forked from WA-Catalog/am_ulb
196 lines
22 KiB
Plaintext
196 lines
22 KiB
Plaintext
\id 1TI
|
|
\ide UTF-8
|
|
\h 1 ጢሞቴዎስ
|
|
\toc1 1 ጢሞቴዎስ
|
|
\toc2 1 ጢሞቴዎስ
|
|
\toc3 1ti
|
|
\mt 1 ጢሞቴዎስ
|
|
\s5
|
|
\c 1
|
|
\cl ምዕራፍ 1
|
|
\p
|
|
\v 1 መታመኛችን በሆነው በክርስቶስ ኢየሱስ እና በአዳኛችን በእግዚአብሔር ትእዛዝ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ ጳውሎስ፣
|
|
\p
|
|
\v 2 በእምነት እውነታኛ ልጄ ለሆነው፣ ለጢሞቴዎስ፡፡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ ምሕረትና ሰላም ለአንተ ይሁን፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 3 ወደ መቄዶንያን በሄደኩ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ልዩ ትምህርትን እናዳያስተምሩ፣
|
|
\v 4 በእምነት የሆነውን የእግዚአብሔርን እቅድ ለማያግዙ ለታሪኮችና መጨረሻ የሌላቸውን የትውልዶችን ሐረግ ለመቁጠር ትኩረት ወደ መስጠት እንዳያዘነብሉ ታስጠነቅቃቸው ዘንድ በኤፌሶን እንድትቀመጥ አዘዝኩህ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 5 ነገር ግን የትእዛዙ ግብ ከንጹህ ልብ፣ ከመልካም ኅሊና እና ከእውነተኛ እምነት የሚወጣ ፍቅር ነ|ው፡፡
|
|
\v 6 አንዳንድ ሰዎች ከእነዚህ ነገሮች ርቀው ወደ ባዶ ወሬ ዞረዋል፡፡
|
|
\v 7 የሕግ አስተማሪዎች ለመሆን ተመኝተዋል፤ ነገር ግን የሚናገሩትንና መሆን አለበት የሚሉትን ነገር አያውቁትም፡፡
|
|
\v 8 ሆኖም ሕግ በትክክል ቢጠቀምበት መልካም እንደሆነ እናወቃለን፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 9 እንዲሁም ሕግ ለጻድቅ ሰው እንዳልተሠራ እናውቃለን፤ ነገር ግን ሕግ የተሰጠው፣ ሕገወጥ ለሆኑና ለአመጸኞች ሰዎች ፣ እግዚአብሔርን ለማይፈሩና ለኃጢአተኞች ፣
|
|
\v 10 ለአመንዝሮችና ለግብረ ሰዶማውያን፣ ሰዎችን ባርያ አድርገው ለሚሸጡ፣ ለውሸተኞች፣ ለሐሰት ምስክሮች፣ ከእውነተኛው ትምህርት ርቀው ለሚገኙ ሰዎች ነው፡፡
|
|
\v 11 ይህ እውነተኛ ትምህርት በተባረከው አምላካችን ለእኔ በአደራ የተሰጠው ወንጌል ነው፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 12 ለዚህ አገልገሎት ታማኝ እንድሆን ያበቃኝንና የሾመኝን፣ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰግናለሁ፡፡
|
|
\v 13 ምንም እንኳ አስቀድሞ ተሳዳቢና አሳዳጅ ብሆንም፣ ባለማወቅና ባለማመን ስላደረግሁት ከጌታ ዘንድ ምሕረትን አግኝቼአለሁ፡፡
|
|
\v 14 ነገር ግን የጌታችንም ጸጋ በክርስቶስ ኢየሱስ ከእምነትና ከፍቅር ጋር ይበልጥ በዛ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 15 ‹‹ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም መጣ›› የሚለው መልዕክት ሁሉም ሊቀበሉት የተገባና አስተማማኝ ነው፡፡ እኔም ከእነዚህ ሁሉ የባስኩ ኃጢአተኛ ነኝ፡፡
|
|
\v 16 በዚህም ምክንያት ከኃጢአተኞች ዋነኛ በምሆን በእኔ ክርስቶስ ኢየሱስ ትእግስቱን ሁሉ ሊያሳይ ምሕረትን አገኘሁ፤ ይህም የሆነው በእርሱ ለሚያምኑና የዘላለም ሕይወት ለሚያገኙ ምሳሌ እሆን ዘንድ ነው፡፡
|
|
\v 17 ስለዚህ ለዘላለም ንጉሥ ፣ ለማይሞተው እና ለማይታየው፣ ብቻውን አምላክ ለሆነው፣ ክብርና ግርማ ለዘላለም ይሁን፡፡ አሜን፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 18 ልጄ ጢሞቴዎስ ሆይ፣ ስለ አንተ አስቀድሞ በተነገረው ትንቢት ተስማምቼ ይህን አዝሃለሁ፤ መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፤
