመረጡትንም አጥንቶች ሙላባት! +\v 5 ከመንጋው የተመረጠውን ውሰድ፥ አጥንቶቹም እንዲበስሉ እንጨት በበታችዋ ማግድ አጥንቶቹም በውስጥዋ ቀቅል። + +\s5 +\v 6 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ዝገት ላለባት ዝገትዋም ለማይለቃት ምንቸት፥ ለደም ከተማ ወዮላት! ጥቂት ጥቂት ከውስጡ ውሰድ፥ ነገር ግን ዕጣ አታውጣላት። + +\s5 +\v 7 ደምዋ በውስጥዋ አለና! በተራቈተ ድንጋይ ላይ አደረገችው እንጂ በአፈር ይከደን ዘንድ በመሬት ላይ አላፈሰሰችውም +\v 8 ይህም መዓትን አመጣባት። ደምዋም እንዳይከደን በተራቈተ ድንጋይ ላይ አፈሰስኩት! + +\s5 +\v 9 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ለደም ከተማ ወዮላት! እኔ ደግሞ የማገዶውን ክምር አሳድጋለሁ። +\v 10 እንጨቱን ጨምር! እሳቱን አንድድ! ሥጋውን ቀቅል መረቁን አጣፍጠው! አጥንቶቹም በደንብ ይቃጠሉ። + +\s5 +\v 11 እንድትሞቅና እንድትግል በውጧ ያለው ርኵሰትዋ በውስጥዋ ይቀልጥ ዘንድ ዝገትዋም ይጠፋ ዘንድ ባዶዋን ድስት በፍም ላይ ጣዳት። +\v 12 በከንቱ ደከመች ሆኖም ዝገትዋ በእሳት ስንኳ አልለቀቀም። + +\s5 +\v 13 አሳፋሪው ተግባርሽ በርኵሰትሽ ውስጥ ነው። እኔ ባነጻሽም አልነጻሽም። መዓቴን በላይሽ እስክጨርስ ድረስ ከርኵሰትሽ አትነጺም። + +\s5 +\v 14 እኔ እግዚአብሔር ይሆናል ብዬ ተናግሬአለሁ ፥ እኔም አደርገዋለሁ! አልመለስም፥ ፥ አልጸጸትምም። እንደ መንገድሽና እንደ ሥራሽ ይፈርዱብሻል! ይላል ጌታ እግዚአብሔር።" + +\s5 +\v 15 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 16 "የሰው ልጅ ሆይ፥ እነሆ፥ የዓይንህን አምሮት በመቅሠፍት እወስድብሃለሁ አንተም ማዘንም ሆነ ማልቀስ የለብህም እንባህንም አታፍስስ። +\v 17 በቀስታ ተክዝ። ለምዋቾችም የቀብር ሥርዓትም አታዘጋጅ። መጠምጠሚያህን በራስህ ላይ አድርግ፥ ጫማህንም በእግርህ አጥልቅ፥ ጢምህን አትሸፍን ወይም ሚስቶቻቸው በመሞታቸው ምክንያት እያዘኑ ያሉ ሰዎችን እንጀራ አትብላ። + +\s5 +\v 18 እኔም በማለዳ ለሕዝቡ ተናገርሁ፥ ምሽት ላይም ሚስቴ ሞተች። በነጋውም እንደ ታዘዝሁ አደረግሁ። + +\s5 +\v 19 ሕዝቡም፥ "ይህ የምታደርገው ነገር ምን እንደ ሆነ አትነግረንምን?" አሉኝ። +\v 20 እኔም እንዲህ አልኋቸው፥ "የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 21 ለእስራኤል ቤት ተናገር እንዲህም በል፥ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የኃይላችሁ ትምክሕት፥ የዓይናችሁ አምሮት፥ ክፉ ምኞታችሁ መቅደሴን አርክሰዋል! ያስቀራችኋቸውም ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ በሰይፍ ይወድቃሉ። + +\s5 +\v 22 እኔም እንዳደረግሁ እናንተ ታደርጋላችሁ ጢማችሁን አትሸፍኑም የኃዘንተኛ ሰዎችንም እንጀራ አትበሉም! +\v 23 ይልቁኑ መጠምጠሚያችሁም በራሳችሁ ጫማችሁም በእግራችሁ ይሆናል፤ አታዝኑም ወይም አታለቅሱምም በኃጢአታችሁም ትሰለስላላችሁና እያንዳንዱ ሰው ስለወንድሙ ያቃስታል። +\v 24 ይህ በሚሆንባችሁ ጊዜ ሕዝቅኤልም ምልክት ይሆናችኋል እርሱ እንዳደረገ ሁሉ እናንተ ታደርጋላችሁ። ከዚያም እኔ ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 25 አንተም የሰው ልጅ ሆይ፥ ደስታቸው፥ ትምክህታቸው የሆነውን መቅደሳቸውንና የሚያዩትና የተመኙትን በያዝኩ ጊዜ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን በወሰድሁባቸው ቀን፥ +\v 26 በዚያ ቀን ያመለጠ ሰው ይህን ሊነግርህ ይመጣል። +\v 27 በዚያ ቀን አፍህ አምልጦ ለመጣው ይከፈታል፥ አንተም ትናገራለህ ከዚያ ወዲያም ዝም አትልም። ምልክትም ትሆናቸዋለህ፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 25 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን ወደ አሞን ልጆች አቅንተህ ትንቢት ተናገርባቸው። + +\s5 +\v 3 ለአሞንም ሰዎች እንዲህ በል፥ 'የጌታን የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡ መቅደሴ በረከሰ ጊዜ የእስራኤልም ምድር ባድማ በሆነች ጊዜ የይሁዳም ቤት በተማረኩ ጊዜ ስለ እነርሱ "እሰይ!" ብላችኋል። +\v 4 ስለዚህ፥ እነሆ፥ ርስት አድርጌ ለምሥራቅ ሰዎች ርስት አድርጌ አሳልፌ አሰጣችኋለሁ፥ እነርሱም በእናንተ ላይ ምሽግን ይሰራሉ ፥ ድንኳኖቻቸውንም በእናንተ ዘንድ ይተክላሉ። ፍሬያችሁን ይበላሉ ወተታችሁንም ይጠጣሉ! +\v 5 የአሞንን ከተማ ለግመሎች ማሰማርያ፥ የአሞንንም ልጆች ለመንጋ መመሰጊያ አደርጋለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 6 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፥ በእጃችሁ አጨብጭባችኋልና፥ በእግራችሁም አሸብሽባችኋልና፥ በእስራኤልም ምድር ላይ በነፍሳችሁ ንቀት ሁሉ ደስ ብሏችኋልና +\v 7 ስለዚህ፥ እነሆ፥ በእጄን እመታችኋለሁ፥ ለአሕዛብም ለብዝበዛ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፥ ከአሕዛብም ለይቼ እቈርጥሃለሁ፥ ከአገሮችም አጠፋሃለሁ እፈጅህማለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃለህ። + +\s5 +\v 8 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ 'ሞዓብና ሴይር እነሆ፥ "የይሁዳ ቤት ያው እንደ ሌሎቹ አሕዛብ ሁሉ ነው!" ብለዋልና +\v 9 ስለዚህ፥ እነሆ፥ የሞዓብን ጫንቃ ከከተሞቹ፥ በዳርቻው ካሉት የምድሩ ትምክሕት ከሆኑት ከተሞቹ፥ ከቤትየሺሞት፥ ከበኣልሜዎን፥ +\v 10 ከቂርያታይም፥ ከአሞን ልጆች ጋር ለምሥራቅ ልጆች እከፍታለሁ። የአሞን ህዝብ በአሕዛብ መካከል ከእንግዲህ ወዲህ እንዳይታሰቡ ርስት አድርጌ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ። +\v 11 በሞዓብም ላይ ፍርድን አደርጋለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 12 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ 'ኤዶምያስ በይሁዳ ቤት ላይ በቀል አድርጎአል፥ ይህን በማድረጉም ስህተት ፈጽሟል። +\v 13 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እጄን በኤዶምያስ ላይ እዘረጋለሁ ከእርስዋም ዘንድ ሰውንና እንስሳን አጠፋለሁ። ከቴማንም ጀምሮ እስከ ድዳንም ድረስ ባድማ አደርጋታለሁ፥ በሰይፍም ይወድቃሉ። + +\s5 +\v 14 በሕዝቤ በእስራኤል እጅ ኤዶምያስን እበቀላለሁ እንደ ቍጣዬና እንደ መዓቴም መጠን በኤዶምያስ ያደርጋሉ በቀሌንም ያውቃሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር!' + +\s5 +\v 15 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል 'ፍልስጥኤማውያን በንቀት በቀልን አድርገዋልና፥ ይሁዳንም ከውስጣቸው ለማጥፋት ደጋግመው ሞክረዋልና +\v 16 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ እጄን በፍልስጥኤማውያን ላይ እዘረጋለሁ፥ ከሊታውያንንም እቈርጣለሁ፥ የባሕሩንም ዳር ቅሬታ አጠፋለሁ። +\v 17 በመዓት መቅሠፍትም ታላቅ በቀል አደርግባቸዋለሁ በቀሌንም በላያቸው ባደረግሁ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 26 +\p +\v 1 እንዲህም ሆነ በአሥራ አንደኛው ዓመት ከወሩ በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፡ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ጢሮስ በኢየሩሳሌም ላይ። 'እሰይ፥ የአሕዛብ በር የነበረች ተሰብራለች ወደ እኔም ተመልሳለች እርስዋ ፈርሳለችና እኔ እሞላለሁ!' ብላለች። + +\s5 +\v 3 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፥ "ጢሮስ ሆይ፥ እነሆ፥ በአንቺ ላይ ነኝ፥ ባሕርም ሞገድዋን እንደምታወጣ እንዲሁ ብዙ ህዝቦችን በአንቺ ላይ አስነሳልሁ። +\v 4 የጢሮስንም ቅጥሮች ያጠፋሉ ግንቦችዋንም ያፈርሳሉ ትቢያዋንም ከእርስዋ እጠርጋለሁ፥ የተራቈተ ድንጋይም አደርጋታለሁ። + +\s5 +\v 5 በባሕር ውስጥ የመረብ ማስጫ ትሆናለች እኔ ተናግሬአለሁና፥ ይላል እግዚአብሔር ለአሕዛብም ብዝበዛ ትሆናለች። +\v 6 በሜዳ ያሉትም ሴቶች ልጆችዋ በሰይፍ ይገደላሉ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 7 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና። እነሆ፥ ከሰሜን የነገሥታት ንጉሥ የባቢሎንን ንጉሥ ናቡከደነፆርን ከፈረሶችና ከሰረገሎች ከፈረሰኞችም ከብዙ ሕዝብ ጋር በጢሮስ ላይ አመጣለሁ። +\v 8 በሜዳ ያሉትን ሴቶች ልጆችሽን በሰይፍ ይገድላቸዋል፥ ምሽግም ይሠራብሻል አፈርንም ይደለድልብሻል ጋሻም ያነሣብሻል። + +\s5 +\v 9 ማፍረሻውን በቅጥርሽ ላይ ያደርጋል፥ መሳሪያውም ግንቦችሽንም ያፈርሳል! +\v 10 ከፈረሶቹም ብዛት የተነሣ ትቢያቸው ይከድንሻል! ሰዎችም በፈርሰ ቅጥር በኩል ወደ ከተማ እንደሚገቡ እርሱ በበሮችሽ ሲገባ፥ ከፈረሰኞችና ከመንኰራኵሮች ከሰረገሎችም ድምፅ የተነሣ ቅጥርሽ ይናወጣል። +\v 11 በፈረሶቹ ኮቴ ጎዳናዎችሽን ሁሉ ይረመርማል፤ ሕዝብሽንም በሰይፍ ይገድላል፥ የብርታትሽም ሐውልት ወደ ምድር ይወድቃል። + +\s5 +\v 12 በዚህ መንገድ ብልጥግናሽንም ሸቀጥሽንም ይዘርፋሉ! ቅጥርሽንም ያፈርሳሉ፥ ተድላ የምታደርጊባቸውን ቤቶችሽን ያጠፋሉ ድንጋይሽንና እንጨትሽን መሬትሽንም በባሕር ውስጥ ይጥላሉ። +\v 13 የዝማሬ ጩኸትሽን ዝም አሰኛለሁ የክራሮች ድምፅ ከዚያ ወዲያ አይሰማም! +\v 14 የተራቈተ ድንጋይ አደርግሻለሁ የመረብም ማስጫ ትሆኛለሽ። ከእንግዲህ እንደገና አትገነቢም እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና፥ ይላል እግዚአብሔር! + +\s5 +\v 15 ጌታ እግዚአብሔር ጢሮስን እንዲህ ይላታል፥ 'በውስጥሽ እልቂት በሆነ ጊዜ በውድቀትሽ ጩኸትና በቆሰሉ ሰዎች የሥቃይ ድምጽ የተወጉት ባንቋረሩ ጊዜ፥ ፥ ከውድቀትሽ ድምፅ የተነሣ ደሴቶች አይነዋወጡምን? +\v 16 የባሕርም አለቆች ሁሉ ከዙፋኖቻቸው ይወርዳሉ መጐናጸፊያቸውን ያወጣሉ ወርቀ ዘቦ ልብሳቸውንም ያወልቃሉ መንቀጥቀጥን ለብሰው በመሬት ላይ ይቀመጣሉ፥ ሁልጊዜም ይንቀጠቀጣሉ ስለአንቺም ይፈራሉ። + +\s5 +\v 17 በአንቺም ላይ ሙሾ ያሞሻሉ፥ እንዲህም ይሉሻል። የመርከበኞች መኖሪያ የነበርሽ እንዴት ወደምሽ! ዝናሽ የወጣ ጠንካራ ከተማ አሁን ግን ከባህር ጠፋሽ! በአንድ ወቅት በእርሷ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ አስፍሪነታቸው በዙሪያቸው ባሉ ሁሉ ላይ ነበር። +\v 18 አሁን በውድቀትሽ ቀን የባህር ዳርቻዎችይንቀጠቀጣሉ፥ በባሕርም ውስጥ ያለ ደሴቶች ከመጥፋትሽ የተነሣ ይደነግጣሉ። + +\s5 +\v 19 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፡ ሰው እንደሌለባቸው ከተሞች ባድማ ከተማ ባደረግሁሽ ጊዜ፥ ቀላያትንም ባንቺ ላይ ባስነሳሁብሽ ጊዜ ብዙ ውኆችም በከደኑሽ ጊዜ፥ +\v 20 ያኔ ወደ ጉድጓድ እንደወረዱ ሰዎች ወደ ጥንት ሰዎች አወርድሻለሁ፤ እንደ ጥንት ዘመን ፍርስራሾች በምድር ጥልቅ ውስጥ እንድትኖሪ አደርግሻልችሁ። ከዚህ የተነሳ ሰዎች ወደሚኖሩበት +\v 21 ጥፋትን አመጣብሻለሁ ለዘላለምም ትጠፊያለሽ፤ ይፈልጉሻል ነገር ግን ለዘላለም አያገኙሽም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\c 27 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 "አንተ የሰው ልጅ ሆይ እንግዲህ ፥ ስለ ጢሮስ ሙሾ ጀምር ጢሮስንም እንዲ በላት +\v 3 'አንቺ በባሕር መግቢያ የምትኖሪ በብዙም ደሴቶች ላይ ከሚኖሩ ህዝቦች ጋር ንግድን የምታደርጊ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጢሮስ ሆይ፥ አንቺ። 'በውበት ፍጹም ነኝ ብለሻል! + +\s5 +\v 4 ዳርቻሽ በባሕር ውስጥ ነው የሰሩሽ ፍጹም ውብ አድርገውታል። +\v 5 ሳንቃዎችሽን ሁሉ ከሳኔር ጥድ ሠርተዋል፥ ደቀልንም ሊሰሩልሽ ከሊባኖስ ዝግባ ወስደዋል። + +\s5 +\v 6 ከባሳን ዛፍ መቅዘፊያሽን ሠርተዋል፥ በዝሆን ጥርስ ከታሸበ ከኪቲም ደሴቶች ዛፍ የመርከብ ወለሎችሽን ሠርተዋል። +\v 7 የመርከብሽ ሸራ ልክ እንደ ሰንደቅ ዓላማሽ የግብጽ ባለብዙ ቀለማት በፍታ ጨርቆች ነበሩ። + +\s5 +\v 8 የሲዶናና የአራድ ሰዎች ቀዛፎችሽ ነበሩ፤ የጢሮስ ጥበበኞችሽ በአንቺ ዘንድ ነበሩ የመርከቦችሽም መሪዎች ነበሩ። +\v 9 ልምድ ያላቸው ጥበበኞች መጋጠሚያዎችሽን ሞልተዋል። የባሕር መርከቦች ሁሉና መርከበኞቻቸው የንግድ እቃዎችሽን ለንግድ ያጓጉዙልሻል። + +\s5 +\v 10 ፋርስና ሉድ ፉጥም በሠራዊትሽ ውስጥ ነበሩ፥ ጋሻና ራስ ቍርም በአንቺ ውስጥ ያንጠለጥሉ ነበር፥ እነርሱም ውበትሽን አሳዩ። +\v 11 በሠራዊትሽ ውስጥ የነበሩት የአራድ እና የኤሌክ ሰዎች በቅጥሮችሽ በዙሪያ ነበሩ፥ ገማዳውያንም በግንቦችሽ ውስጥ ነበሩ! ጋሻቸውንም ዙሪያውን በቅጥርሽ ላይ አንጠለጠሉ! ውበትሽንም ፍጹም አደረጉት! + +\s5 +\v 12 በብዙ ዓይነት ማለትም በብር፥ በብረት ፥ በቈርቈሮና በእርሳስ ካለሽ ብልጥግና ብዛት የተነሣ ተርሴስ የንግድ ደንብኛሽ ነበረች። ሸቀጥሽን ይገዙና ይሸጡ ነበር። +\v 13 ያዋንና ቶቤል ሞሳሕም ባሮችንና ከናስ የተሰሩ እቃዎችን ይነግዱ ነበር። ንግድሽን የሚመሩት እነርሱ ነበሩ። + +\s5 +\v 14 ከቤተ ቴርጋማም መጋዣዎችን፥ የጦር ፈረሶችንና በበቅሎዎችን ወደ ንግድሽ አመጡ። +\v 15 የድዳን ሰዎች በብዙ ዳርቻዎችሽ የንግድ አጋሮችሽ ነበሩ። ንግድ በእጅሽ ነበረ፤ በሸቀጥሽ ምላሽ የዝሆን ጥርስና ዞጲ ይልኩልሽ ነበር። + +\s5 +\v 16 ሶርያ የብዙ ምርቶችሽ ተጠቃሚ ነበረች። በልዋጩም የከበረ ድንጋይ፥ የወይን ጠጅ፥ ባለ ብዙ ቀለም ልብሶች፥ ያማሩ ጨርቆች፥ በዛጎል እና ቀይ ዕንቍም ያቀርቡ ነበር። +\v 17 ይሁዳና የእስራኤል ምድር የንግድ አጋሮችሽ ነበሩ። የሚኒትን ስንዴ ጣፋጭም እንጐቻ፥ ማር ዘይትም በለሳንም ያቀርቡ ነበር። +\v 18 ደማስቆ የምርትሽ ሁሉ፥ ተዝቆ የማያልቅ ሀብትሽ እንዲሁም የኬልቦን የወይን ጠጅና የዘሀርን የበግ ጠጕር ይነግዱ ነበር። + +\s5 +\v 19 ዌንዳንና ያዋን ከአንቺ ጋር ይነግዱ ነበር። ቀልጦ የተሠራ ብረት፥ ብርጕድና ቀረፋም ያቀርቡ ነበረ። ይህም ላንቺ ንግድ ሆነልሽ +\v 20 ድዳን የግላስ ንግድ ከአንቺ ጋር ነበራት። +\v 21 ዓረብና ሌሎች የቄዳር አለቆች ሁሉ የንግድ አጋሮችሽ ነበሩ፤ ጠቦቶች፥ አውራ በጎችና ፍየሎችን ለንግድ ያቀርቡልሽ ነበር። + +\s5 +\v 22 የሳባና የራዕማ ነጋዴዎች ምርጥ የሆነ የቅመም ሽቱ ሁሉና ብዙ ዓይነት የከበሩ ድንጋዮች ሊሸጡልሽ ይመጡ ነበር። ወርቅም ይነግዱ ነበር። +\v 23 ካራንና ካኔ ዔድንም ከሳባ፥ ከአሦርና ከኪልማድ በመሆን የንግድ አጋሮችሽ ነበሩ። + +\s5 +\v 24 እነዚህ ባማረ ልብስ በሰማያዊ ካባ በወርቀ ዘቦም፥ በዝግባ በተሠራች በገመድም በታሰረች በግምጃም በተሞላች ሳጥን ይነግዱ የነበሩ ናቸው። +\v 25 የተርሴስ መርከቦች የሸቀጥሽ ማጓጓዣዎች ነበሩ። አንቺም በባህር መካከል ተሞልተሽ በጭነትም ከብደሽ ነበር። + +\s5 +\v 26 ቀዛፊዎችሽ ወደ ስፊ ባህሮች አመጡሽ፤ የምሥራቅ ነፋስም በባህሮቹ መካከል ሰበረሽ። +\v 27 በውድቀትሽ ቀን ብልጥግናሽ፥ ሸቀጥሽና የንግድ ዕቃዎችሽ፤ የመርከብ ነጂዎችሽ፥ መርከበኞችሽም መርከብ ሠሪዎችሽ፤ ነጋዴዎችሽ ሁሉ በአንቺም ውስጥ የነበሩ ሰዎች ሁሉ በውስጥሽ ካሉት ሠራተኞች ጋር ወደ ባሕር ጥልቅ ይወድቃሉ። + +\s5 +\v 28 ከመርከብ መሪዎች ጩኸት ድምፅ የተነሣ በባህር አጠገብ ያሉ ከተሞች ይንቀጠቀጣሉ። +\v 29 ቀዛፊዎችም ሁሉ መርከበኞችም መርከብ መሪዎችም ሁሉ ከመርከቦቻቸው ወርደው በመሬት ላይ ይቆማሉ። +\v 30 ከዚያም ድምፃቸውን እንድትሰሚ ያደርጉሻል ምርር ብለውም ይጮኻሉ፥ ፤ በራሳቸውም ላይ ትቢያ ይነሰንሳሉ፥ በአመድም ውስጥ ይንከባለላሉ + +\s5 +\v 31 ስለ አንቺም የራሳቸውን ጠጕር ይላጫሉ ማቅም ይታጠቃሉ በምሬትም ስለአንቺ ያነባሉ ይጮኸሉ። +\v 32 በትካዜያቸውም ልቅሶ ያነሡልሻል፥ ስለ አንቺም ሙሾ ያሞሻሉ እንዲህም ይላሉ። በባሕር መካከል ጠፍቶ እንደ ቀረ እንደ ጢሮስ ያለ ማን ነው? +\v 33 ሸቀጥሽ ከባሕር በወጣ ጊዜ ብዙ አሕዛብን ያጠግብ ነበር በብልጥግናሽና በንግድሽ ብዛት የምድርን ነገሥታት ባለ ጠጎች አድርገሻል። + +\s5 +\v 34 ነገር ግን በጥልቅ ውኃ ውስጥ በባህር በተሸፈንሽ ጊዜ ንግድሽና ሠራተኞችሽ ሁሉ ሰጠሙ! +\v 35 በባህር ዳርቻ የሚኖሩ ሁሉ ተደንቀውብሻል፥ ነገሥታቶቻቸውም በፍርሀት ተንቀጥቅጠዋል። ፊታቸውም ደንግጧል። +\v 36 የአሕዛብ ነጋዴዎች አፍዋጩብሽ፤ ለድንጋጤ ሆነሻል፥ ከእንግዲህ በኋላም አትኖሪም። + +\s5 +\c 28 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ የጢሮስን ገዥ እንዲህ በለው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ልብህ ኰርቶአል፥ አንተም "እኔ አምላክ ነኝ! በባሕር መካከል በአማልክት ወንበር ላይ እቀመጣለሁ!" ብለሃል። ነገር ግን አንተ ሰው እንጂ እግዚአብሔር ባትሆንም ልብህን እንደ አምላክ ልብ አደረግህ። +\v 3 እነሆ፥ ከዳንኤል ይልቅ ጥበበኛ እንደሆንክ ምንም ሚስጢር ከአንተ እንደማይሰወር አሰብክ። + +\s5 +\v 4 በጥበብና በማስተዋል ራስህን አበልጽገሀል፥ ወርቅና ብርም በግምጃ ቤትህ ውስጥ ሰብስበሃል! +\v 5 በታላቅ ጥበብና በንግድህ ብልጥግናህን አብዝተሃል ከብልጥግናህም የተነሳ ልብህ ኰርቶአል! + +\s5 +\v 6 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ልብህን እንደ አምላክ ልብ አድርገሃልና +\v 7 ስለዚህ፥ እነሆ፥ እንግዳ ሰዎችን፥ የአሕዛብን ጨካኝ ሰዎችን አመጣብሃለሁ! ሰይፋቸውንም በጥበብህ ውበት ላይ ይመዝዛሉ፥ ክብርህንም ያዋርዳሉ! + +\s5 +\v 8 ወደ ጕድጓድ ያወርዱሃል፥ በባህር ልብ ውስጥ የሞቱትን ሰዎች ሞት ትሞታለህ። +\v 9 በውኑ በገዳይህ ፊት፥ "እኔ አምላክ ነኝ" ትላለህን? አንተ ሰው ነህ እንጂ አምላክ አይደለህም፥ በሚቆራርጡህ እጅ ትወድቃለህ። +\v 10 በእንግዶች ሰዎች እጅ ያልተገረዙትን ሰዎች ሞት ትሞታለህ እኔ ተናግሬአለሁና፥ ይላል እግዚአብሔር!" + +\s5 +\v 11 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 12 የሰው ልጅ ሆይ፥ በጢሮስ ንጉሥ ላይ ሙሾ አሞሽተህ እንዲህ በለው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡ጥበብን የተሞላህ የፍጽምና መደምደሚያ በውበትህም ፍጹም ነበርክ! +\v 13 በእግዚአብሔር ገነት በዔድን ነበርህ! በከበረ ዕንቍስ ሁሉ፥ ሰርድዮን፥ ቶጳዝዮን፥ አልማዝ፥ ቢረሌ፥ መረግድ፥ ኢያስጲድ፥ ሰንፔር፥ በሉር፥ የሚያብረቀርቅ ዕንቍ፥ ወርቅ፥ ተሽፍነህ ነበረ። እነዚህ የከበሩ ድንጋዮች በወርቅ ዕቃ በፊትህ ተቀምጠው ነበር። አነዚህም በተፈጠርህበት ቀን እንድትለብሳቸው ተዘጋጅተው ነበር! + +\s5 +\v 14 የሰውን ዘር እንዲጋርድ እንደቀባሁት ኪሩብ በተቀደሰው በእግዚአብሔር ተራራ ላይ አኖርሁህ! ትመላለስባቸው በነበሩ የእሳት ድንጋዮች መካከል ነበርክ። +\v 15 ከተፈጠርህበት ቀን ጀምረህ በደል እስኪገኝብህ ድረስ በመንገድህ ፍጹም ነበርህ። + +\s5 +\v 16 በንግድህ ብዛት በአምጽ ተሞላህ ስለዚህም ኃጢአትን ሠራህ! ስለዚህ እንደ ርኩስ ነገር ከእግዚአብሔር ተራራ ጣልሁህ የምትጋርድ ኪሩብ ሆይ፥ ከእሳት ድንጋዮች መካከል አጠፋሁህ። +\v 17 በውበትህ ምክንያት ልብህ ኰርቶአል፤ ከክብርህ የተነሣ ጥበብህን አረከስህ! ወደ ምድርም ጣልሁህ! ያዩህም ዘንድ በነገሥታት ፊት አስቀመጥኩህ። + +\s5 +\v 18 በበደልህ ብዛት ቅን ባልሆነው ንግድህም ቅዱስ ስፍራህን አረከስህ! ስለዚህ እሳትን ከውስጥህ አውጥቻለሁ እርስዋም ትበላሀለች። በሚያዩህም ሁሉ ፊት በምድር ላይ አመድ አደርግሀለሁ። +\v 19 በአሕዛብም ውስጥ የሚያውቁህ ሁሉ ይደነቁብሃል፤ ይደነግጣሉ ፥ አንተም እስከ ዘላለምም አትገኝም። + +\s5 +\v 20 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 21 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን ወደ ሲዶና አቅንተህ ትንቢት ተናገርባት! እንዲህም በል፥ +\v 22 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሲዶና ሆይ፥ እነሆ፥ በአንቺ ላይ ነኝ፥ ፍርድን በውስጥሽ በማደርግበት ጊዜ ህዝብሽ እኔ እግዚአብሔር እንድሆንኩ እንዲያውቁ በመካከልሽ ክብሬን እገልጣለሁ። ቅዱስ መሆኔም ይገለጣል። + +\s5 +\v 23 ቸነፈርንም በአንቺ ላይ፥ ደምንም በጎዳናሽ ላይ እሰድዳለሁ፥ በሰይፍ የታረዱ በመካከልሽ ይወድቃሉ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቂያለሽ! +\v 24 እኔ ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ እንዲያውቁ ከእንግዲህም ወዲያ ለእስራኤል ቤት የሚወጋ እሾህ፥ በዙሪያቸውም ካሉ ከናቋቸው ሁሉ የሚያቈስል ኵርንችት አይሆንም + +\s5 +\v 25 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የእስራኤልን ቤት ከተበተኑባቸው አሕዛብ ዘንድ በሰበሰብሁ ጊዜ፥ በአሕዛብም ፊት በተቀደስሁባቸው ጊዜ፥ ለባሪያዬ ለያዕቆብ በሰጠኋት ምድራቸው ይቀመጣሉ። +\v 26 በውስጧም ተዘልለው ይቀመጡባታል ቤቶችንም ይሠራሉ ወይኑንም ይተክላሉ በዙሪያቸውም ባሉ በሚንቋቸው ሁሉ ላይ ፍርድን ባደረግሁ ጊዜ ተዘልለው ይቀመጣሉ እኔም እግዚአብሔር አምላካቸው እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 29 +\p +\v 1 በአሥረኛው ዓመት በአሥረኛው ወር ከወሩም በአሥራ ሁለተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን በግብጽ ንጉሥ በፈርዖን ላይ አድርግ፥ በእርሱና በግብጽ ሁሉ ላይም ትንቢት ተናገር፥ +\v 3 እንዲህም በል። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በወንዞች መካከል የምትተኛና። ወንዙ የእኔ ነው ለራሴም ሠርቼዋለሁ የምትል ታላቅ የባህር ውስጥ ፍጥረት፥ የግብጽ ንጉሥ ፈርዖን ሆይ፥ እነሆ፥ በአንተ ላይ ነኝ። + +\s5 +\v 4 በመንጋጋህ መቃጥን አገባብሃለሁ፥ የወንዞችህንም ዓሦች ወደ ቅርፊትህ አጣብቃለሁ በቅርፊትህ ላይ ከተጣበቁ ዓሦች ሁሉ ጋር ከወንዞችህም መካከል አወጣሃለሁ። +\v 5 አንተንና የወንዞችህን ዓሦች ሁሉ ወደ ምድረ በዳ እጥላለሁ፥ በምድርም ፊት ላይ ትወድቃለህ እንጂ አትከማችም አትሰበሰብም። መብልም አድርጌ ለምድር አራዊትና ለሰማይ ወፎች እሰጥሀለሁ። + +\s5 +\v 6 ለእስራኤል ቤት የሸንበቆ በትር ሆነዋልና በግብጽም የሚኖሩ ሁሉ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። +\v 7 በእጅ በያዙህ ጊዜ ተሰበርህና ተሰነጣጥቅህ ትከሻቸውን ትወጋለህ፤ በተደገፉብህም ጊዜ እግራቸውን ትሰባብራለህ ወገባቸውንም እንዲንቀጠቀጥ ታደርጋለህ። + +\s5 +\v 8 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ ሰይፍ አመጣብሃለሁ፥ ሰውንና እንስሳንም ከአንተ ዘንድ አጠፋለሁ። +\v 9 የባህር ጭራቁ "ወንዙ የእኔ ነው የሠራሁትም እኔ ነኝ" ብሏልና የግብጽ ምድር ባድማና ውድማ ትሆናለች፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ አንተ። +\v 10 ስለዚህ፥ እነሆ፥ በአንተና በወንዞችህ ላይ ነኝ፥ የግብጽንም ምድር ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴዌኔና እስከ ኢትዮጵያ ዳርቻ ድረስ ውድማና ባድማ አደርጋታለሁ። + +\s5 +\v 11 የሰው እግር አያልፍባትም የእንስሳም ኮቴ አያልፍባትም፥ እስከ አርባ ዓመትም ድረስ ማንም አይኖርባትም። +\v 12 ባድማም በሆኑ ምድሮች መካከል የግብጽን ምድር ባድማ አደርጋታለሁ፥ በፈረሱትም ከተሞች መካከል ከተሞችዋ አርባ ዓመት ፈርሰው ይቀመጣሉ ግብጻውያንንም ወደ አሕዛብ እበትናቸዋለሁ በአገሮችም እዘራቸዋለሁ። + +\s5 +\v 13 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ከአርባ ዓመት በኋላ ግብጻውያንን ከተበተኑባቸው አሕዛብ ዘንድ እሰበስባለሁ +\v 14 የግብጽንም ምርኮ እመልሳለሁ፥ ወደ ተወለዱባትም ምድር ወደ ጳትሮስ እመልሳቸዋለሁ በዚያም የተዋረደች መንግሥት ይሆናሉ። + +\s5 +\v 15 ከሌሎች መንግሥታት ሁሉ ይልቅ የተዋረደች ትሆናለች ከእንግዲህ ወዲያ ከአሕዛብ መካከል ከፍ አትልም።ከእንግዲህም በአሕዛብም ላይ እንዳይገዙ አሳንሳቸዋለሁ። +\v 16 ግብጻውያን ከእንግዲህ ለእስራኤል ቤት የትምክህት ምክንያት አይሆኑም። ይልቁኑ እስራኤል ለእርዳታ ፊቷን ወደ ግብጽ ባዞረች ጊዜ የፈጸመችውን በደል የሚያሳስቡ ይሆናሉ።እኔም ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 17 እንዲህም ሆነ በሀያ ሰባተኛው ዓመት በመጀመሪያው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 18 የሰው ልጅ ሆይ፥ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በጢሮስ ላይ ጽኑ ሥራ ለማሰራት ሠራዊቱን ሰበሰበ። ራስ ሁሉ ተላጭቶ ጫንቃም ሁሉ ተልጦ ነበር፥ ነገር ግን በላይዋ ስላገለገለው አገልግሎት እርሱና ሠራዊቱ ምንም አይነት ደመወዝ ከጢሮስ አልተቀበሉም። + +\s5 +\v 19 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የግብጽን ምድር ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር እሰጠዋለሁ፥ ብዛትዋንም ይወስዳል ምርኮዋንም ይማርካል ብዝበዛዋንም ይበዘብዛል ይህም ለሠራዊቱ ደመወዝ ይሆናል። +\v 20 ለእኔ ለሠሩት ሥራ ደመወዝ አድርጌ የግብጽን ምድር ሰጥቼዋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 21 በዚያ ቀን ለእስራኤል ቤት ቀንድን አበቅላለሁ፥ በመካከላቸውም ለአንተ የተከፈተ አፍን እሰጣለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 30 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት ተናገር እንዲህም በል። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ዋይ! በሉ፥ ለቀኑ ወዮ! ቀኑ ቅርብ ነው፥ +\v 3 የእግዚአብሔር ቀን ቅርብ ነው፥ የደመና ቀን፥ ለአሕዛብም ክፉ ወቅት ይሆናል። + +\s5 +\v 4 ሰይፍ በግብጽ ላይ ይመጣል፥ የተገደሉት ሰዎች በግብጽ ውስጥ ሲወድቁ ሀብቷን ሲወስዱ መሠረትዋም ሲፈርስ በኢትዮጵያ ውስጥ ሁከት ይሆናል! +\v 5 ኢትዮጵያ፥ ፉጥና ሉድም እንግዶችም የቃል ኪዳንም ህዝቦች ከእነርሱ ጋር በሰይፍ ይወድቃሉ። + +\s5 +\v 6 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ግብጽን የሚደግፉ ይወድቃሉ፥ የኃይልዋም ትምክህት ይወርዳል። ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴዌኔ ድረስ ወታደሮቻቸው በሰይፍ ይወድቃሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር! +\v 7 ባድማም በሆኑ አገሮች መካከል ይሸበራሉ፥ ከተሞቻቸውም እንደ ፈረሱት ከተሞች ይሆናሉ። + +\s5 +\v 8 እሳትንም በግብጽ ባነደድሁ ጊዜ ረዳቶችዋም ሁሉ በጠፉጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ! +\v 9 በዚያ ቀን መልእክተኞች ተዘልለው የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያንን ለማስፈራት ከፊቴ በመርከብ ይወጣሉ በግብጽም ጥፋት ቀን ሁከት ይሆንባቸዋል። እነሆ፥ ይመጣልና! + +\s5 +\v 10 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነፆር እጅ የግብጽን ህዝብ ፍጻሜ አመጣለሁ። +\v 11 የአህዛብ ድንጋጤ የሆኑት እርሱና ሠራዊቱ ምድሪቱን ለማጥፋት ይመጣሉ፤ ሰይፋቸውንም በግብጽ ላይ ይመዝዛሉ ምድሪቱንም በሞቱ ሰዎች ይሞላሉ! + +\s5 +\v 12 ወንዞችን ደረቅ መሬት አደርጋለሁ ምድሪቱንም ለክፉ ሰዎች እሸጣለሁ። ምድሪቱንና ሙላዋንም በእንግዶች እጅ ባድማ አደርጋለሁ! እኔ እግዚአብሔር ተናግሬያለሁ! + +\s5 +\v 13 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጣዖቶችን አጠፋለሁ እርባና ቢስ የሆኑትን የሜምፎስ ጣዖታት እሽራለሁ። ከእንግዲህ ወዲያ በግብጽ ምድር አለቃ አይገኝም ፥ በግብጽም ምድር ላይ ሽብርን አደርጋለሁ! +\v 14 ጳትሮስንም አፈርሳለሁ፥ በጣኔዎስም እሳትን አነድዳለሁ፥ በኖእ ላይም ፍርድን አደርጋለሁ። + +\s5 +\v 15 በግብጽም ምሽግ በሲን ላይ መዓቴን አፈስሳለሁ፥ የኖእንም ህዝብ አጠፋለሁ። +\v 16 ከዚያም በግብጽ እሳትን አነድዳለሁ። ሲንም ትጨነቃለች ኖእም ትሰበራለች፥ ሜምፎስም በየቀኑ ጠላቶች ይነሱባታል! + +\s5 +\v 17 የሄልዮቱና የቡባስቱም ወጣቶች በሰይፍ ይወድቃሉ ከተሞቻቸውም ይማረካሉ። +\v 18 በዚያ የግብጽን ቀንበር በሰበርሁ ጊዜ በጣፍናስ ቀኑ ይጨልማል የኃይልዋም ትዕቢት ይጠፋል። ደመናም ይጋርዳታል፥ ሴቶች ልጆችዋም ይማረካሉ። +\v 19 እንዲሁ በግብጽ ላይ ፍርድን አደርጋለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 20 እንዲህም ሆነ በአሥራ አንደኛው ዓመት በመጀመሪያው ወር ከወሩም በሰባተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 21 የሰው ልጅ ሆይ፥ የግብጽን ንጉሥ የፈርዖንን ክንድ ሰብሬያለሁ።። እነሆም፥ እንዲድን በጨርቅ አልታሰረም በመቃም አልታሰረለትም ስለዚህም ሰይፍን ለመያዝ የሚያስችል ጥንካሬ የለውም። + +\s5 +\v 22 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ እኔ በግብጽ ንጉሥ በፈርዖን ላይ ተነስቻለሁ! ጠንካራውንም የተሰበረውንም ክንዱን እሰብራለሁ፥ ሰይፉንም ከእጁ አስጥላለሁ። +\v 23 ግብጻውያንንም ወደ አሕዛብ እበትናለሁ ወደ አገሮችም እዘራቸዋለሁ። +\v 24 የፈርዖንን ክንድ ለመስበር የባቢሎንን ንጉሥ ክንድ አበረታለሁ ሰይፌንም በእጁ እሰጣለሁ። በባቢሎን ንጉሥ ፊት ለሞት እንድሚያጣጥር ሰው ያጓራል። + +\s5 +\v 25 የባቢሎንንም ንጉሥ ክንድ አጸናለሁ የፈርዖን ክንድ ግን ይወድቃል። ሰይፌንም በባቢሎን ንጉሥ እጅ በሰጠሁ ጊዜ እርሱም በሰጠሁት ሰይፍ የግብጽን ምድር በሚመታ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። +\v 26 ግብጻውያንንም ወደ አሕዛብ እበትናለሁ ወደ አገሮችም እዘራቸዋለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 31 +\p +\v 1 እንዲህም ሆነ በአሥራ አንደኛው ዓመት በሦስተኛው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ የግብጽን ንጉሥ ፈርዖንንና በዙሪያው ያሉትን አገልጋዮቹን እንዲህ በላቸው። 