|
|
\v 19 ስለዚህም እምነትና መልካም ኅሊና ይኑርህ፡፡ አንዳንድ ሰዎች እነዚህን ክደው መርከብ አለመሪ እንደሚጠፋ በእምነት ነገር ጠፍተዋል፡፡
|
|
\v 20 ከእነዚህም መካከል በእግዚአብሔር ላይ የስድብን ቃል እንዳይናገሩ፣ ለሰይጣን አሳልፌ የሰጠኋቸው፣ ሄሜኔዎስ እና እስክንድሮስ ይገኙባቸዋል፡፡
|
|
\s5
|
|
\c 2
|
|
\cl ምዕራፍ 2
|
|
\p
|
|
\v 1 ስለዚህ ከሁሉ በፊት፣ ጸሎት፣ ምልጃና ምሥጋና ስለ ሰዎቸ ሁሉ እንዲደረግ እመክራለሁ፤ እግዚአብሔርን በመፍራትና በማክበር፣
|
|
\v 2 በጸጥታ ሕይወት ሰላማዊ ኑሮ እንድንኖር፣ ለነገሥታትና በሥልጣን ላይ ላሉ ሁሉ ጸልዩ፡፡
|
|
\v 3 ይህም በአዳኛችን በእግዚአብሔር ፊት መልካምና ተቀባይነት ያለው ነገር ነው፡፡
|
|
\v 4 እርሱ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑና እውነትን ሁሉ ወደ ማውቅ እንዲደርሱ ይፈልጋልና፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 5 አንድ እግዚአብሔር አለና፣ እንዲሁም በሰዎችና በእግዚአብሔር መካከል፣ ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ አንድ መካከለኛ አለ፤
|
|
\v 6 እርሱም ለሁሉ ራሱን ቤዛ አድርጎ የሰጠ፣ በትክክለኛው ጊዜ የተገለጠ ምስክር ነው፡፡
|
|
\v 7 ለዚህም ዓላማ እኔ ራሴ፣ አወጅ ነጋሪና ሐዋርያ ሆኜአለሁ፡፡ እውነትን እናገራለሁ አልዋሽም፤ እኔ ለአሕዛብ የእምነትና የእውነት አስተማሪ ነኝ፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 8 ስለዚህ፣ ወንዶች ሁሉ በየሥፍራው ያለ ጥርጥርና ያለ ቁጣ የተቀደሱ እጆቻቸውን እያነሱ እንዲጸልዩ እፈልጋለሁ፡፡
|
|
\v 9 እንደዚሁም፣ ሴቶች አግባብ ያለው አለባበስ ይኑራቸው፣ ራሳቸውን በመግዛት ረጋ እንዲሉ እንጂ ጸጉራቸውን በወርቅ ወይም በዕንቁ በመሥራት ወይም ውድ የሆኑ ልብሶችን በመልበስ ሊያጌጡ አይገባም፡፡
|
|
\v 10 ነገር ግን እግዚአብሔርን ለሚፈሩ ሴቶች አግባብ እንደሆነው፣ በመልካም ሥራ ተውበው ይታዩ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 11 ሴት በጸጥታና በመታዘዝ ትማር፡፡
|
|
\v 12 ሴት በጸጥታ እንድትኖር እንጂ፣ እንድታስተምርና በወንድ ላይ ሥልጣን እንዲኖራት አልፈቅድም፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 13 አስቀድሞ አዳም ተፈጥሮአልና፣ ከዚያም ሔዋን፡፡
|
|
\v 14 አዳም አልተታለለም፣ ነገር ግን ሴቲቱ ሙሉ ለሙሉ በመተላለፍ ተታልላለች፡፡
|
|
\v 15 ሆኖም፣ በእምነትና በፍቅር፣ በቅድስናም በመልካም አዕምሮ ጸንታ ብትኖር፣ ልጆችን በመውለድ ትድናለች፡፡
|
|
\s5
|
|
\c 3
|
|
\cl ምዕራፍ 3
|
|
\p
|
|
\v 1 አንድ ሰው መሪነትን ቢፈልግ፣ መልካምን ሥራ ተመኝቶአል፣ የሚለው አባባል የታመነ ነው፡፡
|
|
\v 2 ስለዚህ መሪው ነቀፋ የሌለበት፣ የአንዲት ሚስት ባል፣ በመጠን የሚኖር፣ አስተዋይ፣ ሥርዓት ያለው፣ እንግዳ ተቀባይ፣ ለማስተማር የሚበቃ፣
|
|
\v 3 የማይሰክር፣ የማይጨቃጨቅ፣ ነገር ግን፣ ለሌሎች የሚጠነቀቅ፣ ሰላማዊ፣ ገንዘብን የማያፈቅር መሆን አለበት፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 4 ቤቱን በመልካም የሚያስተዳድርና ልጆቹም በሁሉም ረገድ የሚታዘዙለት ለሆን ይገባል፤
|
|
\v 5 ሰው የራሱን ቤት በመልካም ማስተዳደር የማያውቅ ከሆነ ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንዴት ሊጠነቀቅ ይችላል?