'በታላቅነትህ ማንን ትመስላለህ? + +\s5 +\v 3 እነሆ፥ አሦር ጫፉ እንደ ተዋበ፥ ችፍግነቱ ጥላ እንደ ሰጠ፥ ቁመቱም እንደ ረዘመ፥ ራሱም በደመናዎች መካከል እንደ ነበረ እንደ ሊባኖስ ዝግባ ነበረ። +\v 4 ውኆችም አበቀሉት፥ ቀላይም ግዙፍ አደረገው። ወንዞችም በተተከለበት ዙሪያ ይጐርፉ ነበር፥ መስኖዎቻቸውን በሜዳ ወዳሉ ዛፎች ይሰዳሉ። + +\s5 +\v 5 ቁመቱ ከምድረ በዳ ዛፍ ሁሉ ከፍ ያለ ነበር አለ፤ ቅርንጫፎቹም ከብዙ ውኆች የተነሣ ረዘሙ። +\v 6 የሰማይ ወፎች ሁሉ ጎጆቻቸውን በቅርንጫፎቹ ላይ አደረጉ፥ የምድርም አራዊት ሁሉ ከጥላው በታች ተዋለዱ። ታላላቅ ህዝቦች ከጥላውም በታች ኖሩ። +\v 7 ሥሩም በብዙ ውኃ አጠገብ ነበረና በታላቅነቱና በቅርንጫፎቹ ርዝመት የተዋበ ነበረ። + +\s5 +\v 8 በእግዚአብሔር ገነት የነበሩ ዝግባዎች አልተካከሉትም! ጥዶችም ቅርንጫፎቹን አይመስሉትም አስታ የሚባለውም ዛፍ ቅርንጫፎቹን አይተካከሉም! በእግዚአብሔርም ገነት ካሉ ዛፎች በውበቱ ሊተካከለው አልቻለም! +\v 9 በቅርንጫፎቹ ብዛት ውብ አደረግሁት፤ በእግዚአብሔርም ገነት በዔድን የነበሩ ዛፎች ሁሉ ቀኑበት። + +\s5 +\v 10 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ቁመቱ ከፍ ከፍ ብሎአልና፥ ጫፎቹንም ከቅርንጫፎች በላይ አድርጎአልና፥ +\v 11 ልቡም በቁመቱ ልክ ኰርቶአልና ከአሕዛብ ሁሉ በላይ ኃይለኛ ገዢ እጅ አሳልፌ እሰጠዋለሁ! ይህም ገዢ ይቃወመዋል እንደ ክፋቱም መጠን ያሳድደዋለሁ። + +\s5 +\v 12 የአህዛብ ድንጋጤ የሆኑ የሌላ አገር ሰዎች፥ አስወግዱት ፈጽሞም ጣሉት። ቅርንጫፎቹ በተራሮችና ላይና በሸለቆች ውስጥ ወደቁ፥ ቅርንጫፎቹም በምድር ፈሳሾች ሁሉ ላይ ተሰባበሩ። የምድርም አሕዛብ ሁሉ ከጥላው ወጥተው ጥለውት ሄዱ። + +\s5 +\v 13 የሰማይ ወፎች ሁሉ በግንዱ ላይ ይቀመጣሉ የምድርም አራዊት ሁሉ በቅርንጫፎቹ ላይ ይቀመጣሉ። +\v 14 ይህም የሆነው ወደ ጕድጓድ በሚወርዱ በሰው ልጆች መካከል ሁላቸው ለታችኛው ምድር ለሞት አልፈው ተሰጥተዋልና ውሀ ሲጠጡ ከነበሩት ዛፎች ውስጥ አንዳቸውም ረጅም ሆነው እንዳያድጉ፥ ጫፎቻቸውም ከቅጠሎች በላይ እንዳይሆኑ፥ በውኃ አጠገብ ያሉ ዛፎች ሁሉ ከእንግዲህ በቁመታቸው እንዳይረዝሙ ነው። + +\s5 +\v 15 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ወደ ሲኦል በወረደበት ቀን ልቅሶን ወደ ምድር አመጣሁ። በቀላያትም ሸፈንኩት፥ የውቅያኖስ ፈሳሾቹንም ከለከልሁ። ታላላቆችም ውኆች ከለከልኩ፥ ሊባኖስንም ስለ እርሱ አሳዘንሁት! የዱርም ዛፎች ሁሉ ስለ እርሱ አለቀሱ። + +\s5 +\v 16 ወደ ጕድጓድ ከሚወርዱ ጋር ወደ ሲኦል በጣልሁት ጊዜ ክአውዳደቁ ድምፅ የተነሣ በአሕዛብ ላይ መንቀጥቀጥን አመጣሁ! በምድር ዝቅተኛ ቦታ የኤደን ዛፎችን ሁሉ አጽናናለሁ! እነርሱም ውኃ የሚጠጡ ፥ ምርጦችና መልካካሞች የሊባኖስ ዛፎች ናቸው። + +\s5 +\v 17 ክንዱም ወደ የነበሩት በአሕዛብም መካከል በጥላው ሥር የተቀመጡት፥ በሰይፍ ወደ ተገደሉት ሰዎች ወደ ሲኦል ከእርሱ ጋር ወርደዋልና። +\v 18 በክብርና በታላቅነት በዔድን ዛፎች መካከል ማን ይመስልህ ነበር? ነገር ግን ከዔድን ዛፎች ጋር ወዳልተገረዙት መካከል ወደ ታችኛው ምድር ያወርዱሃል፤ በሰይፍም ከተገደሉት ጋር ትኖራለህ! እነርሱም ፈርዖንና አገልጋዮቹ ናቸው ይላል ጌታ እግዚአብሔር!" + +\s5 +\c 32 +\p +\v 1 እንዲህም ሆነ በአሥራ ሁለተኛው ዓመት በአሥራ ሁለተኛው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 2 የሰው ልጅ ሆይ፥ ስለ ግብጽ ንጉሥ ስለ ፈርዖን ሙሾ አሙሽ፥ እንዲህም በለው፥ 'በእህዛብ መካከል እንደ አንበሳ ደቦል በባህር እንዳለ አስፈሪ ፍጥረት ነበርክ፤ ውሃውን አናወጥከው፥ ውሆችን በእግርህ በጥብጠህ አጨቀየሀቸው። + +\s5 +\v 3 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በብዙ አሕዛብ ጉባኤ መረቤን እዘረጋብሃለሁ፥ እነርሱም በመረቤ ይይዙሀል! +\v 4 በምድርም ላይ እተውሃለሁ፥ በምድረ በዳም ፊት እጥልሃለሁ፥ የሰማይንም ወፎች ሁሉ አሳርፍብሃለሁ፥ የተራቡ ምድርን አራዊት በአንተ አጠግባቸዋለሁ። + +\s5 +\v 5 ሥጋህን በተራሮች ላይ አደርጋለሁ ሸለቆቹንም በትል በተሞላ ሬሳህ እሞላለሁ! +\v 6 ደምህንም በተራሮች ላይ አፈሳለሁ መስኖችም በደምህ ይሞላሉ። + +\s5 +\v 7 መብራትህን ባጠፋህ ጊዜ ሰማዮችን እሸፍናለሁ፥ ከዋክብቶችንም አጨልማለሁ። ፀሐይንም በደመና እሸፍናለሁ ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም! +\v 8 የሰማይን ብርሃኖች ሁሉ በላይህ አጨልማለሁ፥ በምድርህም ላይ ጨለማ አደርጋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 9 በአዛብ መካከል ጥፋትህን በማመጣ ጊዜ የማታውቃቸውን የብዙ ሕዝብን ልብ አስደነግጣለሁ። +\v 10 ብዙም አሕዛብን ስለዘንተ አስደንቃለሁ፤ ሰይፌንም በፊታቸው ባወዛወዝሁ ጊዜ ነገሥታቶቻቸው ስለ አንተ እጅግ አድርገው ይፈራሉ። በውድቀትህም ቀን እያንዳንዱ በአንተ ምክንያት ይንቀጠቀጣል። + +\s5 +\v 11 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና። የባቢሎን ንጉሥ ሰይፍ ይመጣብሃል። +\v 12 አገልጋዮችህ የአህዛብ ድንጋጤ በሆኑ ጦርኞች ሥይፍ እንዲወድቁ አደርጋልሁ! የግበጽንም ትዕቢት ያውርዳሉ ህዝቧንም ሁሉ ያጠፋሉ! + +\s5 +\v 13 እንስሶችን ከብዙ ውኃ አጠገብ አጠፋለሁ፤ ከእንግዲህም ወዲያ የሰው እግርም ሆነ የእንስሳት ኮቴ ውሃውን አያደፈርስም! +\v 14 በዚያን ጊዜ ውኃቸውን አረጋጋለሁ፥ እንደ ዘይትም እንዲፈስሱ አደርጋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 15 ሙሉ የነበረውን የግብጽን ምድር ባድማና ውድማ ባደረግሁ ጊዜ፥ የሚኖሩባትንም ሁሉ በቀሠፍሁ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ! +\v 16 የአሕዛብ ቈነጃጅት ያለቅሱበታል ያለቅሱባታልና ሙሾ ይሆናል፥ ነው ስለ ግብጽና ስለአገልጋዮቿ ሁሉ ያለቅሳሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 17 እንዲህም ሆነ በአሥራ ሁለተኛው ዓመት ከወሩም በአሥራ አምስተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 18 የሰው ልጅ ሆይ፥ ስለ ግብጽ አገልጋዮች አልቅስ፥ እርስዋንና የብርቱዎችን አሕዛብ ሴቶች ልጆች ወደ ጕድጓድ ከሚወርዱ ጋር ወደ ታችኛው ምድር ጣላቸው። + +\s5 +\v 19 እንዲህ ብለህ ጥይቃቸው፥ 'ከማንም ይልቅ በውበት ትበልጣላችሁን? ውረዱና ካልተገረዙትም ጋር ተኙ! +\v 20 በሰይፍ በተገደሉት መካከል ይወድቃሉ፤ ጥላቶቿ እርሷንና አገልጋዮቿን ይይዛሉ! +\v 21 በሲኦል የኃያላን አለቆች ስለ ግብጽ ፥ "ወደዚህ ወደ ሲዖል መጥተዋል! በሰይፍ ከተገድሉ ካልተገርዙት ጋር ይተኛሉ!' ብለው ይናገራሉ። + +\s5 +\v 22 አሦርና ጉባኤዋ ሁሉ በዚያ አሉ መቃብሮችም ከበዋታል፤ ሁሉም በሰይፍ የተገደሉ ናቸው። +\v 23 መቃብራቸው በጕድጓዱ በውስጠኛው ክፍል የሆኑትም ከእርሷ ጉባኤ ሁሉ ጋር በዚያ አሉ! መቃብሯ በተገደሉ፥ በሰይፍ በወደቁ እንዲሁም በሕያዋን ምድር ፍርሀትን ባመጡ ተከቧል። + +\s5 +\v 24 ኤላምም ከአገልጋዮቿ ጋር በዚያ አለች፤ መቃብሮቿም ከበዋታል። ሁሉም የተገደሉ ናቸው። እነርሱም በሕያዋን ምድር ያስፈሩ ሁሉ ፥ ሳይገረዙም ወደ ታችኛው ምድር የወረዱ፥ በህያዋን ምድር ሽብርን ያመጡና ወደ ጕድጓድም ከሚወርዱ ጋር እፍረታቸውን የተሸከሙ ናቸው። +\v 25 በተገደሉት መካከል ለኤላምና ለአገልጋዮቻ መኝታን አድርገውላታል፤ መቃብርዋ በዙሪያዋ ነው! ሁሉም ያልተገረዙና በህያዋን ምድር ሽብርን በማምጣታቸው በሰይፍ የተገደሉ ናቸው! ወደ ጕድጓድም ከሚወርዱ ጋር እፍረታቸውን ተሸክመዋል። ኤላምም በተገደሉትም መካከል ነች። + +\s5 +\v 26 ሞሳሕና ቶቤል ብዛታቸውም ሁሉ በዚያ አሉ መቃብራቸውም በዙሪያቸው ነው ሁሉም ያልተገረዙ ሲሆኑ በሕያዋን ምድር ሽብር ያመጡ ስለነበር በሰይፍ የተገደሉ ናቸው! +\v 27 በሕያዋንም ምድር ኃያላኑን ያስፈሩ ነበርና መሣሪያቸውን ይዘው ወደ ሲኦል ከወረዱ፥ ሰይፋቸውንም ከራሳቸው በታች ካደረጉ፥ ካልተገረዙ ኃያላን ጋር አልተኙምን? በህያዋን ምድር አስፈሪ ተዋጊዎች በመሆናቸው ጋሻቸውም በአጥንታቸው ላይ ነው ። + +\s5 +\v 28 አንቺም ግብጽ ባልተገረዙት መካከል ትሰበሪያለሽ! በሰይፍም ከተገደሉት ጋር ትተኚያለሽ። +\v 29 ኤዶምያስ ከነገሥታቶችዋና ከአለቆችዋ ሁሉጋር በዚያ አሉ። ኃያላን ነበሩ፥ ነገር ግን አሁን በሰይፍ ከተገደሉትና ካልተገረዙት ወደ ጕድጓድ ከሚወርዱ ጋር ይተኛሉ ። + +\s5 +\v 30 የሰሜን አለቆች ሁሉ ከሙታን ጋር የወረዱ ከሲዶናውያንም በዚያ አሉ! ኃያላን ነበሩ፥ አሁን ግን በዚያ በእፍረት ፥ በሰይፍ ከተገደሉት ጋር ሳይገረዙ ተኝተዋል። እፍረታቸውን ወደ ጕድጓድም ከሚወርዱት ጋር ይሸከማሉ። + +\s5 +\v 31 ፈርዖንም ይመለከታል በሠይፍ ስለተገደሉት አገልጋዮቹ ይጽናናል ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 32 መፈራቱን በሕያዋን ምድር አድርጌአለሁ፥ ነገር ግን በሰይፍ በተገደሉት ባልተገረዙት መካከል ይተኛል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር!" + +\s5 +\c 33 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ለሕዝብህ ልጆች ተናገር እንዲህም በላቸው፥ 'ሰይፍን በምድር ላይ ባመጣሁ ጊዜ፥ የምድር ሕዝብ ከመካከላቸው ሰውን ወስደው ለራሳቸው ጕበኛ ያድርጉ። +\v 3 ሰይፍ በመጣ ጊዜ ይመልከት ቀንደ መለከቱንም በመንፋት ህዝቡን ያስጠንቅቅ! +\v 4 ህዝቡም የመለከቱን ድምፅ ሰምተው ባይጠነቀቁ ፥ ሰይፍ መጥቶ ቢገድላቸው እያንዳንዱ ሰው ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል። + +\s5 +\v 5 አንድ ሰው የመለከቱን ድምፅ ሰምቶ ባይጠነቀቅ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል፤ ነገር ግን ቢጠነቀቅ የራሱን ህይወት ያድናል። +\v 6 ጕበኛው ግን ሰይፍ ሲመጣ ቢያይ መለከቱንም ባይነፋ ሕዝቡንም ባያስጠነቅቅ ሰይፍም መጥቶ አንድን ሰው ቢገድል እሱ በኃጢአቱ ይሞታል፥ደሙን ግን ከጕበኛው እጅ እፈልጋለሁ። + +\s5 +\v 7 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ለእስራኤል ቤት ጕበኛ አድርጌሃለሁ፤ ከአፌ ቃሌን ስማ እኔን ወክለህ አስጠንቅቃቸው። +\v 8 ኃጢአተኛውን "ኃጢአተኛ ሆይ፥ በእርግጥ ትሞታለህ!" ባልኩት ጊዜ፥ ኃጢአተኛውን ከመንገዱ እንዲመለስ ለማስጠንቀቅ ባትናገር ያ ኃጢአተኛ በኃጢአቱ ይሞታል፥ ደሙን ግን ከእጅህ እፈልጋለሁ። +\v 9 ነገር ግን ከመንገዱ እንዲመለስ ኃጢአተኛውን ብታስጠነቅቀው እርሱ ግን ከመንገዱ ባይመለስ በኃጢአቱ ይሞታል አንተ ግን ነፍስህን አድነሃል። + +\s5 +\v 10 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ የእስራኤልን ቤት እንዲህ በላቸው፥ 'እናንተ በደላችንና ኃጢአታችን በላያችን አሉ እኛም ሰልስለንባቸዋል እንዴትስ በሕይወት እንኖራለን? ብላችኋል' ። +\v 11 'እኔ ሕያው ነኝና ኃጢአተኛው ከመንገዱ ተመልሶ በሕይወት እንዲኖር እንጂ ኃጢአተኛው እንዲሞት አልፈቅድም፥ የእስራኤል ቤት ሆይ ንስሀ ግቡ! ስለ ክፉ መንገዳችሁ ንስሀ ግቡ ለምን ትሞታላችሁ ይላል ጌታ እግዚአብሔር?' በላቸው። + +\s5 +\v 12 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ህዝብህን እንዲህ በላቸው፥' ጻድቅ ቢበድል ጽድቁ አያድነውም! ኃጢአተኛም ከኃጢአቱ ቢመለስ በኃጢአቱ አይጠፋም። ጻድቁም ኃጢአት ቢስራ በጽድቁ በሕይወት ሊኖር አይችልም። +\v 13 እኔ ጻድቁን፥ "በእርግጥ በሕይወት ይኖራል!" ባልሁ ጊዜ፥ እርሱ በጽድቁ ታምኖ ኃጢአት ቢሠራ በሠራው ኃጢአት ይሞታል እንጂ ጽድቁ አላስብለትም። + +\s5 +\v 14 እኔም ኃጢአተኛውን። በእርግጥ ትሞታለህ ባልሁ ጊዜ፥ እርሱ ከኃጢአቱ ተመልሶ ፍርድንና ቅን ነገርን ቢያደርግ፥ +\v 15 ኃጢአተኛውም የብድር መያዣን ቢመልስ የነጠቀውንም ቢመልስ ሕይወት በሚሰጡ ትእዛዛት ቢራመድ ከዚያም በኋላ ኃጢአት ባይሠራ፥ በእርግጥም በሕይወት ይኖራል እንጂ አይሞትም። +\v 16 የሠራው ኃጢአት ሁሉ አይታሰብበትም። ፍርድንና ቅን ነገርን አድርጎአል በእርግጥ በሕይወት ይኖራል። + +\s5 +\v 17 ነገር ግን ሕዝብህ ፥ "የጌታ መንገድ የቀና አይደለም!" ይላሉ ነገር ግን ቅን ያልሆነው የእናንተ መንገድ ነው! +\v 18 ጻድቅ ከጽድቁ ተመልሶ ኃጢአትን ቢሠራ በኃጢአቱ ይሞታል! +\v 19 ኃጢአተኛውም ከኃጢአቱ ተመልሶ ፍርድንና ቅን ነገርን ቢያደርግ ባደረጋቸው ነገሮች ምክንያት በሕይወት ይኖራል። +\v 20 እናንተ ግን፥ "የጌታ መንገድ የቀና አይደለም!" ትላላችሁ። የእስራኤል ቤት ሆይ፥ በእያንዳንዳችሁ ላይ እንደ መንገዳችሁ እፈርድባችኋለሁ። + +\s5 +\v 21 እንዲህም ሆነ በተማረክን በአሥራ ሁለተኛው ዓመት በአሥረኛው ወር ከወሩም በአምስተኛው ቀን ከኢየሩሳሌም ያመለጠ አንድ ሰው ወደ እኔ መጥቶ "ከተማይቱ ተያዘች!"አለኝ። +\v 22 ሰውዬው ከመምጣቱ በፊት ባለው ምሽት የእግዚአብሔር እጅ በእኔ ላይ ነበረች፥ ሰውዬው በምሽት ወደ እኔ በመጣ ጊዜ አፌ ተከፍቶ ነበር። ስለዚህም አፌ ተከፍቶ ነበር ከዚያም በኋላ እኔ ዲዳ አልሆንሁም። + +\s5 +\v 23 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። +\v 24 የሰው ልጅ ሆይ፥ በእስራኤል ምድር ባሉ በባድማ ስፍራዎች የተቀመጡ፥ 'አብርሃም ብቻውን ሳለ ምድሪቱን ወረሰ እኛም ብዙዎች ነን ምድሪቱም ርስት ሆና ለእኛ ተሰጥታለች' ይላሉ። + +\s5 +\v 25 ስለዚህ እንዲህ በላቸው፥'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ከደም ጋር ትበላላችሁ፥ ዓይናችሁንም ወደ ጣዖቶቻችሁ ታነሣላችሁ፥ የስዎችንም ደም ታፈስሳላችሁ። በውኑ ምድሪቱን ትወርሳላችሁን? +\v 26 በሰይፋችሁ ተማምናችሁ፥ ርኩስ ነገርን ታደርጋላችሁ፥ የባልንጀሮቻችሁንም ሚስቶች ታስነውራላችሁ። በውኑ ምድሪቱን ትወርሳላችሁን? + +\s5 +\v 27 እንዲህም በላቸው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ ሕያው ነኝና በባድማ ስፍራዎች ያሉ በሰይፍ ይወድቃሉ፥ በምድረ በዳ ያለውን ለአራዊት መብል አድርጌ እሰጣለሁ፥ በአምባዎችና በዋሾች ያሉ በቸነፈር ይሞታሉ። +\v 28 ምድሪቱንም ባድማና ውድማ አደርጋታለሁ በኃይሏም መመካቷ ይቀራል፥ የእስራኤልም ተራሮች ማንም የማያልፍባቸው በረሀ ይሆናሉ፥ ። +\v 29 ስላደረጉትም ርኵሰት ሁሉ ምድሪቱን ባድማና ውድማ ባደርግሁ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 30 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ሕዝብህ በቅጥር አጠገብና በቤት ደጆች ውስጥ ስለ አንተ ይናገራሉ፥ እርስ በርሳቸውም፥ አንዱ ከአንዱ ጋር፥ 'ወደ ነቢዩ እንሂድና እግዚአብሔር ያለው ቃል ምን እንደ ሆነ እንስማ!' እያሉ ይነጋገራሉ። +\v 31 ስለዚህ ሕዝቤ ብዙ ጊዜ እንደሚያደርጉት መጥተው በፊትህ ይቀመጣና ቃልህንም ይሰማሉ ነገር ግን አያደርጉትም። ትክክለኛው ቃል በፍቸው ነው ፥ ልባቸው ግን ቅንነት የሌለበትን ትርፍ ትከተላለች። + +\s5 +\v 32 እነሆ፥ አንተ መልካም ድምፅ እንዳለው እንደሚወደድ መዝሙር ማለፊያም አድርጎ እንደሚጫወቱት በገና ሆነህላቸዋል ስለዚህም ቃልህን ይሰማሉ ነገር ግን አንዳቸውም አያደርጉትም። +\v 33 እነሆ፥ ይህ ይመጣል በመጣም ጊዜ እነርሱ ነቢይ በመካከላቸው እንደ ነበረ ያውቃሉ።" + +\s5 +\c 34 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ በእስራኤል እረኞች ላይ ትንቢት ተናገር፥ እረኞችንም እንዲህ በላቸው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ራሳቸውን ለሚያሰማሩ ለእስራኤል እረኞች ወዮላቸው! እረኞች በጎችን ያሰማሩ ዘንድ አይገባቸውምን? +\v 3 ጮማውን ትበላላችሁ ጠጕሩንም ትለብሳላችሁ! ከመንጋው መካከል የወፈሩትን ታርዳላችሁ! በጎቹን ግን ፈጽሞ አታሰማሩም። + +\s5 +\v 4 የደከመውን አላጸናችሁትም የታመመውንም አላከማችሁትም የተሰበረውንም አልጠገናችሁትም የባዘነውንም አልመለሳችሁትም የጠፋውንም አልፈለጋችሁትም በኃይልና በጭቈናም ገዛችኋቸው። +\v 5 ያለ እረኛም በማጣት ተበተኑ፥ ከተበተኑም በኋላ ለምድር አራዊት ሁሉ መብል ሆኑ። +\v 6 በጎቼ በተራሮች ሁሉና በረዘሙ ኮረብቶች ሁሉ ላይ ተቅበዝብዘዋል፥ በምድርም ፊት ሁሉ ላይ ተበትነዋል። የሚፈልጋቸውም የለም። + +\s5 +\v 7 ስለዚህ፥ እረኞች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ +\v 8 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ ሕያው ነኝና እረኛ ስለሌለ እረኞቼም በጎቼን ስላልፈለጉ እረኞችም ራሳቸውን እንጂ በጎቼን ስላላሰማሩ፥ በጎቼ ንጥቂያና፥ ለምድር አራዊት ሁሉ መብል ሆነዋልና + +\s5 +\v 9 ስለዚህ፥ እረኞች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ +\v 10 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በእረኞች ላይ ነኝ፥ በጎቼንም ከእጃቸው እፈልጋለሁ፥ በጎቼንም ከማሰማራት አስተዋቸዋለሁ። ከዚያም ወዲያ እረኞች ራሳቸውን አያሰማሩም በጎቼንም ከአፋቸው አድናለሁ፥ መብልም አይሆኑላቸውም። + +\s5 +\v 11 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና። እነሆ፥ እኔ ራሴ በጎቼን እሻለሁ አሰማራቸውማለሁ። +\v 12 እረኛ በተበተኑት በጎች መካከል ባለ ጊዜ መንጋውን እንደሚፈልግ፥ እንዲሁ በጎቼን እፈልጋለሁ በደመናና በጨለማ ቀን ከተበተኑት ስፍራ ሁሉ አድናቸዋለሁ። +\v 13 ከአሕዛብም መካከል አወጣቸዋለሁ ከአገሮችም እሰበስባቸዋለሁ፥ ወደ ገዛ አገራቸውም እሰበስባቸዋለሁ። በእስራኤልም ተራሮች ላይ በፈሳሾችም አጠገብ በምድርም ላይ ሰዎች በሚኖሩበት ስፍራ ሁሉ አሰማራቸዋለሁ። + +\s5 +\v 14 በመልካም ማሰማርያ እሰማራቸዋለሁ የእስራኤል ረጃጅም ተራሮች የግጦሽ ቦታቸው ይሆናል። በዚያ በለመለመ መስክ በመልካምም የግጦሽ ሥፍራ ያርፋሉ፥ በእስራኤልም ተራሮች ላይ ይግጣሉ። +\v 15 እኔ ራሴ በጎቼን አሰማራለሁ አስመስጋቸውማለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ +\v 16 የጠፋውንም እፈልጋለሁ የባዘነውንም እመልሳለሁ የተሰበረውንም እጠግናለሁ የደከመውንም አጸናለሁ የወፈረውንና የበረታውንም አጠፋለሁ! በመልካም አሰማራለሁ። + +\s5 +\v 17 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እናንተም መንጋዬ ሆይ፥ እነሆ፥ በበግና በበግ መካከል፥ በአውራ በግና በአውራ ፍየልም መካከል፥ እፈርዳለሁ። +\v 18 የቀረውን ማሰማርያችሁን በእግራችሁ የረገጣችሁት፥ በመልካሙ ማሰማርያ መሰማራታችሁ አልበቃ ብሏችሁ ነው? የቀረውንስ ውኃ በእግራችሁ ያደፈረሳችሁት፥ ጥሩውን ውኃ መጠጣታችሁ አልበቃ ብሏችሁ ነው? +\v 19 በጎቼም በእግራችሁ በረገጣችሁት ይሰማራሉ በእግራችሁም ያደፈረሳችሁትን ይጠጣሉ። + +\s5 +\v 20 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላቸዋል፥ እነሆ፥ እኔ በወፈሩት በጎችና በከሱት በጎች መካከል እፈርዳለሁ። +\v 21 ይህም እስክትበትኑአቸው ድረስ በእንቢያና በትከሻ ስለምትገፉአቸው የደከሙትንም ሁሉ በቀንዳችሁ ስለምትወጉአቸው ነው። + +\s5 +\v 22 ስለዚህ መንጋዬን አድናለሁ፥ ከእንግዲህ ወዲህም ለንጥቂያ አይሆኑም። በበግና በበግ መካከልም እፈርዳለሁ። +\v 23 በላያቸውም አንድ እረኛ አቆማለሁ እርሱም ያሰማራቸዋል፥ እርሱም ባሪያዬ ዳዊት ነው! ያሰማራቸዋል እረኛም ይሆናቸዋል። +\v 24 እኔም እግዚአብሔር አምላክ እሆናቸዋለሁ ባሪያዬም ዳዊት በመካከላቸው አለቃ ይሆናል እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ። + +\s5 +\v 25 የሰላምን ቃል ኪዳን ከእነርሱ ጋር እገባለሁ ክፉዎችንም አራዊት ከምድሪቱ አጠፋለሁ፥ በጎቼም ተጠብቀው በምድረ በዳ ይኖራሉ በዱርም ውስጥ ይተኛሉ። +\v 26 በእነርሱና በዙሪያ ባሉ ኮረብቶቼ በረከቴን አፈሳለሁ፥ ዝናቡንም በጊዜው እልካለሁ። ይህም የበረከት ዝናብ ይሆናል። +\v 27 የምድረ በዳም ዛፍ ፍሬውን ይሰጣል ምድርም ቡቃያዋን ትሰጣለች፥ በጎቼ በምድራቸው ተዘልለው ይኖራሉ የቀንበራቸውንም ማነቆ በሰበርሁ ጊዜ ከሚገዙአቸውም እጅ ባዳንኋቸው ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 28 እንግዲህም ለአሕዛብ ንጥቂያ አይሆኑም የምድርም አራዊት አይበሉአቸውም ተዘልለውም ይቀመጣሉ የሚያስፈራቸውም የለም። +\v 29 መልካም የእርሻ ቦታ አዘግዝጅላቸዋልሁ፥ ከእንግዲህም ከራብ የተነሣ በምድሪቱ አያልቁም አሕዛብም ከእንግዲህ ወዲህ አይሰድቧቸውም። + +\s5 +\v 30 እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው ከእነርሱ ጋር እንዳለሁ ያውቃሉ። የእስራኤል ቤት ሕዝቤ እነርሱ ህዝቤ ናቸው ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 31 እናንተም በጎቼ፥ የማሰማርያዬ በጎች፥ ህዝቤ ናችሁ እኔም አምላካችሁ እሆናለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር" + +\s5 +\c 35 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን ወደ ሴይር ተራራ አድርግ፥ ትንቢትም ተናገርበት፥ +\v 3 እንዲህም በለው 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የሴይር ተራራ ሆይ፥ እነሆ፥ በአንተ ላይ ነኝ፥ በእጄ እመታሀለሁ ባድማና ድንጋጤ አደርግሃለሁ። + +\s5 +\v 4 ከተሞችህንም አፈራርሳቸዋለሁ፥ አንተም ባድማ ትሆናለህ፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃለህ። +\v 5 ለእስራኤልን ህዝብ ሁል ጊዜ ጥላቻ ስላለህ በመከራቸውም ጊዜ በጽኑ ቅጣት በተቀጡበት ጊዜ የእስራኤልን ልጆች በሰይፍ እጅ ጥለሃቸዋልና +\v 6 ስለዚህ እኔ ሕያው ነኝና ለደም መፋሰስ አሳልፌ እሰጥሃለሁ ደም መፋሰስም ያሳድድሃል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር ደም መፋሰስን ስላልጠላህ ደም መፋሰስ ያሳድድሃል። + +\s5 +\v 7 በእርሱ የሚያልፈውንም ሆነ ወደ እርሱ የሚመለስ እንዳይኖሬ በማድረግ የሴይርን ተራራ ውድማ አደርገዋለሁ ። +\v 8 ተራሮቹንም በተገደሉት ሰዎች እሞላለሁ በኮረብቶችህና በሸለቆችህ በፈሳሾችህም ሁሉ ላይ በሰይፍ የተገደሉት ሁሉ ይወድቃሉ። +\v 9 ለዘላለምም ባድማ አደርግሃለሁ ከተሞችህም ሰው የማይኖርባቸው ይሆናሉ፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 10 አንተ፥ "እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋሬ ቢሆንም እነዚህ ሁለቱ ሕዝቦች እነዚህም ሁለቱ አገሮች ለእኔ ይሆናሉ እኛም እንወርሳቸዋለን" ብለሃል። +\v 11 ስለዚህ እኔ ሕያው ነኝና እንደ ቍጣህ መጠን እነርሱንም ጠልተህ እንዳደረግኸው እንደ ቅንዓትህ መጠን እኔ አደርግብሀለሁ፥ በፈረድሁብህም ጊዜ በእነርሱ ዘንድ የታወቅሁ እሆናለሁ ይላል ጌታ እግዚአብሔር ። + +\s5 +\v 12 ስለዚህም እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ታውቃለህ። በእስራኤል ተራሮች ላይ "ፈርሰዋል! መብልም ሆነው ለእኛ ተሰጥተዋል" ብለህ የተናገርኸውን ስድብ ሁሉ ሰምቻለሁ። +\v 13 በአፋህም በእኔ ላይ የተናገርከውን ትምክህት የተሞላ ንግግር ሰምቻለሁ፤ በኔ ላይ ብዙ ነገሮችን ተናገርክ።፥ እኔም ሰምቼዋለሁ። + +\s5 +\v 14 ጌታ እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል። ምድር ሁሉ ደስ ሲላት አንተን ባድማ አደርግሃለሁ። +\v 15 የእስራኤል ቤት ርስት ባድማ ስለ ሆነ አንተ ደስ እንዳለህ፥ እንዲሁ አደርግብሃለሁ። የሴይር ተራራ ሆይ፥ አንተና ኤዶምያስ ሁሉ ሁለንተናውም ባድማ ትሆናላችሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 36 +\p +\v 1 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ለእስራኤል ተራሮች ትንቢት ተናገር እንዲህም በላቸው ፥ 'የእስራኤል ተራሮች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ!' +\v 2 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠላት በእናንተ ላይ "እሰይ! የጥንት ከፍታዎች ለእኛ ርስት ሆነዋል" ብሎአል። +\v 3 ስለዚህ ትንቢት ተናገር እንዲህም በል፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ባድማ በመሆናችሁና ከሁሉም አቅጣጫ ከመጣባችሁ ጥቃት የተነሳ ለሌሎች አሕዛብ ርስት ሆናችኋል፤ የተናጋሪዎች ከንፈር መተረቻና የአሕዛብ ማላገጫም ሆናችኋል። + +\s5 +\v 4 ስለዚህ፥ እናንተ የእስራኤል ተራሮች ሆይ፥ የጌታን የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፥ ጌታ እግዚአብሔር ለተራሮችና ለኮረብቶች፥ ለፈሳሾችና ለሸለቆች ለምድረ በዳዎች ባዶ ለሆኑትም በዙሪያ ላሉት ለቀሩት አሕዛብ ምርኮና መሳቂያ ለሆኑት ከተሞች እንዲህ ይላል +\v 5 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ያሳድዱአትና ይበዘብዙአት ዘንድ በልባቸው ሁሉ ደስታና በነፍሳቸው ንቀት ምድሬን ርስት አድርገው ለራሳቸው በወሰዱ በቀሩት አሕዛብና በኤዶምያስ ሁሉ ላይ በቅንዓቴ እሳት ተናግሬአለሁ +\v 6 ስለዚህ ስለ እስራኤል ምድር ትንቢት ተናገር፥ ለተራሮችና ለኮረብቶችም ለፈሳሾችና ለሸለቆችም እንዲህ በል። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የአሕዛብን ስድብ ስለ ተሸከማችሁ በቅንዓቴና በመዓቴ ተናግሬአለሁ + +\s5 +\v 7 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በዙሪያችሁ ያሉ አሕዛብ ስድባቸውን በእርግጥ ይሸከማሉ ብዬ ምያለሁ። + +\s5 +\v 8 እናንተ የእስራኤል ተራሮች ግን ወደ እናንተ ተመልሰው የሚመጡበት ቀን ቀርቧልና፥ ቅርንጫፎቻችሁን ታቈጠቍጣላችሁ፥ ለሕዝቤ ለእስራኤልም ፍሬአቸሁን ትሰጣላችሁ። +\v 9 እነሆ፥ እኔ ለእናንተ ነኝና ወደ እናንተም እመለከታለሁ፥ እናንተም ትታረሳላችሁ ይዘራባችሁማል። + +\s5 +\v 10 ስለዚህም እናንተ ተራሮች ሆይ በእስራኤል ቤት ሁሉ ሰዎችን አበዛባችኋለሁ። ሁሉም! ከተሞች የሰዎች መኖሪያ ይሆናሉ ባድማዎቹም ስፍራዎች ይሠራሉ። +\v 11 እናንተ ተራሮች ሆይ ሰውንና እንስሳውንም አበዛባችኋለሁ፥ እነርሱም ይበዛሉ ያፈሩማል። ቀድሞ እንደነበራችሁት የሰዎች መኖሪያ አደርጋችኋለሁ፥ ከቀድሞ ይልቅ አበለጥጋችኋለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። +\v 12 በእናንተ ላይ እንዲረማመዱ የሕዝቤን የእስራኤልን ሰዎችን አመጣቸዋለሁ። እነርሱም ይወርሱዋቸዋል ርስትም ትሆኑላቸዋላችሁ፥ ከእንግዲህም የልጆቻቸው ሞት ምክንያት አትሆኑም። + +\s5 +\v 13 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነርሱ "እናንተ ሰው በሊታ ናችሁ የሕዝባችሁም ልጆች አልቀዋል" ብለዋችኋልና +\v 14 ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲያ ሰው በሊታ አትሆኑም፥ ዳግመኛም ሕዝብችሁን በሚሞቱ ሰዎች ምንንያት እንዲያለቅሱ አታደርጉም ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 15 ዳግመኛም የአሕዛብን ስድብ አላሰማብሽም፤ ዳግመኛም የአሕዛብን ስድብ አትሸከሚም፥ ዳግመኛም ሕዝብሽን አታሰናክዪም፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\v 16 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 17 "የሰው ልጅ ሆይ፥ የእስራኤል ቤት በምድራቸው በተቀመጡ ጊዜ በመንገዳቸውና በሥራቸው አረከሱአት፥ መንገዳቸውም በፊቴ እንደ መርገም አደፍ ነበረ። +\v 18 በምድሪቱም ላይ ስላፈሰሱት ደም በጣዖቶቻቸውም ስላረከሱአት መዓቴን አፈሰስሁባቸው። + +\s5 +\v 19 ወደ አሕዛብም በተንኋቸው ወደ አገሮችም ተዘሩ እንደ መንገዳቸውና እንደ ሥራቸው መጠን ፈረድሁባቸው። +\v 20 ወደ ሌሎች ሕዝቦች ሄዱ። በሄዱም ጊዜ ሰዎች ስለነርሱ 'አሁን እነዚህ ከአገራቸው የተፈናቅሉ የእግዚአብሔር ሕዝብ እነዚህ ናቸው?' በማለታቸው ቅዱስ ስሜን አረከሱ። +\v 21 እኔ ግን የእስራኤል ቤት በመጡባቸው በአሕዛብ መካከል ስላረከሱት ስለ ቅዱስ ስሜ ስል ራራሁላቸው። + +\s5 +\v 22 ስለዚህ ለእስራኤል ቤት እንዲህ በል፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ይህን የማደርገው በሄዳችሁበት በአሕዛብ መካከል ሁሉ ስላረከሳችሁት ስለ ቅዱስ ስሜ ነው እንጂ ስለ እናንተ አይደለም። +\v 23 በአሕዛብም ዘንድ የረከሰውን፥ በመካከላቸው ያረከሳችሁትን ስሜን እቀድሰዋለሁ። በዓይናቸውም ዘንድ በተቀደስሁባችሁ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ አሕዛብ ያውቃሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 24 ከአሕዛብም መካከል እወስዳችኋለሁ ከየአገሩም ሁሉ እሰበስባችኋለሁ ወደ ገዛ ምድራችሁም አመጣችኋለሁ። +\v 25 ከእርኩሰታችሁ ሁሉ እንድትነጹም ጥሩ ውኃን እረጭባችኋለሁ። ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ። + +\s5 +\v 26 አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ። +\v 27 መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ በትእዛዜም መሄድ አስችላችኋለሁ ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ። +\v 28 ለአባቶቻችሁም በሰጠኋት ምድር ትኖራላችሁ ሕዝቤ ትሆናላችሁ እኔም አምላካችሁ እሆናለሁ። + +\s5 +\v 29 ከርኵሰታችሁም ሁሉ አድናችኋለሁ እህልንም እጠራዋለሁ አበዛውማለሁ ከእንግዲህም ራብን አላመጣባችሁም። +\v 30 ደግሞም የራብን ስድብ በሕዝቦች መካከል እንዳትሸከሙ የዛፍን ፍሬና የእርሻውን ቡቃያ አበዛለሁ። +\v 31 ከዚያም ክፉውን መንገዳችሁንና መልካም ያይደለውን ሥራችሁንም ታስባላችሁ፥ ስለ በደላችሁና ስለ ርኵሰታችሁም ራሳችሁን ትጸየፋላችሁ። + +\s5 +\v 32 ይህን ያደረኩት ስለ እናንተ ብዬ እንዳይደለ እወቁ-ይላል ጌታ እግዚአብሔር። የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ስለ መንገዳችሁ እፈሩና ተዋረዱ። +\v 33 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ክእርኩሰታችሁ ሁሉ ባነጻኋችሁበት ቀን በከተሞቻችሁ እንድትኖሩ የፈረሱትንም ሥፍራዎች እንደገና እንድትጠግኑ አደርጋችኋለሁ። +\v 34 ባድማ የነበረች ምድር በመንገደኛ ሁሉ ዓይን ባድማ ባል ድረስ ትታረሳለች። + +\s5 +\v 35 ሰዎችም፥ "ባድማ የነበረች ይህች ምድር እንደ ዔድን ገነት ሆናለች የፈረሱት ባድማ የሆኑት የጠፉትም ከተሞች ተመሽገዋል ሰውም የሚኖርባቸው ሆነዋል" ይላሉ። +\v 36 በዙሪያችሁም ያሉ አሕዛብ እኔ እግዚአብሔር የፈረሱትን ስፍራዎች እንደ ሠራሁ ውድማ የሆነውንም እንደገና እንደተከልሁ ያውቃሉ፥ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ፥ እኔም አደርገዋለሁ። + +\s5 +\v 37 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ስለዚህ ደግሞ እንደመንጋ እንዳበዛቸው የእስራኤል ቤት ይጠይቁኛል። +\v 38 ለእግዚአብሔሬእንደ ተለዩ በጎች፥ በበዓላቶችዋ ቀን እንደሚሆኑ እንደ ኢየሩሳሌም በጎች፥ እንዲሁ የፈረሱት ከተሞች በሰዎች መንጋ ይሞላሉ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 37 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም እጅ በላዬ ነበረ እግዚአብሔርም በመንፈሱ አወጣኝ አጥንቶችም በሞሉባት ሸለቆ መካከል አኖረኝ። +\v 2 ዙሪያውን በመካከላቸው እንዳልፍ አደረገኝ፥ እነሆ በሸለቆው ውስጥ እጅግ ብዙ ነበሩ፥ እነሆም፥ እጅግ ደርቀው ነበር። +\v 3 እርሱም፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ እነዚህ አጥንቶች እንደገና በሕይወት ሊኖሩ ይችላሉን?" አለኝ። እኔም። ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ይህን የምታውቀው አንተ ብቻ ነህ!" አልሁ። + +\s5 +\v 4 እርሱም እንዲህ አለኝ፥ "በእነዚህ አጥንቶች ላይ ትንቢት ተናገር እንዲህም በላቸው፥ 'እናንተ የደረቃችሁ አጥንቶች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ሰሙ። +\v 5 ጌታ እግዚአብሔር ለእነዚህ አጥንቶች እንዲህ ይላል። እነሆ፥ መንፈስን አገባባችኋለሁ በሕይወትም ትኖራላችሁ። +\v 6 ጅማትም እሰጣችኋለሁ ሥጋንም አወጣባችኋለሁ በእናንተም ላይ ቁርበትን እዘረጋለሁ ትንፋሽንም አገባባችኋለሁ በሕይወትም ትኖራላችሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። + +\s5 +\v 7 እንዳዘዘኝም ትንቢት ተናገርሁ ስናገርም ፥ እነሆ የሚያናውጥ ድምፅ ሆነ፥ አጥንቶችም አጥንት ከአጥንት ጋር ተቀራረቡ። +\v 8 እኔም አየሁ፥ እነሆም፥ ጅማት ነበረባቸው ሥጋም ወጣ ቁርበትም በላያቸው ተዘረጋ፥ ህይወት ግን አልነበራቸውም። + +\s5 +\v 9 እርሱም፦ የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት ተናገር፥ ለነፋስ ትንቢት ተናገር፥ ለነፋስም 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦' መንፈስ ቅዱስ! ከአራቱ ነፋሳት ዘንድ ና፥ እነዚህም የተገደሉት በሕይወት ይኖሩ ዘንድ እፍ በልባቸው" በል አለኝ። +\v 10 እንዳዘዘኝም ትንቢት ተናገርሁ፥ የእግዚአብሔርም መንፈስ ገባባቸው ሕያዋንም ሆኑ! እጅግም ታላቅ ሠራዊት ሆነው በእግራቸው ቆሙ። + +\s5 +\v 11 እርሱም እንዲህ አለኝ፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ እነዚህ አጥንቶች የእስራኤል ቤት ሁሉ ናቸው። እነሆ! አጥንቶቻችን ደርቀዋል ተስፋችንም ጠፍቶአል ፈጽመንም ተቈርጠናል ብለዋል። +\v 12 ስለዚህ ትንቢት ተናገር እንዲህም በላቸው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሕዝቤ ሆይ፥ እነሆ፥ መቃብራችሁን እከፍታለሁ ከመቃብራችሁም አወጣችኋለሁ፥ ወደ እስራኤልም ምድር እመልሳችኋለሁ! + +\s5 +\v 13 ሕዝቤ ሆይ፥ መቃብራችሁን በከፈትሁ ጊዜ ከመቃብራችሁም ባወጣኋችሁ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። +\v 14 መንፈሴንም በውስጣችሁ አሳድራለሁ፥ እናንተም በሕይወት ትኖራላችሁ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንኩ ባወቃችሁ ጊዜ በገዛ ምድራችሁም እንድታርፉ አደርጋለሁ። እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁ አደርገውማለሁ ይላል እግዚአብሔር። + +\s5 +\v 15 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 16 "አንተ፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ አንድ በትር ውሰድና። 'ለይሁዳና ለባልንጀሮቹ ለእስራኤል ልጆች'ብለህ በላዩ ጻፍ። 'ሌላም በትር ውሰድና 'ለኤፍሬም በትር ለዮሴፍና ለባልንጀሮቹ ለእስራኤል ቤት ሁሉ' ብለህ በላዩ ጻፍ። +\v 17 ከዚያም በእጅህ ውስጥ አንድ እንዲሆኑ ሁልቱንም በትሮች በአንድ ላይ ያዛቸው። + +\s5 +\v 18 ሕዝብህም ፥ 'ይህ የምታደርገው ነገር ምን ማለት እንደሆነ አትነግረንምን? ብለው በተናገሩህ ጊዜ፥ +\v 19 አንተ። 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በኤፍሬም እጅ ያለውን የዮሴፍን በትር ባልንጀሮቹንም የእስራኤልን ነገዶች እወስዳለሁ፥ ከይሁዳ በትር ጋር አጋጥማቸዋለሁ አንድ በትርም አደርጋቸዋለሁ፥ በእጄም ውስጥ አንድ ይሆናሉ' በላቸው። +\v 20 የጻፍክባቸውንም በትሮች በዓይናቸው ፊት በእጅህ ያዛቸው። + +\s5 +\v 21 ከዚያም እንዲህ በላቸው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የእስራኤልን ልጆች ከሄዱባቸው ከአሕዛብ መካከል የምወስድበት ጊዜ ደርሷል ከአካባቢው አገሮች ሁሉ እሰበስባቸዋለሁ ወደ ገዛ ምድራቸውም አመጣቸዋለሁ። +\v 22 በምድሪቱም ውስጥ በእስራኤል ተራሮች ላይ አንድ ሕዝብ አደርጋቸዋለሁ፥ አንድ ንጉሥም በሁላቸው ላይ ይነግሣል ከዚያ ወዲያ ሁለት ሕዝብ አይሆኑም፥ ከዚያ ወዲያም ሁለት መንግሥቶች ሆነው አይለዩም። +\v 23 ከዚያ ወዲያም በጣዖቶቻቸውና በርኵሰታቸው በመተላለፋቸውም ሁሉ አይረክሱም፥ ኃጢአትም ከሠሩባት ዓመፅ ሁሉ አድናቸዋለሁ አነጻቸውማለሁ ሕዝብም ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ። + +\s5 +\v 24 ባሪያዬም ዳዊት በላያቸው ይነግሳል። ለሁሉም አንድ እረኛ ይሆንላቸዋል በፍርዴም ይሄዳሉ ትእዛዜንም ይጠብቃሉ ያደርጓትማል። +\v 25 አባቶቻችሁም በኖሩበት ለባሪያዬ ለያዕቆብ በሰጠኋት ምድር ይኖራሉ እነርሱና ልጆቻቸው የልጅ ልጆቻቸውም ለዘላለም ይኖሩባታል ባሪያዬም ዳዊት ለዘላለም አለቃ ይሆናቸዋል። + +\s5 +\v 26 ከእነርሱ ጋር የሰላምን ቃል ኪዳን አደርጋለሁ፥ ከእነርሱም ጋር የዘላለምም ቃል ኪዳን ይሆናል። እኔም አጸናቸዋለሁ አበዛቸውማለሁም መቅደሴንም ለዘላለም በመካከላቸው አኖራለሁ። +\v 27 ማደሪያዬም በእነርሱ ዘንድ ይሆናል፤ ይሆናል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል። +\v 28 መቅደሴም ለዘላለም በመካከላቸው በሆነ ጊዜ፥ እኔ እስራኤልን ለራሴ የለየሁ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ አሕዛብ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 38 +\p +\v 1 የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፥ +\v 2 "የሰው ልጅ ሆይ፥ ፊትህን በጎግ ላይና በማጎግ ምድር ላይ፥ በሞሳሕና በቶቤል ዋነኛ አለቃ ላይ አቅናበት፥ ትንቢትም ተናገርበት፥ +\v 3 እንዲህም በል፥ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የሞሳሕና የቶቢል ዋነኛ አለቃ ጎግ ሆይ፥ እነሆ፥ እኔ በአንተ ላይ ነኝ። + +\s5 +\v 4 እመልስህማለሁ በመንጋጋህም ልጓም አገባብሃለሁ፥ አንተንና ሠራዊትህንም ሁሉ፥ ፈረሶችንና ፈረሰኞችን የጦር ልብስ የለበሱትን ሁሉ፥ ጋሻና ራስ ቍርን ሰይፍንም ያያዙትን ሁሉ፥ ታላቁን ወገን አወጣለሁ! +\v 5 ጋሻና የራስ ቍርን የለበሱት ፋርስን ኢትዮጵያና ፉጥ ከእነርሱ ጋር ናቸው! +\v 6 ጋሜርንና ጭፍሮቹን ሁሉ፥ በሰሜን ዳርቻም ያለውን የቴርጋማን ቤትና ጭፍሮቹን ሁሉ፥ ብዙዎች ሕዝቦች ከእነርሱ ጋር ናቸው። + +\s5 +\v 7 ተዘጋጅ! አዎ፥ ራስህንና ሠራዊትህን አዘጋጅ አለቃም ሁናቸው። +\v 8 ከብዙ ቀናትም በኋላ ትጠራልህ ክተወሰኑ ዓመታት በኋላ ክሠይፍ እያገገመች ወዳለችው፥ ከብዙ ሕዝቦችም መካከል ተሰብስበው ያለማቋረጥ ባድማ በነበሩት በእስራኤል ተራሮች ላይ ዳግም ወደ ተሰበሰቡ ትሄዳለህ። የምድሪቱ ሕዝብ ግን ከሕዝቦች መካከል ወጥተው ሁሉም ሳይፈሩ ይቀመጡባታል። +\v 9 አንተም ትወጣለህ፥ እንደ ዐወሎ ነፋስም ትመጣለህ አንተና ጭፍሮችህ ሁሉ ከአንተም ጋር ብዙ ሕዝብ ምድሪቱን እንደ ደመና ትሸፍናላችሁ። + +\s5 +\v 10 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በዚያ ቀን በልብህ ታቅዳለህ፥ +\v 11 ክፉ አሳብንም ታስባለህ።' እንዲህም ትላለህ፥ 'ቅጥር ወደሌላቸው መንደሮች እወጣለሁ ተዘልለው ወደሚኖሩ፥ ሁላቸው ሳይፈሩ ያለ ቅጥርና ያለ መወርወሪያ ያለ መዝጊያም ወደሚቀመጡ እገባለሁ +\v 12 ባድማም በነበሩና በቅርቡ ሰዎች በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ላይ፥ ከብትና ዕቃንም ይዘው ከአሕዛብም በተሰበሰቡ ሰዎች በምድርም መካከል በሚኖሩ ሕዝብ ላይ እጄን እዘረጋናምርኮን እማርካለሁ ብዝበዛንም እበዘብዛለሁ ። + +\s5 +\v 13 ሳባና ድዳን የተርሴስም ነጋዴዎች ከወጣት ጦረኞቻችው ሁሉ ጋር እንዲህ ይሉሀል፥ 'የመጣኸው ምርኮን ለመማረክ ነው? ጦርህን የሰበሰብከው ብዝበዛን ለመበዝበዝ ብርንና ወርቅንስ ለመውሰድ፥ ከብትንና ዕቃንስ ለመውሰድ እጅግም ብዙ ምርኮ ለመማረክ ነው?'። + +\s5 +\v 14 ስለዚህም የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት ተናገር ጎግንም እንዲህ በለው፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በዚያ ቀን ሕዝቤ እስራኤል ሳይፈራ በተቀመጠ ጊዜ አንተ ስለእነርሱ አታውቀውምን? +\v 15 አንተም፥ ከአንተም ጋር ብዙ ሕዝብ ሁላቸው በፈረሶች ላይ የተቀመጡ፥ ታላቅ ወገንና ብርቱ ሠራዊት፥ ከሰሜን ዳርቻ ከስፍራችሁ ትመጣላችሁ። +\v 16 ደመና ምድርን እንድሚሸፍን ህዝቤን ታጠቃለህ። ጎግ ሆይ እንዲህ ይሆናል በዓይናቸው ፊት በተቀደስሁብህ ጊዜ አሕዛብ ያውቁኝ ዘንድ በኋለኛው ዘመን በምድሬ ላይ አመጣሃለሁ። + +\s5 +\v 17 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በእነርሱ ላይ እንደማመጣህ በዚያች ዘመን ብዙ ዓመት ትንቢት በተናገሩ በባሪያዎቼ በእስራኤል ነቢያቶች በቀደመው ዘመን ስለ እርሱ የተናገርሁ አንተ አይደለህምን? +\v 18 በዚያም ቀን ጎግ በእስራኤል ምድር ላይ በመጣ ጊዜ መቅሠፍቴ በመዓቴ ይመጣል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 19 በቁጣዬ ትኩሳትና በመዓቴ እሳት ተናግሬአለሁ፥ በእርግጥ በዚያ ቀን በእስራኤል ምድር ጽኑ የምድር መናወጥ ይሆናል። +\v 20 የባሕር ዓሣዎችና የሰማይ ወፎች የምድረ በዳም አራዊት በምድርም ላይ የሚንቀሳቀሱ ተንቀሳቃሾች ሁሉ በምድርም ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ በፊቴ ይንቀጠቀጣሉ። ተራሮችም ይገለባበጣሉ ገደላገደሎችም ይወድቃሉ ቅጥርም ሁሉ ወደ ምድር ይወድቃል። + +\s5 +\v 21 በተራሮቼም ሁሉ በእርሱ ላይ ሰይፍን እጠራለሁ፥ የሰውም ሁሉ ሰይፍ በወንድሙ ላይ ይሆናል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ +\v 22 በቸነፈር፥ በደም ፥በዶፍ ዝናብና የድንጋይ እሳት እፈርድባቸዋለሁ። ድኝም በእርሱና በጭፍሮቹ ከእርሱም ጋር ባሉ በብዙ ሕዝብ ላይ አዘንባለሁ። +\v 23 ታላቅነቴንና ቅዱስ መሆኔን አሳያለሁ በብዙ አሕዛብም ዓይን የታወቅሁ እሆናለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\c 39 +\p +\v 1 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ በጎግ ላይ ትንቢትን ተናገር እንዲህም በል፥ 'ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፥ የሞሳሕና የቶቤል ዋነኛ አለቃ ጎግ ሆይ፥ እነሆ፥ እኔ በአንተ ላይ ነኝ +\v 2 እመልስሃለሁ፥ እነዳህማለሁ፥ ከሰሜንም ዳርቻ እጐትትሃለሁ፥ ወደ እስራኤልም ተራሮች አመጣሃለሁ። +\v 3 ከግራ እጅህም ቀስትህን አስጥልሃለሁ፥ ከቀኝ እጅህም ፍላጾችህን አስረግፍሃለሁ። + +\s5 +\v 4 የአንተና የጭፍሮች ሁሉ ከአንተም ጋር ያሉ ሠራዊትና ወታደሮች ሬሳ ይገኛል። ለሚናጠቁ ወፎች ሁሉና ለምድር አራዊትም መብል አድርጌ እሰጥሃለሁ። +\v 5 አንተ በምድር ፊት ላይ ትወድቃለህ እኔ ተናግሬአለሁና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 6 በማጎግም ላይ ሳይፈሩም በደሴቶች በሚቀመጡ ላይ እሳትን እሰድዳለሁ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 7 ቅዱሱም ስሜ በሕዝቤ በእስራኤል መካከል እንዲታወቅ አደርጋለሁ፥ ቅዱሱንም ስሜን ከእንግዲህ ወዲህ እንዲረክስ አልፈቅድም፤ አሕዛብም እግዚአብሔር፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ እኔ እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። +\v 8 ያልሁት ቀን እነሆ፥ ይመጣል ይሆንማል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር ። + +\s5 +\v 9 በእስራኤልም ከተሞች የሚኖሩ ይወጣሉ፥ የጦር መሣሪያዎችን፥ አላባሽ ጋሻንና ጋሻን፥ ቀስትንና ፍላጻዎችን፥ ጎመድንና ጦርንም ያቃጥላሉ፥ ለሰባት ዓመት በእሳት ያቃጥሉአቸዋል። +\v 10 በጦር መሣሪያው እሳትን ያነድዳሉ እንጂ እንጨትን ከምድረ በዳ አይወስዱም ከዱርም አይቈርጡም የገፈፉአቸውንም ይገፍፋሉ የበዘበዙአቸውንም ይበዘብዛሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 11 በዚያም ቀን በእስራኤል ዘንድ በባሕር ምሥራቅ የሚያልፉበትን ሸለቆ የመቃብርን ስፍራ ለጎግ እሰጣለሁ፥ የሚያልፉትንም ይከለክላል በዚያም ጎግንና ብዛቱን ሁሉ ይቀብራሉ የሸለቆውንም ስም ሐሞንጎግ ብለው ይጠሩታል። + +\s5 +\v 12 ምድሩንም ያጸዱ ዘንድ የእስራኤል ቤት ሰዎች ሰባት ወር ይቀብሩአቸዋል፥ +\v 13 የምድሪቱም ሰዎች ሁሉ ይቀብሩአቸዋል፥ እኔ የምከብርበት የማይረሳ ቀን ይሆንላችኋል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 14 ምድርንም ለማጽዳት በምድሩ ላይ ወድቀው የቀሩትን የሚቀብሩ፥ ዘወትር በምድሩ ላይ የሚዞሩትን ሰዎች ይመድባሉ ስራውንም ከሰባት ወርም በኋላ ይጀምራሉ። +\v 15 በምድሩ ላይ እንዲዞሩ የተመደቡት በሚያልፉብት ጊዜ የሰውን አጥንት ካዩ ፥ ቀባሪዎች መጥተው በሐሞን ጎግ ሸለቆ እስኪቀብሩት ድረስ ምልክት አድርገው ያልፋሉ። +\v 16 ስሟ ሐሞና የሚሰኝ ከተማ በዚያ ትገኛለች። በዚህ መንገድ ምድሪቱን ያጸዳሉ። + +\s5 +\v 17 አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ለወፎች ሁሉና ለምድር አራዊት ሁሉ እንዲህ በላቸው፥ 'ኑ፥ ተከማቹ፥ ሥጋንም ትበሉ ዘንድ ደምንም ትጠጡ ዘንድ በእስራኤል ተራሮች ላይ ወደማርድላችሁ ታላቅ መሥዋዕት፥ ከየስፍራው ሁሉ ተሰብሰቡ። +\v 18 የኃያላኑን ሥጋ ትበላላችሁ የምድርንም አለቆች፥ የአውራ በጎችንና የጠቦቶችን፥ የፍየሎችንና የወይፈኖችን፥ የባሳንን ፍሪዳዎች ሁሉ፥ ደም ትጠጣላችሁ። + +\s5 +\v 19 እኔም ከማርድላችሁ መሥዋዕት እስክትጠግቡ ድረስ ጮማ ትበላላችሁ እስክትሰክሩም ድረስ ደም ትጠጣላችሁ። +\v 20 በሰደቃዬም ከፈረሶችና ከፈረሰኞች፥ ከኃያላንና ከሰልፈኞች ሁሉ ትጠግባላችሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\v 21 ክብሬንም በአሕዛብ መካከል አኖራለሁ አሕዛብም ሁሉ ያደርግሁትን ፍርዴን፥ በላያቸውም ያኖርኋትን እጄን ያያሉ። +\v 22 ከእንግዲህም ወዲያ የእስራኤል ቤት እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። + +\s5 +\v 23 አሕዛብም የእስራኤል ቤት እኔን ባቃለሉበት በኃጢአታቸው ምክንያት እንደ ተማረኩ ያውቃሉ፥ ስለ በደሉኝ እኔም ፊቴን ከእነርሱ ስለ ሸሸግሁ፥ በጠላቶቻቸው እጅ አሳልፌ ሰጠኋቸው፥ እነርሱም ሁሉ በሰይፍ ወደቁ። +\v 24 እንደ ርኵሰታቸውም እንደ መተላለፋቸውም መጠን አደረግሁባቸው ፊቴንም ከእነርሱ ሸሸግሁ። + +\s5 +\v 25 ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ አሁን የያዕቆብን ምርኮ እመልሳለሁ ለእስራኤልም ቤት ሁሉ እራራለሁ፥ ስለ ቅዱስ ስሜም እቀናለሁ። +\v 26 እፍረታቸውንና እኔን የካዱበትን ክህደት ይረሳሉ። ማንም ሳያስፈራቸው በምድራቸው ተዘልለው በተቀመጡ ጊዜ እነዚህን ነገሮች ሁሉ ይረሳሉ። +\v 27 ከአሕዛብም ዘንድ በመለስኋቸው ጊዜ ከጠላቶቻቸውም ምድር በሰበሰብኋቸው ጊዜ በብዙ አሕዛብም ፊት እቀደሳለሁ። + +\s5 +\v 28 እኔም ወደ አሕዛብ አስማርኬአቸዋለሁና፥ ወደ ገዛ ምድራቸውም ሰብስቤአቸዋለሁና እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። ከእነርሱም አንድንም ሰው በአሕዛብ መካከል አልተውኩም። +\v 29 ፊቴንም ከእነርሱ ከእንግዲህ ወዲህ አልሸሽግም መንፈሴን በእስራኤል ቤት ላይ አፍስሻለሁና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\c 40 +\p +\v 1 በተማረክን በሀያ አምስተኛው ዓመት በዓመቱ መጀመሪያ ከወሩ በአሥረኛው ቀን፥ ከተማይቱ ከተመታች በኋላ በአሥራ አራተኛው ዓመት፥ በዚያው ቀን የእግዚአብሔር እጅ በእኔ ላይ ነበረ እርሱም ወደዚያ ወሰደኝ። +\v 2 በእግዚአብሔር ራእይ ወደ እስራኤል ምድር አመጣኝ እጅግም በረዘመ ተራራ ላይ አኖረኝ፥ በዚያም ላይ በደቡብ ወገን እንደ ከተማ ሆኖ የተሠራ ነገር ነበረ። + +\s5 +\v 3 ወደዚያም አመጣኝ፥ እነሆም፥ መልኩ እንደ ናስ መልክ የመሰለ አንድ ሰው በዚያ ነበረ፥ በእጁም የተልባ እግር ገመድና የመለኪያ ዘንግ ነበረ እርሱም በከተማይቱ በር አጠገብ ቆሞ ነበር። +\v 4 ሰውዬውም፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ ወደዚህ ያመጣሁህ ይህን ላሳይህ ስለሆን በዓይንህ እይ በጆሮህም ስማ በማሳይህም ሁሉ ላይ ልብ በል የምታየውንም ሁሉ ለእስራኤል ቤት ንገር አለኝ። + +\s5 +\v 5 እነሆም፥ በቤተመቅደሱ ዙሪያው ቅጥር ነበረ፥ በሰውዬውም እጅ ርዝመቱ ስድስት ክንድ የሆነ የመለኪያ ዘንግ ነበር። እያንዳንዱም ክንድ አንድ ክንድ ከስንዝር ነበረ። ሰውዬውም ቅጥሩን ለካ፤ የቅጥሩም ስፋት አንድ ዘንግ ቁመቱንም አንድ ዘንግ ነበረ። +\v 6 ወደ ምሥራቅ ወደሚመለከተውም በር ሄዶ በደረጃዎቹ ወጣ፥ የመድረኩንም ወለል ለካ፥ ወርዱን አንድ ዘንግ ነበር። +\v 7 የዘበኞቹም ጓዳ ሁሉ ርዝመቱ አንድ ዘንግ፥ ወርዱም አንድ ዘንግ ነበረ በዘበኞቹም ጓዳዎች መካከል አምስት ክንድ ርቀት ነበረ በበሩም ደጀ ሰላም በስተ ውስጥ በኩል የሚገኝ የበሩ የመድረክ ወለል አንድ ዘንግ ነበረ። + +\s5 +\v 8 የበሩን መተላለፊያ ደጅ ለካ ርዝመቱም አንድ ዘንግ ነበር። +\v 9 የበሩን መተላለፊያ ደጅ ለካ፥ ጥልቀቱ አንድ ዘንግ ነበረ። የግንቡንም አዕማድ ወርድ ሁለት ክንድ ነበረ። አድርጎ ለካ ።