|
|
\s5
|
|
\v 6 ዲያብሎስ በትእቢት እንደወደቀ እንዳይወድቅ አዲስ አማኝ የቤተ ክርስቲያን መሪ አይሁን፤
|
|
\v 7 በውጭ ባሉት ዘንድ መልካም ምስክርነት ያለው ሊሆን ይገባል፣ በመሆኑም በነቀፋ እና በዲያብሎስ ወጥመድ አይወድቅም፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 8 ዲያቆናትም እንዲሁ፣ የተከበሩ፣ ቃላቸው አንድ የሆነ፣ ብዙ የወይን ጠጅ የማይጠጡ፣ የማይስገበገቡ መሆን አለባቸው፡፡
|
|
\v 9 በንጹህ ኅሊና የተገለጠውን የእምነት እውነት ሊጠብቁ ይገባቸዋል፡፡
|
|
\v 10 አስቀድመው ይገምገሙ፣ ከዚያም ያለነቀፋ ሆነው ከተገኙ በዲቁና አገልግሎት ይሾሙ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 11 እንዲሁም ሴቶች የተከበሩ፣ የማያሙ፣ ልከኞችና በሁሉ ነገር የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡
|
|
\v 12 ዲያቆናት እያንዳንዳቸው የአንዲት ሚስት ባል መሆን አለባቸው፤ ቤታቸውንና ልጆቻቸውንም በመልካም የሚያስተዳሩ ሊሆኑ ይገባል፡፡
|
|
\v 13 መልካም አገልግሎት የሚያበረክቱ እነርሱ በክርስቶስ ኢየሱስ ባላቸው እምነት ለራሳቸውእውነተኛ መሠረትና ድፍረትን ያገኛሉ፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 14 እነዚህን ነገሮች ስጽፍልህ ወደ አንተ በቅርቡ እንደምመጣ ተስፋ በማድረግ ነው፡፡
|
|
\v 15 ነገር ግን ብዘገይ፣ በእግዚአብሔር ቤት፣ ማለትም የእውነት ዓምድና መሠረት በሆነው፣ በሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንዴት መኖር እንደሚገባህ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 16 እኛ ሁላችን በዚህ እንስማማለን፡- ‹‹የተገለጠው እግዚአብሔርን የመምሰል ምስጢር ታላቅ ነው፣›› ይህም በሥጋ የተገለጠው፣ በመንፈስ የጸደቀው፣ በመላእክት የታየው፣ በሕዝቦች መካከል የታወጀው፣ በዓለም የታመነው፣ በክብር ወደ ሰማይ ያረገ ነው፡፡
|
|
\s5
|
|
\c 4
|
|
\cl ምዕራፍ 4
|
|
\p
|
|
\v 1 አሁን ግን መንፈስ በመጨረሻ ዘመን አንዳንድ ሰዎች የራሳቸውን ኅሊና በውሸት በተሞላ ግብዝነት በማደንዘዝ፤
|
|
\v 2 ለሚያስቱ መናፍስትና ለአጋንንት ትምህርት ትኩረት በመስጠት እምነትን ይክዳሉ በማለት በግልፅ ይናገራል፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 3 እውነትን ለማወቅ የመጡትን አማኞች ከምሥጋና ጋር ከሚቀበሉትና እርስበርሳቸው ከሚካፈሉት እግዚአብሔር ከፈጠረው ምግብ እንዲርቁ፣ ጋብቻንም እንዳያደርጉ ይከለክላሉ፡፡
|
|
\v 4 በእግዚአብሔር የተፈጠረው ሁሉ መልካም ነውና፤ በምሥጋና የሚቀበሉት እንጂ የሚጣል የለውም፡፡
|
|
\v 5 በእግዚአብሔር ቃልና በጸሎት የተቀደሰ ነው።
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 6 እነዚህን ነገሮች ለወንድሞች ብታስረዳ፣ በእምነት ቃሎች እና በተከተልከውም መልካም ትምህርት የምትመገብ የኢየሱስ ክርስቶስ መልካም አገልጋይ ትሆናለህ፡፡
|
|
\v 7 ራስህን እግዚአብሔርን ለመምሰል አሰልጥን እንጂ፣ አሮጊቶች የሚወዱአቸውን አለማዊ ተረቶችን አትቀበል፡፡
|
|
\v 8 የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጥቂት ነገር ይጠቅማል፣ ነገር ግን እግዚአብሔርን መምሰል ለአሁኑና ለሚመጣውም ሕይወት ተስፋ ስላለው ለሁሉ ነገር ይጠቅማል፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 9 ይህ መልእክት የታመነና ሁሉም ሊቀበሉት የተገባው ነው፡፡
|
|
\v 10 ለዚህም እንታገላለን ጠንክረንም እንሠራለን፣ ይህም የሚሆነው ሰዎችን ሁሉ በተለይም የሚያምኑትን በሚያድን በሕያው እግዚአብሔር ስለምንታመን ነው፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 11 እነዚህን ነገሮች አውጅ አስተምርም፡፡
|
|
\v 12 ማንም ወጣትነትህን አይናቀው፣ ነገር ግን በዚህ ፈንታ፣ በቃልና በሥራ፣ በፍቅር፣ በእምነትና በንጽሕና የእምነት ምሳሌ ሁን፡፡
|
|
\v 13 እስክመጣ ድረስ፣ ማንበብህን፣ መምከርህን እና ማስተማርህን ቀጥል፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 14 በትንቢት ከሽማግሌዎች የእጅ መጫን ጋር ለአንተ የተሰጠህን የጸጋ ስጦታ ቸል አትበል፡፡
|
|
\v 15 ለእነዚሀ ነገሮች ተጠንቀቅ፣ በእነርሱም ጽና፣ ይህን በማድረግህ ማደግህ በሁሉም ዘንድ ይገለጻል፡፡
|
|
\v 16 ለራስህ እና ለትምህርቱ ተጠንቀቅ፣ በእነዚህም ጽና ይህን ብታደርግ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህ፡፡
|
|
\s5
|
|
\c 5
|
|
\cl ምዕራፍ 5
|
|
\p
|
|
\v 1 ሽማግሌ የሆነውን አትገስጸው፣ ነገር ግን እንደ አባት ለምነው፣ ወጣቶችን እንደ ወንድሞች፣
|
|
\v 2 አሮጊቶችን እንደ እናቶች፣ ቆነጃጅቶችን እንደ እኅቶች በሙሉ ንጽሕና ለምናቸው፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 3 በትክክል መበለት የሆኑትን አክብር፤
|
|
\v 4 ነገር ግን ባሏ የሞተባት ልጆችና የልጅ ልጆች ከሏት፣ እነርሱ ራሳቸው በቤታቸው አክብሮትን፣ ለወላጆቻቸው ብድራት መክፈልን ይማሩ፣ ይህ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 5 ነገር ግን እውነተኛ መበለት ሁሉን ነገር ትታ በእግዚአብሔር ታምና ትኖራለች፣ ልመናዋን ሁል ጊዜ በእርሱ ፊት በማቅረብ ሌትና ቀን ትጠባበቃለች፡፡
|
|
\v 6 የሆነ ሆኖ፣ መቀማጠልን የምትወድ ሴት በሕይወትም ብትኖር የሞተች ነች፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 7 ከወቀሳ የራቁ እንዲሆኑ እነዚህን ነገሮች ስበክ፡፡
|
|
\v 8 ነገር ግን ማንም ለዘመዶቹ የሚያስፈልጋቸውን የማይሰጥ፣ ይልቁንም ለገዛ ቤተሰቡ የማያስብ እምነትን የካደ ከማያምን ሰው ይልቅ የከፋ ነው፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 9 ባሏ የሞተባት ሴት በመዝገብ ለመጻፍ እድሜዋ ከስድሳ ማነስ የለበትም፣ የአንድ ባል ሚስትም መሆን አለባት፡፡
|
|
\v 10 ልጆቿን በሥርዓት የምታሳድግ፣ እንግዶችን የምትቀበል፣ ወይም የቅዱሳንን እግር በማጠብ፣ የተጨነቁትንም በማጽናናት፣ በመልካም ሥራ ሁሉ የተመሰከረላት መሆን አለባት፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 11 ወጣት መበለቶችን ግን እንደ መበለት አትመዝግባቸው፣ ምክንያቱም የክርስቶስ ተቃራኒ የሆነው ሥጋዊ ፍላጎታቸው ሲያይልባቸው ለማግባት ይፈልጋሉና፡፡