ይህም በቤተመቅደሱ ትይዩ የሚገኘው ድጅ መተላለፊያ ነበረ። +\v 10 በበሩ አጠገብ የሚገኙት የዘበኛ ጓዳዎች በበሩ በሁለቱም በኩል ሦስት ሦስት ነበሩ፥ የሁሉም መጠን እኩል ነበረ በሁሉም አቅጣጫ የሚለያቸው ግንብም እኩል መጠን ነበረው። + +\s5 +\v 11 ቀጥሎም ሰውዬው የበሩን መግቢያ ወርድ ለካ አሥር ክንድ ሆነ፤ የበሩንም መግቢያ ርዝመት ለካ አሥራ ሦስት ክንድ ሆነ። +\v 12 በእያንዳንዱ በዘበኛ ጓዳ ፊት ከፍታው አንድ ክንድ የሆነ መከለያ ነበረ። የዘበኛ ጓዳዎቹም በሁሉም አቅጣጫ ስድስት ክንድ ከፍታ ነበራቸው። +\v 13 ከአንዱም የዘበኛ ጓዳ ደርብ ጀምሮ እስከ ሌላው ደርብ ድረስ የበሩን ወርድ ሀያ አምስት ክንድ ለካ ይህም ከመጀምሪያው የዘበኞች ጓዳ መግቢያ እስከ ሌላኛው መግቢያ ድረስ ነው። + +\s5 +\v 14 ቀጥሎም በዘበኞች ጓዳ መካከል የሚያልፈውን ግንብ ለካ፤ ስድስት ክንድም ሆነ። እስከ መግቢያው መተላለፊያ ድረስ ለካ ። +\v 15 ከበሩም መግቢያ ፊት ጀምሮ እስከ ውስጠኛው የበሩ መተላለፊያ መጨረሻ ድረስ አምሳ ክንድ ነበረ። +\v 16 በዘበኛ ጓዳዎቹም በበሩ ውስጥ በዙሪያው በነበሩትም በግንቡ አዕማድ ትንንሽ መስኮቶች ነበሩዋቸው። በበሩም ደጅ መተላለፊያ እንደዚያው ነበር። ሁሉም መስኮቶች በውስጥ በኩል ነበሩ። በግንቡም አዕማድ ሁሉ ላይ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጾባቸው ነበር። + +\s5 +\v 17 ቀጥሎም ሰውዬው ወደ ውጭውም አደባባይ አመጣኝ። እነሆም፥ በአደባባዩ ዙሪያ ክፍሎችና ወለል ነበሩ። በወለሉም ላይ ሠላሳ ክፍሎች ነበሩ። +\v 18 ወለሉም እስከ በሮቹ ይደርስ ነበር ስፋቱም እንደ በሮቹ ርዝመት መጠን ነበረ። ይህም ታችኛው ወለል ነበር። +\v 19 ከታችኛውም በር ፊት ጀምሮ እስከ ውስጠኛው በር ፊት ድረስ ያለውን ርቀት ለካ፤ በምስራቅ በኩል አንድ መቶ ክንድ በሰሜኑም በኩል ተመሳሳይ ነበረ። + +\s5 +\v 20 ቀጥሎም ከውጭው አደባባይ በሰሜን በኩል ያለውን በር ርዝመትና ስፋት ለካ። +\v 21 በበሩ በዚህና በዚያ የዘበኛ ጓዳዎቹም ነበሩ፥ በሩና መተላለፊያው ከዋናው በር ልኬታቸው እኩል ነበር- ርዝመቱ አምሳ ክንድ ወርዱም ሀያ አምስት ክንድ ነበረ። + +\s5 +\v 22 መስኮቶቹም ፥መተላለፊያዎቹና የዘንባባ ዛፎቹ ወደ ምሥራቅ እንደሚመለከተው በር ጋር ይዋሰኑ ነበር። ወደ እርሱና ወደ መተላለፊያዎቹ የሚያደርሱ ሰባት ደረጃዎች ነበሩ። +\v 23 በውስጠኛውም አደባባይ በሰሜኑና በምሥራቁ በኩል በሌላው በር አንጻር በር ነበረ፤ ሰውዬውም ከአንዱ በር እስከ በር ድረስ ለካ። ርቀቱም አንድ መቶ ክንድ ነበር። + +\s5 +\v 24 ቀጥሎም ሰውዬው ወደ ደቡቡ መግቢያ አመጣኝ፥ እነሆም፥ ግንቡና መተላለፊያዎቹ ከሌላኛው መውጪያው በር ጋር እኩል ልኬት ነበራቸው። +\v 25 በመግቢያውና በመተላለፊያዎቹ እንደዚያኛው በር አይነት ትንንሽ መስኮቶች ነበሩዋቸው። የድቡቡ በርና መተላልፊያው ርዝመቱ አምሳ ክንድ ወርዱም ሀያ አምስት ክንድ ነበረ። + +\s5 +\v 26 ወደ በሩና መተላለፊያዎቹ የሚያደርሱ ሰባት ደረጃዎች ነበሩ፥ በግንቡም አዕማድ ላይ በሁለቱም ወገን የዘንባባ ዛፍ ተቀርጾባቸው ነበር። +\v 27 በደቡብ በኩል ወደ ውስጠኛው አደባባይ የሚያስገባ መግቢያ ነበረ፥ ሰውዬውም ከዚህኛው በር እስከ ደቡቡ መግቢያ ድረስ ለካ፥ ርቀቱ መቶ ክንድ ነበረ። + +\s5 +\v 28 ቀጥሎም ሰውዬው ከሌላኛው በር እኩል ልኬት ባለው በደቡብ በር በኩል ወደ ውስጠኛው አደባባይ አገባኝ ። +\v 29 የዘበኛ ጓዳዎቹንና የግንቡን አዕማድና መተላለፊያዎቹ ከመጀመሪያዎቹ መግቢያዎች እኩል ነበሩ፤ በመተላለፊያዎቹ ዙሪያ መስኮቶች ነበሩ።ውስጠኛው መግቢያና መተላለፊያው ርዝመቱ አምሳ ክንድ ወርዱም ሀያ አምስት ክንድ ነበረ። +\v 30 በውስጠኛው ግንብ ዙሪያውም መተላለፊያዎች ነበሩ። ርዝመታቸውም ሀያ አምስት ክንድ ወርዳቸውም አምስት ክንድ ነበረ። +\v 31 መተላለፊያዎቹም ወደ ውጭው አደባባይ ይመለከቱ ነበር በግንቡም አዕማድ ላይ የዘንባባ ዛፍ ተቀርጾ ነበር ወደ እርሱም የሚያደርሱ ስምንት ደረጃዎች ነበሩ። + +\s5 +\v 32 ቀጥሎም ከሌሎቹ መግቢያዎች እኩል ልኬት ባለው በምስራቁ በር በኩል ወደ ውስጠኛው አደባባይ አገባኝ። +\v 33 የዘበኛ ጓዳዎቹንና የግንቡን አዕማድ መተላለፊያዎቹ ሌኬታቸው ከሌሎቹ መግቢያዎች እኩል ነበር በዙሪያም መስኮቶች ነበሩ። መግቢያውና መተላልፊያው ርዝመቱም አምሳ ክንድ ወርዱም ሀያ አምስት ክንድ ነበረ። +\v 34 መተላለፊያዎቹም በስተ ውጭ ወዳለው አደባባይ ይመለከቱ ነበር በግንቡም አዕማድ ላይ በዚህና በዚያ ወገን የዘንባባ ዛፍ ተቀርጾ ነበር ወደ እርሱም የሚያደርሱ ስምንት ደረጃዎች ነበሩት። + +\s5 +\v 35 በሰሜንም ወዳለው በር አመጣኝ፥ በሩንም ለካው፤ ልኬቱም ከሌሎቹ በሮች እኩል ነበር። +\v 36 የዘበኛ ጓዳዎቹንና የግንቡን አዕማድ መተላለፊያዎቹ ልኬታቸው ከሌሎቹ በሮች እኩል ነበር በዙሪያውም መስኮቶች ነበሩ። ርዝመቱም አምሳ ክንድ ወርዱም ሀያ አምስት ክንድ ነበረ። +\v 37 መተላለፊያውም ወደ ውጭው አደባባይ ይመለከቱ ነበር በግንቡም አዕማድ ላይ በዚህና በዚያ ወገን የዘንባባ ዛፍ ተቀርጾ ነበር ወደ እርሱም የሚያደርሱ ስምንት ደረጃዎች ነበሩት። + +\s5 +\v 38 በእያንዳኔዱ ውስጠኛ መግቢያ በር ያላቸው ክፍሎች ነበሩ። ይህም የሚቃጠለውን መሥዋዕት የሚያጥቡበትነበር። +\v 39 የሚቃጠለውንም መሥዋዕት የኃጢአቱንና የበደሉንም መሥዋዕት ያርዱባቸው ዘንድ፥ በበሩ መተላለፊያ በዚህ ወገን ሁለት ገበታዎች፥ በዚያም ወገን ሁለት ገበታዎች ነበሩ። + +\s5 +\v 40 በሰሜን በኩል ባለው በር በስተ ውጭው፥ በመወጣጫው ደረጃዎች አጠገብ፥ በአንድ ወገን ሁለት ገበታዎች ነበሩ፥ በሌላውም ወገን በበሩ መተላለፊያ በኩል ሁለት ገበታዎች ነበሩ። +\v 41 በበሩ በሁለቱም ወገን አራት ገበታዎች ነበሩ፤ በስምንቱም ገበታዎች እንስሳትን ይሰው ነበር። + +\s5 +\v 42 ለሚቃጠለውም መሥዋዕት ርዝመታቸው አነድ ክንድ ተኩል ወርዳቸውም አንድ ክንድ ተኩል ቁመታቸውም አንድ ክንድ የሆኑ ከተጠረበ ድንጋይ የተሠሩ አራት ገበታዎች ነበሩ። በእነርሱም ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና ሌላ መሥዋዕቱን የሚያርዱበትን መሳሪያ ያኖሩባቸው ነበር። +\v 43 በዙሪያውም በመተላለፊያው አንድ ጋት የሚርዝም መስቀያዎችነበሩ፥ የመስዋዕቱም ሥጋ የሆነ ክፈፍ በገበታዎቹም ላይ ይቀመጡ ነበር። + +\s5 +\v 44 በውስጠኛው አደባባይ ከውስጠኛው መግቢያም አጠገብ የዘማሪያን ክፍሎች ነበሩ። ከክልሎቹ አንዱ በሰሜን በኩል ነበረ፥ ሌላውም በስተደቡብ ነበረ። +\v 45 ሰውዬውም፥ "ይህ ወደ ደቡብ የሚመለከት ቤት በመቅደሱ ውስጥ ለማገልገል ተረኛ ለሆኑለሚተጉ ካህናት ነው። + +\s5 +\v 46 ወደ ሰሜንም የሚመለከተው ቤት በመሠዊያው ዙሪያ ለሚያገለግሉ ካህናት ነው። እነዚህ ከሌዊ ልጆች መካከል ያገለግሉት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡ የሳዶቅ ልጆች ናቸው" አለኝ። +\v 47 ቀጥሎም አደባባዩን ለካ፥ አራት ማዕዘን ሆኖ ርዝመቱን መቶ ክንድ ወርዱንም መቶ ክንድ ነበረ መሠዊያውም በቤቱ ፊት ነበረ። + +\s5 +\v 48 ከዚያም ሰውዬው ወደ ቤቱ መተላለፊያ አመጣኝ፥ የግንብ አዕማዱንም ለካ፤ ወርድ በዚህ ወገን አምስት ክንድ በዚያም ወገን አምስት ክንድ ነበረ። መግቢያው ራሱ ወርዱ አሥራ አራት ክንድ ነበረ፥ በበሩም በዚህ ወገንና በዚያ ወገን የነበሩት ግንቦች ስፋት ሦስት ሦስት ክንድ ነበር። +\v 49 የቤተ መቅደሱ መተላለፊያ ርዝመት ሀያ ክንድ ወርዱም አሥራ ሁለት ክንድ ነበረ። ወደ እርሱም የሚያደርሱ ደረጃዎች በሁለቱም አቅጣጫ የቆሙ አዕማድ ነበሩ። + +\s5 +\c 41 +\p +\v 1 ከዚያም ሰውዬው ወደ መቅደሱም ቅዱስ ስፍራ አገባኝ፥ የግንቡንም አዕማድ ወርድ በዚህ ወገን ስድስት ክንድ በዚያም ወገን ስድስት ክንድ አድርጎ ለካ። +\v 2 የመግቢያውም ወርድ አሥር ክንድ ነበረ፥ የመግቢያውም መቃኖች በዚህ ወገን አምስት ክንድ በዚያም ወገን አምስት ክንድ ነበሩ።ቀጥሎም ሰውዬው ቅዱስ ስፍራውን ርዝመቱ አርባ ክንድ ወርዱም ሀያ ክንድአድርጎ ለካ። + +\s5 +\v 3 ከዚያም ሰውዬው ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ገባ፥ የመግቢያውንም የግንብ አዕማድ ወርድ ሁለት ክንድ አድርጎ ለካ የመግቢያውም ወርድ ስድስት ክንድ ነበረ። የመግቢያውም ግንብ ወርድ በዚህ ወገን ሰባት ክንድ በዚያም ወገን ሰባት ክንድ ነበረ። +\v 4 የክፍሉንም ርዝመት ወደ መቅደሱ ፊት ለፊት ሀያ ክንድ ወርዱንም ሀያ ክንድ አድርጎ ለካና፥ "ይህ ቅድስተ ቅዱሳን ነው" አለኝ። + +\s5 +\v 5 የመቅደሱንም ግንብ ስድስት ክንድ አድርጎ። በመቅደሱም ዙሪያ ሁሉ ያሉትን የጓዳዎቹን ሁሉ ወርድ አራት ክንድ ነበረ። +\v 6 ጓዳዎቹም አንዱ ከአንዱ በላይ በሦስት ደርብ ነበሩ፥ በእያንዳንዱም ደርብ ሠላሳ ጓዳዎች ነበሩ። በመቅደሱም ግንብ ዙሪያ ድጋፍ የሆኑ መደርደሪያዎች ነበሩ፥ ምክንያቱም በመቅደሱ ግንብ ውስጥ ድጋፎች አልነበሩም። +\v 7 ላይኞቹ ጓዳዎች ከታችኞቹ ጓዳዎች ይበልጡ ነበር ከታችኛውም ደርብ ወደ መካከለኛው ከመካከለኛውም ደርብ ወደ ላይኛው የሚወጣበት ደረጃ ነበረ። + +\s5 +\v 8 በመቅደሱም ዙሪያ የጓዳዎቹም መሠረት የሆነ ከፍ ያለ ወለል እንዳለ አየሁ ቁመቱም ሙሉ ዘንግ የሚያህል ስድስት ክንድ ነበረ። +\v 9 የጓዳዎቹም የውጭው ግንብ ውፍረት አምስት ክንድ ነበረ። በመቅደሱም ጓዳዎች ውጭ የቀረ አንድ ባዶ ስፍራ ነበረ። + +\s5 +\v 10 በዚህም ባዶ ስፍራ በአንድ ወገን የካህናት በረንዳዎች ነበሩ፤ የባዶውም ስፍራ ወርድ በዙሪያ አምስት ክንድ ነበረ። ይህም ባዶ ሥፍራ በመቅደሱ ዙሪያ ወርዱ ሀያ ክንድ ነበረ። +\v 11 በዚህም በባዶው ስፍራ አንዱ በሰሜን በኩል አንዱም በደቡብ በኩል የጓዳዎች መግቢያ ነበረ። የባዶውም ስፍራ ዙሪያ ወርድ አምስት ክንድ ነበረ። + +\s5 +\v 12 በምዕራብም በኩል ባለው ግቢ አንጻር ያለው ህንጻ ስፋቱ ሰባ ክንድ ነበረ። በግቢውም ዙሪያ የነበረ ግንብ ውፍረቱ አምስት ክንድ ርዝመቱም ዘጠና ክንድ ነበረ። +\v 13 የመቅደሱንም ርዝመት መቶ ክንድ፥ የልዩውን ስፍራና ግቢውን ከግንቡ ጋር አንድ መቶ ክንድ አድርጎ ለካ። +\v 14 ደግሞም ከቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት የሚገኘው ግቢ የፊት ለፊት ወርዱ አንድ መቶ ክንድ ነበር። + +\s5 +\v 15 ቀጥሎም ሰውዬው ከቤተ መቅደሱ በስተዋላ ያለውን ህንጻ የምዕራብ ክፍል በዚህና በዚያ ከነበሩት ፎቆች ጋር እንዲሁም ቅዱስ ስፍራውና መድረኩን አንድ መቶ ክንድ አድርጎ ለካ። +\v 16 ውስጠኛዎቹ ግድግዳዎች፥ ጠባቦቹን ጨምሮ መስኮቶቹ እንዲሁም በሶስት ደረጃዎች ያሉ ፎቆች በእንጨት ተለብጠው ነበር። +\v 17 ከደጁም በላይ እስከ ውስጠኛው ክፍል ድረስ፥ በውጭም ግንቡ ሁሉ ውስጡም ውጭውም ተለብጦ ነበር። + +\s5 +\v 18 በኪሩቤልና በዘንባባ ዛፎች ተውቦ ነበር የዘንባባውም ዛፍ ከኪሩብና ከኪሩብ መካከል ነበረ እያንዳንዱም ኪሩብ ሁለት ፊት ነበረው። +\v 19 የሰው ፊት የሚመስለው በአንድ ወገን ወዳለው የዘንባባ ዛፍ ይመለከት ነበር፥ የአንበሳ ፊት የሚመስለው ደግሞ በሌላ ወገን ወዳለው የዘንባባ ዛፍ ይመለከት ነበር። ይህም በዙሪያ ያሉትን ቤቶች አስውቦ ነበር። +\v 20 ከመሬት አንሥቶ እስከ ደጁ አናት ድረስ እና በመቅደሱ ላይ በኪሩቤልና በዘንባባ ዛፎች ተውበው ነበር። + +\s5 +\v 21 የመቅደሱ መቃኖችም አራት ማዕዘን ነበሩ፥ ሁሉም ለእርስ በእርስ ትይዩ ነበሩ። +\v 22 ከቅዱሱ ሥፍራ ፊት ለፊት የሚገኘው ከእንጨት የተሰራው መስዋዕት ቁመቱ ሦስት ክንድ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ወርዱም ሁለት ክንድ ነበር። ማዕዘኖቹም እግሩም አገዳዎቹም ከእንጨት ተሠርተው ነበር። ሰውዬውም ፥ "ይህች በእግዚአብሔር ፊት ያለችው ገበታ ናት" አለኝ። +\v 23 ለተቀደሰው ስፍራና ለቅድስተ ቅዱሳኑ ሁለት መዝጊያዎች ነበሩአቸው። +\v 24 ለእያንዳንዱ መዝጊያም ሁለት ተዘዋዋሪ ሳንቃዎች ነበሩት ለአንዱ መዝጊያ ሁለት ለሌላውም መዝጊያ ሁለት ሳንቃዎች ነበሩት። + +\s5 +\v 25 ግንቦቹን እንዳስዋቡት ዓይነት በእነዚህ በቅዱስ ስፍራው መዝጊያዎች ላይ ኪሩቤልና የዘንባባ ዛፎች ተቀርጸው ነበር፣ በስተ ውጭም ባለው በደጀ ሰላሙ ፊት የእንጨት ጣራ ነበረ። +\v 26 በደጀ ሰላሙም በሁለቱ ወገን በዚህና በዚያ ጠባብ መስኮቶችና የተቀረጹ የዘንባባ ዛፎች ነበሩበት። እነዚህም የመቅደሱም ጓዳዎች ነበሩ ፥ እነርሱም ተንጠልጣይ ጣሪያዎችም ነበሯቸው። + +\s5 +\c 42 +\p +\v 1 በመቀጠልም ሰውዬው በውጭ በሰሜን አቅጣጫ ወደሚገኘው አደባባይ አወጣኝ፥ በልዩውም ስፍራ አንጻርና በሰሜን በኩል ባለው ግቢ ፊት ለፊት ወዳሉ ክፍሎች አመጣኝ ። +\v 2 ክፍሎቹም በፊት ለፊት ገጽታቸው መቶ ክንድ ስፋታቸውም አምሳ ክንድ ነበረ። +\v 3 ከእነዚህ ክፍሎች አንዳንዶቹ ፊታቸው ወደ ግቢው ወስጥ ነበር ከቤተመቅደሱም ሃያ ክንድ ይርቁ ነበር። ባለ ሶስት ደርብ ክፍሎችም ነበሩ። ከላይ ያለው ክፍል ወደታችኛው ክፍሎች ይመለከትና ለእነርሱ ክፍት ነበር መላለፊያ መንገድም ነበረው። የተወሰኑት ክፍሎች ወደ ወደውጪኛው አደባባይ ይመለከቱ ነበረ። + +\s5 +\v 4 ከክፍሎቹም ፊት በስተ ውስጥ ወርዱ አሥር ክንድ ርዝመቱ መቶ ክንድ የሆነ መተላለፊያ ነበረ። የክፍሎቹም መዝጊያዎች ወደ ሰሜን ይመለከቱ ነበር። +\v 5 ነገር ግን መተላለፊያው ከህንጻው መካከለኛና ከታችኛው ክፍል በላይ ቦታቸውን የያዘ በመሆኑ የላይኞቹ ክፍሎች ትንንሽ ነበሩ። +\v 6 በሦስት ደርብ በመስራታቸውና በአደባባዩም እንዳሉት አዕማድ ያሉ፥ አዕማድ ስላልነበሯቸው ላይኞቹ ደርቦች ከመካከለኞቹና ከታችኞቹ ይልቅ ጠባብ ነበሩ + +\s5 +\v 7 የውጪው ግንብ ከክፍሎቹና ከክፍሎቹ ፊት ለፊት ከሚገኘው ክውጭው አደባባይ ትይዩ ይገኛል ፥ ርዝመቱም አምሳ ክንድ ነበረ። +\v 8 በውጪኛው አደባባይ ርዝመቱ ሃምሳ ክንድ ሲሆን በመቅደሱ ፊት የነበሩት ክፍሎች ደግሞ ርዝመታቸው መቶ ክንድ ነበረ። +\v 9 ከእነዚህም ዕቃ ቤቶች በታች በስተ ምሥራቅ በኩል፥ ከውጭው አደባባይ የሚጀምር መግቢያ ነበረ። + +\s5 +\v 10 በምስራቅ በኩል የውጭውን አደባባይ ተከትሎ ከቤተመቅደሱ ውስጠኛ አደባባይ ፊት ለፊት ክፍሎች ነበሩ። +\v 11 በስተ ፊታቸውም የነበረ መንገድ በርዝመቱና በወርዱ በሰሜን በኩል ከነበሩት ክፍሎች ጋር ተመሳሳይ ሲሆን መግቢያዎቻቸውም በቁጥር እኩል ነበሩ። +\v 12 በደቡብም በኩል ልክ በሰሜን በኩል እንዳለው ወደ ክፍሎቹ የሚያስገቡ መግቢያዎች አሉ። በውስጥ በኩል ያለው መተላለፊያ ከበላዩ መግቢያ ያለው ሲሆን መተላለፊያው ወደተለያዩ ክፍሎች ያመሩ ነበር። በምስራቅ በኩል ወደ መተላለፊያው አንደኛው ጫፍ የሚያመራ መግቢያ ነበር። + +\s5 +\v 13 ከዚያም እንዲህም አለኝ፥ "በውጭኛው አደባባይ ፊት ለፊት የሚገኙት የሰሜንና የደቡብ ክፍሎች ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡ ካህናት ከሁሉ ይልቅ የተቀደሰውን ምግብ የሚበሉባቸው የተቀደሱ ክፍሎች ናቸው። ስፍራው ቅዱስ ስለሆን በዚያ የተቀደሰውን ነገር የእህሉን ቍርባን የኃጢአቱንና የበደሉን መሥዋዕት ያስቀምጣሉ። +\v 14 ካህናቱም አንድ ጊዜ ወደዚያ ከገቡ ሲያገለግሉ የሚለብሷቸው ልብሶች ቅዱስ በመሆናቸው ሳያወልቁ ከተቀደሰው ሥፍራ ወደውጭኛው አደባባይ መውጣት የለባቸውም። ስለዚህም ወደ ሕዝቡ ከመጠጋታቸው በፊት ሌላ ልብስ መልበስ አለባቸው። + +\s5 +\v 15 ውስጠኛውንም ቤት ለክቶ በፈጸመ ጊዜ ወደ ምሥራቅ ወደሚመለከት በር አወጣኝና ዙሪያውን ሁሉ ለካ። + +\s5 +\v 16 የምሥራቁን ወገን በመለኪያ ዘንግ አምስት መቶ ክንድ አድርጎ ለካ። +\v 17 የሰሜኑንም ወገን በመለኪያ ዘንግ አምስት መቶ ክንድ አድርጎ ለካ። +\v 18 የደቡቡንም ወገን በመለኪያ ዘንግ አምስት መቶ ክንድ አድርጎ ለካ። +\v 19 ዞረም፥ የምዕራቡንም ወገን በመለኪያ ዘንግ አምስት መቶ ክንድ አድርጎ ለካ። + +\s5 +\v 20 በአራቱ ወገን ለካው። የተቀደሰውንና ያልተቀደሰውን ይለይ ዘንድ ርዝመቱ አምስት መቶ ክንድ ወርዱም አምስት መቶ ክንድ የሆነ ቅጥር በዙሪያው ነበረ። + +\s5 +\c 43 +\p +\v 1 ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በር አመጣኝ። +\v 2 እነሆም፥ የእስራኤል አምላክ ክብር ከምሥራቅ በኩል መጣ፤ ድምፁም እንደ ብዙ ውኆች ያለ ነበር፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር ታበራ ነበር። + +\s5 +\v 3 ያየሁትም ራእይ ከተማይቱን ለማጥፋት በመጣ ጊዜ እንዳየሁትና በኮበር ወንዝ እንዳየሁት አይነት ራእይ ነበረ- እኔም በግምባሬ ተደፋሁ! +\v 4 የእግዚአብሔርም ክብር ወደ ምሥራቅ በሚመለከት በር ወደ መቅደሱ ገባ። +\v 5 መንፈሱም አነሣኝ ወደ ውስጠኛውም አደባባይ አገባኝ እነሆም፥ የእግዚአብሔር ክብር መቅደሱን ሞልቶት ነበር። + +\s5 +\v 6 ሰውዬው በአጠገቤ ቆሞ ሳለ ከመቅደሱ ውስጥ የሚናገረኝን ሌላ ሰው ሰማሁ። +\v 7 እንዲህም አለኝ፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ ይህ በእስራኤል ልጆች መካከል ለዘላለም የምቀመጥበት የዙፋኔ ስፍራና የእግሬ ጫማ መረገጫ ነው፤ ዳግመኛም የእስራኤል ቤትና ነገሥታቶቻቸው በግልሙትናቸውና በጣዖት ማምለኪያ ቦታዎቻቸው ባለው በነገሥታቶቻቸው ሬሳ ቅዱስ ስሜን አያረክሱም፡፡ +\v 8 ከእንግዲህ ግንብ ብቻ በመካከል በማድርግ የጣዖቶቻቸውን መድረክ በመድረኬ አጠገብ፥ የጣዖቶቻቸውን መቃኖች በመቃኔ አጠገብ በማስቀመጥ ቅዱስ ስሜን አያረክሱም። በሠሩትም ርኵሰት ቅዱስ ስሜን አረከሱ ስለዚህ በቍጣዬ አጠፋኋቸው። + +\s5 +\v 9 አሁንም ግልሙትናቸውንና የነገሥታቶቻቸውን ሬሳ ከፊቴ ያርቁ፥ እኔም ለዘላለም በመካከላቸው አድራለሁ! + +\s5 +\v 10 አንተም የሰው ልጅ፥ ከኃጢአታቸው የተነሣ ያፍሩ ዘንድ ለእስራኤል ቤት ራስህ ልትነግራቸው ይገባል። ስለዚህ የቤቱ ዝርዝር መግለጫ ማሰብ አለባቸው። +\v 11 ከሠሩትም ሥራ ሁሉ የተነሣ ቢያፍሩ፥ የቤቱን መልክና ምሳሌውን መውጫውንም መግቢያውንም ሥርዓቱንም ሕጉንም ሁሉ አስታውቃቸው። የቤቱን አሰራርና ሕጉን ሁሉ ይጠብቁ ዘንድ ያደርጉትም ዘንድ በፊታቸው ጻፈው። + +\s5 +\v 12 የቤቱ ሥርዓት ይህ ነው፡ ከተራራው ራስ ጅምሮ በዙሪያው ያለ ዳርቻ ሁሉ እጅግ የተቀደስ ይሆናል። አስተውል! የቤቱ ሥርዓት ይህ ነው። + +\s5 +\v 13 የመሠዊያውም ልክ በረጅም ክንድ ይህ ነው፥ ይህም ማለት አንድ ክንድ ከጋት ነው። በመሰዊያው ዙሪያ ያለው አሸንዳ ቁመቱ አንድ ክንድ ወርዱም አንድ ክንድ ነው። የዙሪያው ጠርዝ አንድ ስንዝር ነው። ይህም የመሰዊያው መሠረት ነው። +\v 14 በመሬቱም ላይ ካለው አሸንዳ ጀምሮ እስከ ታችኛው የመስዊያው እርከን ድረስ ሁለት ክንድ ወርዱም አንድ ክንድ ነው። ከመሰዊያው ትንሹ ጠርዝ እስከ ትልቁ ጠርዝ ድረስ አራት ክንድ፥ የሰፊው ጠርዝ ስፋትም አንድ ክንድ ነው። + +\s5 +\v 15 ለሚቃጠል መስዋዕት የሚያገለግለው በመሰዊያው ላይ ያለው ምድጃ አራት ክንድ ነው፥ በምድጃውም ላይ ጫፋቸው ወደላይ የቆመ ቀንዶች አሉበት። +\v 16 ምድጃውም አራት ማዕዘን ሆኖ ርዝመት አሥራ ሁለት ክንድ ወርዱም አሥራ ሁለት ክንድ ነው። +\v 17 ጠርዙም በአራቱም ማዕዘን አሥራ አራት ክንድ ወርዱም አሥራ አራት ክንድ ነው፥ በዙሪያውም ያለው ክፈፍ ግማሽ ክንድ ነው። አሽንዳውም ወደምስራቅ ከሚያመለክቱት ደረጃዎቹ ጋር ዙሪያውን አንድ ክንድ ነው። + +\s5 +\v 18 ቀጥሎም እንዲህ አለኝ፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ያቀርቡበት ዘንድ ደሙንም ይረጩበት ዘንድ መሰዊያውን በሚሠሩበት ቀን የመሠዊያው ሕግ ይህ ነው። +\v 19 ያገለግሉኝ ዘንድ ወደ እኔ ለሚቀርቡ ከሳዶቅ ዘር ለሚሆኑ ለሌዋውያኑ ካህናት ለኃጢአት መሥዋዕት የሚሆነውን ወይፈን ትሰጣቸዋለህ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 20 ከደሙም ትወስዳለህ፥ በአራቱ ቀንዶቹም በእርከኑም በአራቱ ማዕዘን ላይ በዙሪያውም ባለው ክፈፍ ላይ ትረጨዋለህ እንዲሁ ታነጻዋለህ ታስተሰርይለትማለህ። +\v 21 ለኃጢአትም መሥዋዕት የሚሆነውን ወይፈን ትወስዳለህ፥ በመቅደሱም ውጭ በተዘጋጀለት ስፍራ ታቃጥለዋለህ። + +\s5 +\v 22 በሁለተኛውም ቀን ለኃጢአት መሥዋዕት የሚሆነውን ነውር የሌለበትን አውራ ፍየል ታቀርባለህ፤ ካህናቱም በወይፈኑ ደም እንዳነጹት እንዲሁ መሠዊያውን ያነጹበታል። +\v 23 ማንጻቱንም ከፈጸምህ በኋላ ነውር የሌለበትን ወይፈንና ከመንጋው የወጣውን ነውር የሌለበትን አውራ በግ ታቀርባለህ። +\v 24 በእግዚአብሔርም ፊት ታቀርባቸዋለህ፥ ካህናቱም ጨው ይጨምሩባቸዋል፥ የሚቃጠለውንም መሥዋዕት አድርገው ለእግዚአብሔር ያቀርቡአቸዋል። + +\s5 +\v 25 ለሰባት ቀንም በየዕለቱ ለኃጢአት መሥዋዕት የሚሆነውን አውራ ፍየልን ታቀርባለህ፥ ካህናቱም ነውርም የሌለባቸውን አንድ ወይፈን ከመንጋውም የወጣውን አንድ አውራ በግ ያቀርባሉ። +\v 26 ሰባት ቀን ለመሠዊያው ያስተሰርያሉ ያነጹትማል፥ እንዲሁም ይቀድሱታል። +\v 27 እነዚህ ቀኖችንም መፈጸም አለባቸው፥ በስምንተኛውም ቀን ከዚያም በኋላ ካህናቱ የሚቃጠለውን መሥዋዕታችሁን የደኅንነትንም መሥዋዕታችሁን በመሠዊያው ላይ ያደርጋሉ እኔም እቀበላችኋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\c 44 +\p +\v 1 ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር እንደገና አመጣኝ በሩም በጣም ተዘግቶ ነበር። +\v 2 እግዚአብሔርም፥ "ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ማንም አይገባበትም፥ በጥብቅ የተዘጋውም ለዚህ ነው +\v 3 የእስራኤል አለቃ በውስጡ ተቀምጦ በእግዚአብሔር ፊት እንጀራ ይበላል። በበሩ ደጀ ሰላም መንገድ ይገባል በዚያም መንገድ ይወጣል። + +\s5 +\v 4 ቀጥሎም ከቤቱ ፊት ለፊት በሰሜኑ በር በኩል አመጣኝ። እኔም አየሁ፥ እነሆም፥ የእግዚአብሔር ክብር የእግዚአብሔርን ቤት ሞልቶት ነበር፥ እኔም በግምባሬ ተደፋሁ። +\v 5 እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ ስለ እግዚአብሔርም ቤት ሥርዓትና ሕግ ሁሉ የምናገርህን ሁሉ ልብ አድርግ ሁሉ በዓይንህም ተመልከት በጆሮህም ስማ። የቤቱንም መግቢያ የመቅደሱንም መውጫ ሁሉ ልብ በል። + +\s5 +\v 6 ለዓመፀኛው ለእስራኤል ቤት እንዲህ በል፥ "ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦እናንተ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ +\v 7 እንጀራዬን፥ ስብንና ደምን፥ በምታቀርቡበት ጊዜ በመቅደሴ ውስጥ ይሆኑ ዘንድ ቤቴንም ያረክሱ ዘንድ በልባቸውና በሥጋቸው ያልተገረዙትን እንግዶችን ሰዎች አግብታችኋልና፥ እነርሱም በርኵሰታችሁ ሁሉ ላይ ይጨመሩ ዘንድ ቃል ኪዳኔን አፍርሰዋልና ርኵሰታችሁ ሁሉ ይብቃችሁ። + +\s5 +\v 8 የተቀደሰውን ሥፍራዬን ኃላፊነት ለሌሎች ሰጣችሁ እንጂ ስለእኔ ያለባችሁን ግዴታ አልተወጣችሁም። +\v 9 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በእስራኤል ልጆች መካከል ካሉት ሁሉ በልቡና በሥጋው ያልተገረዘ እንግዳ ሁሉ ወደ መቅደሴ አይግባ። + +\s5 +\v 10 ከእኔ ዘንድ የራቁ፥ እስራኤልም በሳቱ ጊዜ ጣዖታቸውን ተከትለው ከእኔ ዘንድ የሳቱ ሌዋውያን ኃጢአታቸውን ይሸከማሉ። +\v 11 እነርሱ የመቅደሴ በሮች ጠባቂዎች በመቅደሴም ውስጥ አገልጋዮች ናቸው። ለሕዝቡም የሚቃጠለውን መሥዋዕትና ሌላ መሥዋዕቱን ያርዳሉ፥ ያገለግሉአቸውም ዘንድ በፊታቸው ይቆማሉ። +\v 12 ነገር ግን በጣዖቶቻቸውም ፊት መስዋዕት በማቅረባቸው ለእስራኤልም ቤት የኃጢአት ዕንቅፋት ሆነዋል። ስለዚህ ኃጢአታቸውን ይሸከማሉ ብዬ እጄን አንስቼ ምያለሁ ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር! + +\s5 +\v 13 ካህናትም ይሆኑኝ ዘንድ ወደ እኔ አይቀርቡም፥ ወደ ተቀደሰውም ነገሬና ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ነገር አይቀርቡም እፍረታቸውንና የሠሩትንም ርኵሰታቸውን ይሸከማሉ። +\v 14 ነገር ግን ለአገልግሎቱ ሁሉና በእርሱ ውስጥ ለሚደረገው ሁሉ የቤቱ ሥርዓት ጠባቂዎች አደርጋቸዋለሁ። + +\s5 +\v 15 ነገር ግን የእስራኤል ልጆች ከእኔ በራቁ ጊዜ የመቅደሴን ሥርዓት የጠበቁ የሳዶቅ ልጆች ሌዋውያን ካህናት ያገለግሉኝ ዘንድ ወደ እኔ ይቀርባሉ ስቡንና ደሙንም ወደ እኔ ያቀርቡ ዘንድ በፊቴ ይቆማሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። +\v 16 ወደ መቅደሴም ይገባሉ ያገለግሉኝም ዘንድ ወደ ገበታዬ ይቀርባሉ ሥርዓቴንም ይጠብቃሉ። + +\s5 +\v 17 ወደ ውስጠኛውም አደባባይ በር በገቡ ጊዜ የተልባ እግር ልብስ ይልበሱ ወደ ውስጠኛውም አደባባይ በርና ወደ ቤቱ ውስጥ የሱፍ ልብስ ለብሰው መግባት የለባቸውም። +\v 18 በራሳቸው ላይ የተልባ እግር መጠምጠሚያ ይሁን፥ በወገባቸውም ላይ የተልባ እግር ሱሪ ይሁን የሚያልብ ልብስ መልበስ የለባቸውም። + +\s5 +\v 19 ወደ ውጭውም አደባባይ ወደ ሕዝብ ሲወጡ ሲያገለግሉ ለብሰውት የነበረውን ልብስ ማውለቅ አለባቸው፤ በተቀደሰ ልብሳቸው ነክተው ሕዝቡንም እንዳይቀድሱ አውልቀው በተቀደሰውም ክፍል ውስጥ ያስቀምጡት። + +\s5 +\v 20 ራሳቸውንም አይላጩ የራሳቸውንም ጠጕር ይከርከሙ እንጂ ጠጕራቸውን አያሳድጉ። +\v 21 ካህናቱም ሁሉ በውስጠኛው አደባባይ ሲገቡ የወይን ጠጅ አይጠጡ። +\v 22 መበለቲቱንና የተፈታችይቱን አያግቡ ነገር ግን ከእስራኤል ቤት ዘር ድንግሊቱን ወይም የካህን ሚስት የነበረችይቱን መበለት ብቻ ያግቡ። + +\s5 +\v 23 በተቀደሰውና ባልተቀደሰው መካከል ያለውን ልዩነት ለሕዝቤ ያስተምራሉ፥ ንጹሁን ንጹሕ ካልሆነው መለየት እንዲችሉ ያደርጓቸዋል። +\v 24 ክርክርም በሚያጋጥም ጊዜ በህጌ መሰረት ይፍረዱ፤ ፍትሀዊ መሆን አለባቸው። በበዓላቴ ሁሉ ሕጌንና ሥርዓቴን ይጠብቁ፥ ሰንበታቴንም ይቀድሱ። + +\s5 +\v 25 እንዳይረክሱም የአባት ወይም የእናት ወይም የወንድ ልጅ ወይም የሴት ልጅ ወይም የወንድም ወይም ከወንድ ጋር ያሌተኛች እኅት ካልሆን በስተቀር ወደ ሰው ሬሳ አይቅረቡ፤ ያለዚያ ይረክሳሉ። +\v 26 ካህን ከርከሰ ህዝቡ ሰባት ቀን ይቈጠርለት። +\v 27 በመቅደስም ውስጥ ያገለግል ዘንድ ወደ ውስጠኛው አደባባይ ወደ መቅደሱ ከመግባቱ በፊት፥ የኃጢአትን መሥዋዕት ለራሱ ያቅርብ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 28 ይህም ርስት ይሆንላቸዋል፡ እኔ ርስታቸው እሆንላቸዋለሁ! ስለዚህ በእስራኤል ዘንድ ግዛት አትሰጡአቸው እኔ ግዛታቸው ነኝ። +\v 29 የእህሉን ቍርባንና የኃጢአትን መሥዋዕት የበደልንም መሥዋዕት ይበላሉ በእስራኤልም ለእግዚአብሔር የተለየው ነገር ሁሉ ለእነርሱ ይሆናል። + +\s5 +\v 30 ከበኵራቱ ሁሉ የተሻለው ከየዓይነቱ ከቍርባናችሁም ሁሉ የማንሣት ቍርባን ሁሉ ለካህናት ይሆናል፥ በቤታችሁም ውስጥ በረከት ያድር ዘንድ የዱቄታችሁን በኵራት ለካህናቱ ትሰጣላችሁ። +\v 31 ካህናቱ የሞተ ወይም በአውሬ የተሰበረ ፥ ወፍ ወይም እንስሳ ቢሆን፥ አይበሉም። + +\s5 +\c 45 +\p +\v 1 ርስትም አድርጋችሁ ምድሪቱን በዕጣ በምታካፍሉበት ጊዜ ለእግዚአብሔር መባ ታቀርባላችሁ። ይህም መባ የምድሪቱ የተቀደሰ ሥፍራ ሲሆን ርዝመቱ ሀያ አምስት ሺህ ክንድ ወርዱም ሀያ ሺህ ክንድ ይሆናል በዳርቻው ሁሉ ዙሪያውን የተቀደሰ ይሆናል። +\v 2 ከእርሱም ርዝመቱ አምስት መቶ ወርዱም አምስት መቶ ክንድ አራት ማዕዘን የሆነ ቦታ ለመቅደሱ ይሆናል በዙሪያውም ባዶ ስፍራ የሚሆን አምሳ ክንድ ይሆናል። + +\s5 +\v 3 ከዚያ ቦታ ርዝመቱ ሀያ አምስት ሺህ ክንድ ወርዱም አሥር ሺህ ክንድ የሆነ ስፍራ ትለካለህ፤ እርሱም ቅዱስ ስፍራና ቅድስተ ቅዱሳን ይሆንልሀል። +\v 4 ከምድሪቱም እግዚአብሔርን ለሚያገለግሉና ሊያገለግሉትም ወደ እግዚአብሔር ለሚቀርቡት ለካህናት የተለየ ክፍል ይሆናል። ለቤቶቻቸውም የሚሆን ስፍራ ለመቅደስም የሚሆን የተቀደሰ ስፍራ ይሆናል። +\v 5 ርዝመቱም ሀያ አምስት ሺህ ወርዱም አሥር ሺህ የሆነ ስፍራ ለቤቱ አገልጋዮች ለሌዋውያን ይሆናል፥ ለሚቀመጡባቸውም ከተሞች ለራሳቸውም የርስት ይዞታ ይሆናል። + +\s5 +\v 6 ለከተማ የሚሆን ሥፍራም ከተቀደሰው የዕጣ ክፍል አጠገብ ወርዱ አምስት ሺህ ርዝመቱም ሀያ አምስት ሺህ የሆነውን ስፍራ ትለያላችሁ። ይህም ከተማ ለእስራኤል ቤት ሁሉ ይሆናል። +\v 7 ለአለቃ ይዞታ የሆነው የዕጣ ክፍል በተቀደሰው መባና በከተማይቱ ይዞታ አጠገብ በዚህና በዚያ ይሆናል። በምዕራብና በምሥራቅ ይሆናል። ርዝመቱም እንደ አንድ ነገድ ዕጣ ክፍል ሆኖ ከምድሩ ከምዕራቡ ዳርቻ ጀምሮ እስከ ምሥራቁ ዳርቻ ድረስ ይሆናል። + +\s5 +\v 8 ይህም ለእስራኤል አለቃ ይዞታ ይሆንለታል። አለቆቼም ለእስራኤል ቤት ምድሪቱን እንደ ነገዳቸው መጠን ይሰጡአቸዋል እንጂ ሕዝቤን ከእንግዲህ ወዲህ አያስጨንቋቸውም። + +\s5 +\v 9 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የእስራኤል አለቆች ሆይ፥ ይብቃችሁ ግፍንና ብዝበዛን አስወግዱ፥ ፍርድንና ጽድቅንም አድርጉ! ሕዝቤን መቀማት አቁሙ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር! +\v 10 እውነተኛ ሚዛን እውነተኛም የኢፍ መስፈሪያ እውነተኛውም የባዶስ መስፈሪያ ይሁንላችሁ። +\v 11 የኢፍና የባዶስ መስፈሪያ መጠናቸው እኩል ሆኖ የባዶስ መስፈሪያ የቆሮስ መስፈሪያ አንድ አሥረኛ ይሆናል ፥ መስፈሪያው እንደ ቆሮስ መስፈሪያ ይሁን። +\v 12 ሰቅሉም ሀያ አቦሊ ይሁን ሀያ ሰቅል፥ ሀያ አምስት ሰቅል፥ አሥራ አምስት ሰቅል፥ ምናን ይሁንላችሁ። + +\s5 +\v 13 የምታቀርቡት መባ ይህ ነው ከአንድ ቆሮስ መስፈሪያ ስንዴ የኢፍ መስፈሪያ አንድ ስድስተኛ፥ ከአንድም ቆሮስ መስፈሪያ ገብስ የኢፍ መስፈሪያ አንድ ስድስተኛ ትሰጣላችሁ። +\v 14 የዘይቱም ደንብ፥ ከእያንዳንዱ የቆሮስ መስፈሪያ የባዶስን አንድ አሥረኛ ወይም ለእያንዳንዱ ቆሮስ ምክንያቱም አሥር የባዶስ መስፈሪያ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ነው። +\v 15 ውኃም ካለበት ከእስራኤል አውራጃ ከመንጋው ከሁለቱ መቶ አንዱን የበግ ጠቦት ትሰጣላችሁ ይህ ያስተሰርይላችሁ ዘንድ ለእህል ቍርባንና ለሚቃጠል መሥዋዕት ለደኅንነትም መሥዋዕት ይሆናል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\v 16 የአገሩም ሕዝብ ሁሉ ይህን መባ ለእስራኤል አለቃ ይሰጣሉ። +\v 17 በየበዓላቱም በየመባቻውም በየሰንበታቱም በእስራኤልም ቤት ዓመት በዓል ሁሉ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህሉን ቍርባን የመጠጡንም ቍርባን በየመደቡ ማዘጋጀት የአለቃው ይሆናል። እርሱ የእስራኤል ቤት ወክሎ የኃጢአቱን መሥዋዕትና የእህሉን ቍርባን የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የደኅንነቱን መሥዋዕት ያቀርባል። + +\s5 +\v 18 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመጀመሪያው ወር ከወሩም በመጀመሪያው ቀን ነውር የሌለበትን ወይፈን ውሰድ ስለ መቅደሱም የኃጢአት መስዋዕት ታቀርባላችሁ። +\v 19 ካህኑም ከኃጢአቱ መሥዋዕት ደም ወስዶ በመቅደሱ መቃኖችና በመሠዊያው እርከን በአራቱ ማዕዘን በውስጠኛውም አደባባይ በበሩ መቃኖች ላይ ይርጨው. +\v 20 ይህንንም ከወሩ በሰባተኛው ቀን ስለ ሳተውና ስላላወቀው ታደርጋለህ። በዚህ መንገድ ለቤተ መቅድሱ ታስተስርያላችሁ። + +\s5 +\v 21 በመጀመሪያ ወር ከወሩም በአሥራ አራተኛው ቀን የፋሲካን በዓል ታደርጋላችሁ። የሰባት ቀንም በዓል ይሆናል። የቂጣ እንጀራም ትበላላችሁ። +\v 22 በዚያም ቀን አለቃው ለራሱና ለአገሩ ሕዝብ ሁሉ የኃጢአት መሥዋዕት የሚሆነውን ወይፈን ያቀርባል። + +\s5 +\v 23 በበዓሉም በሰባቱ ቀኖች የሚቃጠለውን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር ያቅርብ፡ ሰባቱንም ቀኖች በየዕለቱ ነውር የሌለባቸውን ሰባት ወይፈንና ሰባት አውራ በጎች ያቅርብ ለኃጢአትም መሥዋዕት በየዕለቱ አንድ አውራ ፍየል ያቅርብ። +\v 24 ለአንድም ወይፈን አንድ የኢፍ መስፈሪያ ለአንድም አውራ በግ አንድ የኢፍ መስፈሪያ ለአንድም የኢፍ መስፈሪያ አንድ የኢን መስፈሪያ ዘይት ለእህል ቍርባን ያቅርብ። + +\s5 +\v 25 አለቃው በሰባተኛውም ወር ከወሩም በአሥራ አምስተኛው ቀን በበዓሉ ሰባት ቀኖች፥ የኃጢአቱን መሥዋዕት የሚቃጠለውንም መሥዋዕት የእህሉንም ቍርባን ከዘይቱ ጋር እንዲሁ ያቅርብ። + +\s5 +\c 46 +\p +\v 1 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በውስጠኛው አደባባይ ወደ ምሥራቅ የሚመለከተው በር ሥራ በሚሠራበት በስድስቱ ቀን ተዘግቶ ይቈይ ነገር ግን በሰንበት ቀንና በመባቻ ቀን ይከፈት። +\v 2 አለቃውም በስተ ውጭ ባለው በር በደጀ ሰላሙ መንገድ ገብቶ ካህናቱም የእርሱን የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የደኅንነቱን መሥዋዕት እስኪያቀርርቡ ድረስ በበሩ መቃን አጠገብ ይቁም። ከዚያም በበሩ መድረክ ላይ ሰግዶ ይውጣ ፥ በሩ ግን እስከ ማታ ድረስ አይዘጋ። + +\s5 +\v 3 የአገሩም ሕዝብ በዚያ በር መግቢያ በእግዚአብሔር ፊት በሰንበታትና በመባቻ ይስገዱ። +\v 4 አለቃውም በሰንበት ቀን ለእግዚአብሔር የሚያቀርበው የሚቃጠል መሥዋዕት ነውር የሌለባቸው ስድስት የበግ ጠቦቶች ነውርም የሌለበት አንድ አውራ በግ ይሁን +\v 5 የእህሉም ቍርባን ለአውራ በጉ አንድ የኢፍ መስፈሪያ ይሁን፥ ለጠቦቶቹም የእህል ቍርባን የሚቻለውን ያህል ይሁን፥ ለአንዱም የኢፍ መስፈሪያ አንድ የኢን መስፈሪያ ዘይት ያቅርብ። + +\s5 +\v 6 በመባቻም ቀን ከመንጋው መካከል ነውር የሌለበትን አንድ ወይፈን፥ ነውር የሌለባቸውንም ስድስት ጠቦቶችና አንድ አውራ በግ ያቅርብ +\v 7 ለወይፈኑም አንድ የኢፍ መስፈሪያ ለአውራውም በግ አንድ የኢፍ መስፈሪያ ለጠቦቶቹም እንደ ተቻለው ያህል፥ የእህል ቁርባን እንዲሁም ለአንዱም የኢፍ መስፈሪያ የእህል ቁርባን አንድ የኢን መስፈሪያ ዘይት ያቅርብ። +\v 8 አለቃውም በሚገባበት ጊዜ በበሩ ደጀ ሰላም መንገድ ይግባ በዚያውም ይውጣ። + +\s5 +\v 9 የአገሩ ሕዝብ ግን በየክብረ በዓሉ ቀን ወደ እግዚአብሔር ፊት በመጡ ጊዜ በሰሜን በር በኩል ሊሰግድ የሚገባው በደቡብ በር በኩል ይውጣ፥ በደቡብም በር የሚገባው በሰሜን በር በኩል ይውጣ። በፊት ለፊት ይውጣ እንጂ በገባበቱ በር አይመለስ። +\v 10 በሚገቡበት ጊዜ አለቃው በመካከላቸው ይግባ በሚወጡበትም ጊዜ ይውጣ። + +\s5 +\v 11 በበዓላትም የእህሉ ቍርባን ለወይፈኑ አንድ የኢፍ መስፈሪያ፥ ለአውራ በጉ አንድ የኢፍ መስፈሪያ፥ ለጠቦቶቹም እንደሚቻለው ያህል፥ ለኢፍ መስፈሪያም አንድ የኢን መስፈሪያ ዘይት ይሆናል። +\v 12 አለቃውም በፈቃዱ የሚያቀርበውን መሥዋዕት፥ የሚቃጠለውን መሥዋዕት፥ ወይም በፈቃዱ ለእግዚአብሔር የሚያቀርበውን የደኅንነቱን መሥዋዕት፥ ባቀረበ ጊዜ፥ የምሥራቁን በር ይክፈት፥ በሰንበትም ቀን እንደሚያደርግ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የደኅንነቱን መሥዋዕት ያቅርብ ከዚያም በኋላ ይውጣ፥ ከወጣም በኋላ በሩን ይዝጋ። + +\s5 +\v 13 በየዕለቱም ለሚቃጠል መሥዋዕት ነውር የሌለበትን የአንድ ዓመት በግ ጠቦት ለእግዚአብሔር ታቀርባላችሁ፤ ይህንንም በየማለዳው ታደርጋላችሁ። +\v 14 ከእርሱም ጋር እንደ ቋሚ ሥርዓት የእህልን ቍርባን፥ በኢን መስፈሪያ ሢሶ ዘይት የተለወሰ የኢፍ መስፈሪያ ስድስተኛ እጅ መልካም ዱቄትን፥ በየማለዳው ታቀርባላችሁ። +\v 15 እንዲሁ ዘወትር ለሚቃጠለው መሥዋዕት ጠቦቱንና የእህሉን ቍርባን ዘይቱንም በየማለዳው ያቅርብ። + +\s5 +\v 16 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ አለቃው ከልጆቹ ለአንዱ ከርስቱ ስጦታ ቢሰጥ የልጁ ውርስ ይሆናል። የልጆቹ ንብረት ውርስ ይሆንላቸዋል። +\v 17 ነገር ግን ከባሪያዎቹ ለአንዱ ከርስቱ ስጦታ ቢሰጥ እስከ ነጻነት ዓመት ድረሰ ለእርሱ ይሁን፥ ከዚያም በኋላ ለአለቃው ይመለስ። ርስቱ ግን ለልጆቹ ይሁን። +\v 18 አለቃውም ሕዝቡን ከይዞታቸው ያወጣቸው ዘንድ ከርስታቸው በግድ አይውሰድ ሕዝቤ ሁሉ ከይዞታቸው እንዳይነቀሉ ከገዛ ይዞታው ለልጆች ርስትን ይስጥ። + +\s5 +\v 19 ከዚያም ሰውዬው ወደ ሰሜን ወደሚመለከተው ለካህናት ወደሚሆን ወደ ተቀደሱ ክፍሎች እነሆም፥ በስትምዕራብ በኩል አንድ ስፍራ ነበረ። +\v 20 እርሱም፥ "ካህናቱ ሕዝቡን ለመቀደስ ወደ ውጭው አደባባይ እንዳያወጡ የበደሉን መሥዋዕትና የኃጢአቱን መሥዋዕት የሚቀቅሉበት፥ የእህሉንም ቍርባን የሚጋግሩበት ስፍራ ይህ ነው አለኝ። + +\s5 +\v 21 በውጭው አደባባይ አወጣኝ በአደባባይም ወዳለው በአራቱ ማዕዘን በኩል አሳለፈኝ እነሆም፥ በእያንዳንዱ የአደባባዩ ማዕዘን ሌላ አደባባይ እንዳለ አየሁ። +\v 22 በአደባባዩ በአራቱ ማዕዘን ርዝመቱ አርባ ክንድ ወርዱም ሠላሳ ክንድ የሆነ አደባባይ ነበረ። በማዕዘኑ ላሉ ለእነዚህ ለአራቱ ስፍራዎች አንድ ልኬቱ እኩል ነበረ። +\v 23 በአራቱም ዙሪያ ሁሉ ግንብ ነበረ፥ በግንቡም ሥር በዙሪያው የመቀቀያ ቦታ ነበረ። +\v 24 ሰውዬውም፥ "እነዚህ የቤቱ አገልጋዮች የሕዝቡን መሥዋዕት የሚቀቅሉባቸው ስፍራዎች ናቸው አለኝ። + +\s5 +\c 47 +\p +\v 1 ወደ መቅደሱም መዝጊያ መለሰኝ እነሆም፥ ውኃ ከቤቱ መድረክ በታች ወደ ምሥራቅ ይወጣ ነበር፥ የቤቱ ፊት ወደ ምሥራቅ ይመለከት ነበርና ውኃውም ከመስዊውው በስተቀኝ በኩል ወደ ቤተመቅደሱ ደቡብ አቅጣጫ ይወርድ ነበር። +\v 2 በሰሜኑም በር በኩል አወጣኝ በስተ ውጭ ባለው መንገድ፥ ወደ ምሥራቅ ወደሚመለከት በስተ ውጭ ወዳለው በር መራኝ እነሆም፥ ውኃው ከበሩ ምዕራብ ወገን ይፈስስ ነበር። + +\s5 +\v 3 ሰውዬውም ገመዱን በእጁ ይዞ ወደ ምሥራቅ ወጣ አንድ ሺህም ክንድ ለካ፥ በውኃውም ውስጥ አሻገረኝ፥ ውኃም እስከ ቍርጭምጭሚት ደረሰ። +\v 4 ደግሞ አንድ ሺህ ለካ በውኃውም ውስጥ አሻገረኝ፥ ውኃውም እስከ ጕልበት ደረሰ። ደግሞም አንድ ሺህ ለካ በውኃውም ውስጥ አሻገረኝ፥ ውኃውም እስከ ወገብ ደረሰ። +\v 5 ደግሞ አንድ ሺህ ለካ ልሻገረውም የማልችለው ወንዝ ሆነ ውኃውም ጥልቅ ነበረ፥ የሚዋኝበትም ውኃ ነበረ ሰው ሊሻገረው የማይችለው ወንዝ ነበረ። + +\s5 +\v 6 ሰውዬውም፥ "የሰው ልጅ ሆይ፥ አይተሃልን?" አለኝ። አመጣኝም፥ ወደ ወንዙም ዳር መለሰኝ። +\v 7 በተመለስሁም ጊዜ፥ እነሆ፥ በወንዙ ዳር በዚህና በዚያ እጅግ ብዙ ዛፎች ነበሩ። +\v 8 እርሱም እንዲህ አለኝ፥ "ይህ ውኃ ወደ ምሥራቅ ምድር ይወጣል ወደ ዓረባም ይወርዳል ወደ ጨው ባሕሩም ወደ መልካም ውሃነቱ ይመልሰዋል። + +\s5 +\v 9 ሕያው ነፍስ ያለው ተንቀሳቃሽ ሁሉ ወንዙ በመጣበት ስፍራ ሁሉ በሕይወት ይኖራል ይህም ውኃ በዚያ ስለ ደረሰ ዓሣዎች እጅግ ይበዛሉ። ጨዋማ ባህርን መልካም ያደርጋል። ወንዙም በሚመጣበት ያለው ሁሉ በሕይወት ይኖራል። +\v 10 የዓይንጋዲ አጥማጆችም በወንዙ ዳር ይቆማሉ በዓይንጋዲ መረብ መዘርጊያ ቦታ ይገኛል። በጨው ባህርም ዓሣዎች እንደ ታላቁ ባሕር ዓሣዎች በየወገናቸው እጅግ ይበዛሉ። + +\s5 +\v 11 ነገር ግን የጨው ባህር እረግረጉና እቋሪው ሥፍራ ጨው ለመስጠት ጨዋማ እንደ ሆነ ይኖራል እንጂ አይቀየርም። +\v 12 በወንዙም አጠገብ በዳሩ ላይ በዚህና በዚያ ፍሬው የሚበላ ዛፍ ሁሉ ይበቅላል። ቅጠሉም አይረግፍም ፍሬውም አይቋረጥም። ውኃውም ከመቅደስ የሚመጣ በመሆኑ ዛፎቹ በየወሩ ፍሬ ያፈራሉ። ፍሬውም ለመብል ቅጠሉም ለመድኃኒት ይሆናል። + +\s5 +\v 13 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ርስት አድርጋችሁ ለአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ምድሪቱን የምትከፍሉበት እንደዚህ ነው፡ ለዮሴፍ ሁለት እድል ፈንታ ይሰጠዋል። +\v 14 ለአባቶቻችሁ እሰጣቸው ዘንድ ምዬ ነበርና እናንተ እያንዳንዳችሁ እኩል አድርጋችሁ ትካፈላላችሁ። በዚህም መንገድ ይህች ምድር ርስት ትሆናችኋለች። + +\s5 +\v 15 የምድሪቱም ድንበር ይህ ነው። በሰሜኑ ወገን ከታላቁ ባሕር ጀምሮ በሔትሎን መንገድ ወደ ጽዳድ መግቢያ +\v 16 ሐማት፥ ቤሮታ፥ በደማስቆ ድንበርና በሐማት ድንበር መካከል ያለው ሲብራይም፥ በሐውራን ድንበር አጠገብ ያለው ሐጸርሃቲኮን። +\v 17 ስለዚህም ድንበሩ ከባሕሩ በደማስቆ ድንበር ላይ ያለው ሐጸርዔናን ሐማት ድንበር ይሆናል። ይህ የሰሜኑ ድንበር ነው። + +\s5 +\v 18 የምሥራቁም ድንበር በሐውራን በደማስቆና በገለዓድ በእስራኤልም ምድር መካከል ዮርዳኖስ ይሆናል። ይህም ድንበር እስከ ታማር ድረስ ይሄዳል። +\v 19 የደቡቡም ድንበር ከደቡብ ታማር ጀምሮ እስከ ሜርባ ቃዴስ ውኃ እስከ ግብጽ ወንዝ እስከ ታላቁ ባሕር ድረስ ይሆናል። የደቡቡ ድንበር ይህ ነው። +\v 20 የምዕራቡም ድንበር ከታላቁ ባሕር ጀምሮ እስከ ሐማት መግቢያ አንጻር ድረስ ይሆናል። የምዕራቡ ድንበር ይህ ነው። + +\s5 +\v 21 እንዲሁ ይህችን ምድር እንደ እስራኤል ነገድነታችሁ ለእናንተ ትካፈላላችሁ። +\v 22 ለእናንተና በእናንተ መካከል ለሚቀመጡ በእናንተም መካከል ልጆችን ለሚወልዱ ፥ በእስራኤል ልጆች መካከል እንዳሉ እንደአገር ልጆች ላሉ መጻተኞች ርስት አድርጋችሁ በዕጣ ትካፈሉአታላችሁ ። በእስራኤልም ነገዶች መካከል ለርስት ክፍፍል ዕጣ ትጣላላችሁ። +\v 23 መጻተኛውም በማናቸውም ነገድ መካከል ቢቀመጥ በዚያ ርስቱን ትሰጡታላችሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፦ + +\s5 +\c 48 +\p +\v 1 የነገዶችም ስም ይህ ነው። የዳን ነገድ አንድ የዕጣ ክፍል ይወስዳል፡ ድንብሩም በሔትሎን መንገድ አጠገብ ወደ ሐማት መግቢያ በደማስቆም ድንበር ባለው በሐጸርዔናን በሐማትም አጠገብ በሰሜን በኩል ካለው ከሰሜን ድንበር ይጀምራል። ወርዳቸውም ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ይሆናል። +\v 2 ከዳንም ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለአሴር አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። +\v 3 ከአሴርም ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለንፍታሌም አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። + +\s5 +\v 4 ከንፍታሌም ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለምናሴ አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። +\v 5 ከምናሴም ደቡብ ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለኤፍሬም አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። +\v 6 ከኤፍሬምም ደቡብ ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለሮቤል አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። +\v 7 ከሮቤልም ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለይሁዳ አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። + +\s5 +\v 8 ከይሁዳም ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለመባ የሆነ የዕጣ ክፍል ይሆናል ወርዱ ሀያ አምስት ሺህ ክንድ ይሆናል ርዝመቱም ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ከዕጣ ክፍሎች እንደ አንዱ ይሆናል፥ መቅደሱም በመካከሉ ይሆናል። +\v 9 ለእግዚአብሔር የምታቀርቡት መሬት ርዝመቱ ሃያ አምስት ሺህ ወርዱም ሃያ ሺህ ክንድ ይሆናል። + +\s5 +\v 10 ይዚህም ቅዱስ ስፍራ አገልግሎት ይህ ነው፡ ለካህናቱ በሰሜን በኩል ርዝመቱ ሀያ አምስት ሺህ፥ በምዕራብም በኩል ወርዱ አሥር ሺህ፥ በምሥራቅም በኩል ወርዱ አሥር ሺህ፥ በደቡብም በኩል ርዝመቱ ሃያ አምስት ሺህ ክንድ የሆነ ቦታ ይለይላቸዋል። የእግዚአብሔርም መቅደስ በመካከሉ ይሆናል። +\v 11 ይህም የእስራኤል ልጆች በሳቱ ጊዜ፥ ሌዋውያን እንደ ሳቱት ላልሳቱት ሥርዓቴንም ለጠበቁት ከሳዶቅ ልጆች ወገን ለተቀደሱት ካህናት ይሆናል። +\v 12 ለእነርሱም የሚሆነው መባ እስከ ሌዋውያን ድንበር የሚደርስ የዚህ የተቀደሰ ሥፍራ ክፍል ነው። + +\s5 +\v 13 የሌዋውያን መሬት በካህናቱም ድንበር አንጻር ርዝመቱ ሀያ አምስት ሺህ ወርዱም አሥር ሺህ የሆነ ዕጣ ይሆናል። የእነኚህ ኩታ ገጠም መሬቶች ጠቅላላ ርዝመት ሀያ አምስት ሺህ ወርዱም ሀያ ሺህ ክንድ ይሆናል። +\v 14 ለእግዚአብሔርም የተቀደሰ ነውና ከእርሱ ምንም አይሸጡም አይለውጡምም፥ የምድሩም በኵራት አይፋለስም። + +\s5 +\v 15 የቀረው ሀያ አምስት ሺህ ክንድ ስፋትና አምስት ሺህ ክንድ ርዝመት ያለው ስፍራ ለከተማይቱ የጋራ ጉዳይ ፥ ለመኖሪያና ለማስማርያም ይሆናል ከተማይቱም በመካከሉ ትሆናለች። +\v 16 የከተማይቱም ልኬት ይህ ነው፡ በሰሜን በኩል አራት ሺህ አምስት መቶ፥ በደቡብም በኩል አራት ሺህ አምስት መቶ፥ በምሥራቅም በኩል አራት ሺህ አምስት መቶ፥ በምዕራብም በኩል አራት ሺህ አምስት መቶ ክንድ ይሆናል። + +\s5 +\v 17 ለከተማይቱም በሰሜን በኩል ሁለት መቶ አምሳ፥ በደቡብም በኩል ሁለት መቶ አምሳ፥ በምሥራቅም በኩል ሁለት መቶ አምሳ፥ በምዕራብም በኩል ሁለት መቶ አምሳ ክንድ ጥልቀት ያለው ማሰማርያ ይኖራታል። +\v 18 ቀሪው የተቀደሰው በተቀደሰው የመሬት መባ ርዝመቱ ወደ ምሥራቅ አሥር ሺህ ወደ ምዕራብም አሥር ሺህ ክንድ ይሆናል። ድንበሩም በተቀደሰው የመሬት የተያያዘ ይሆናል። ፍሬውም ከተማይቱን ለሚያገለግሉ ለመብል ይሆናል። + +\s5 +\v 19 ከእስራኤል ነገድ ሁሉ ከተማይቱን የሚያገለግሉ ምድሪቱን ያርሱታል። +\v 20 መባው ሁሉ ርዝመቱ ሀያ አምስት ሺህ ወርዱም ሀያ አምስት ሺህ ክንድ ይሆናል ። በዚህም መንገድ የተቀደሰውን የመሬት መባና የከተማይቱን ይዞታ ታደርጋላችሁ። + +\s5 +\v 21 በተቀደሰው መባና በከተማይቱ ይዞታ በዚህና በዚያ ወገን የቀረው ሥፍራ ለአለቃው ይሆናል። በምስራቅ በኩል ያለው የአለቃው ኩታ ገጠም መሬት ከተቀደሰው የመሬት መባ ሀያ አምስት ሺህ ክንድ ወደ ምሥራቁ ድንበር፥ በምዕራብም በኩል ደግሞ ሀያ አምስት ሺህ ክንድ ወደ ምዕራቡ ድንበር ይዘልቃል። የተቀደሰውም የመሬት መባውና የቤተ መቅደሱ የተቀደሰ ስፍራ በመካከል ይሆናል። +\v 22 የአለቃውም ይዞታው ከሌዋውያን ርስትና ክከተማይቱ ይዞታ መካከል ይሆናል፤ በይሁዳ ድንበርና በብንያም ድንበርም መካከል ይሆናል። + +\s5 +\v 23 ለቀሩትም ነገዶች ድርሻቸው ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ይሆናል። የብንያም ነገድ አንድ የዕጣ ክፍል ይቀበላል። +\v 24 ከብንያምም ደቡባዊ ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለስምዖን አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። +\v 25 ከስምዖንም ደቡባዊ ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለይሳኮር አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። +\v 26 ከይሳኮርም ደቡባዊ ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለዛብሎን አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። + +\s5 +\v 27 ከዛብሎንም ደቡባዊ ድንበር ቀጥሎ ከምሥራቅ ጀምሮ እስከ ምዕራብ ድረስ ለጋድ አንድ የዕጣ ክፍል ይሆናል። +\v 28 ከጋድም ድንበር ቀጥሎ በደቡብ በኩል ድንበሩ ከታማር ጀምሮ እስከ ሜሪባ ቃዴስ ውኃ እስከ ግብጽ ወንዝ እስከ ታላቁ ባሕር ድረስ ይሆናል። +\v 29 ርስት አድርጋችሁ ለእስራኤል ነገዶች በዕጣ የምታካፍሉአት ምድር ይህች ናት፥ ይህም ርስታቸው ይሆናል፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። + +\s5 +\v 30 የከተማይቱም መውጫዎች እነዚህ ናቸው፡ በሰሜን ወገን ልኩ አራት ሺህ አምስት መቶ ክንድ ነው። +\v 31 የከተማይቱ በሮች ሦስት ሲሆኑ እንደ እስራኤል ነገዶች ስም በሰሜን በኩል አንዱ የሮቤል በር አንዱም የይሁዳ በር አንዱም የሌዊ በር ይሆናሉ። +\v 32 በምሥራቁም ወገን አራት ሺህ አምስት መቶ ክንድ በሚረዝመው ሥፍራ፥ ሦስትም በሮች አሉ፡ አንዱ የዮሴፍ በር አንዱም የብንያም በር አንዱም የዳን በር ይሆናሉ። + +\s5 +\v 33 በምስራቅ ወገን አራት ሺህ አምስት መቶ ክንድ በሚረዝመው ሥፍራ፥ ሦስት በሮች አሉ፡ አንዱ የስምዖን ፥አንዱ የይሳኮር፥ እና አንዱም የዛብሎን በር ናቸው። +\v 34 በምዕራቡም ወገን ልኬቱ አራት ሺህ አምስት መቶ ክንድ ሲሆን፥ በዚያ ሦስት በሮች አሉ፡ አንዱ የጋድ፥ አንዱም የአሴር፥ ሌላውም የንፍታሌም በር ናቸው። +\v 35 የከተማይቱ ዙሪያም አሥራ ስምንት ሺህ ክንድ ይሆናል፥ ከዚያም ቀን ጀምሮ የከተማይቱ ስም "እግዚአብሔር በዚያ አለ" ተብሎ ይጠራል።