|
|
\v 12 በዚህ ሁኔታ የቀድሞ እምነታቸውን ስለተዉ በደለኞች ናቸው፡፡
|
|
\v 13 ለሥራ ፈትነትም ስለሚጋለጡ ከቤት ወደ በት የሚዞሩ ይሆናሉ፡፡ ሥራ ፈቶች መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ሐሜተኞችና በሰው ጉዳይ ጣልቃ እየገቡ የማይገባውን የሚናገሩ ይሆናሉ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 14 ስለዚህ ወጣት ሴቶች እንዲያገቡ እና ልጆችን እንዲወልዱ ቤታቸውንም በመልካም እንዲያስተዳድሩ፣ ተቃዋሚውም ክፉ እንደምናደርግ የሚከስበትን ምክንያት እንዲያሳጡት እመክራለሁ፡፡
|
|
\v 15 አንዳንዶች ሰይጣንን ለመከተል ዞር ብለዋል፡፡
|
|
\v 16 መበለቶች ያሏት አንዲት የምታምን ሴት ብትኖር፣ ትርዳቸው፣ ስለሆነም የቤተ ክርስቲያን ሸክም ይቀልላታል እውነተኞቹን መበለቶች ለመርዳት ትችላለች፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 17 በመልካም የሚያስተዳድሩ መሪዎች በተለይም በቃሉ ስብከትና በማስተማር የሚተጉ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል፡፡
|
|
\v 18 የእግዚአብሔር ቃል ‹‹የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር›› እንዲሁም ‹‹ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋል›› ይላል፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 19 ሁለት ወይም ሦስት ምስክሮች ሳታገኝ በሽማግሌ ላይ ክስ አትቀበል፡፡
|
|
\v 20 ሁሉም ይማሩ ዘንድ አጥፊዎችን በሁሉ ፊት ገስጻሳቸው፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 21 በእግዚአብሔር ፊት፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት፣ በተመረጡትም መላእክት ፊት አዝዝሃለሁ፣ አንዳች አድልኦ ሳታደርግ እነዚህን ደንቦች ጠብቅ፡፡
|
|
\v 22 በማንም ላይ ቸኩለህ እጅህን አትጫን፣ ከማንም ኃጢአት ጋር አትተባበር፣ ርስህን በንጽሕና መጠበቅ አለብህ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 23 በተደጋጋሚ ሆድህን ስለሚያምህ ጥቂት የወይን ጠጅ ጠጣ እንጂ ለወደፊቱ ውኃ ብቻ አትጠጣ፡፡
|
|
\v 24 የአንዳንድ ሰዎች ኃጢአት በግልጽ የታወቀ ነው፣ ፍርድን ያስከትልባቸዋል፣ አንዳንዶች ግን ኋላ ይከተሉታል፡፡
|
|
\v 25 ልክ እንደዚሁ አንዳንድ መልካም ሥራዎች የተገለጡ ናቸው፣ ነገር ግን ሌሎቹ በጊዜው የተገለጡ ባይሆንም እንኳ የተሰወሩ አይደሉም፡፡
|
|
\s5
|
|
\c 6
|
|
\cl ምዕራፍ 6
|
|
\p
|
|
\v 1 የእግዚአብሔር ስምና ትምህርቱ እንዳይሰደብ ከቀንበር በታች ያሉ ባሪያዎች ለገዢዎቻቸው የሚገባቸውን ክብር ይስጡ፡፡
|
|
\v 2 አማኞች የሆኑ ገዢዎች ያሉአቸው ባሪያዎች፣ በእምነት ወንድሞቻቸው ስለሆኑ ገዢዎቻቸውን መናቅ የለባቸውም፡፡ ይልቁንም በመልካም ሥራቸው የሚጠቅሙ የተወደዱ ወንድሞች በመሆናቸው አብልጠው ያገልግሉአቸው፡፡ እነዚህን ነገሮች አስተምር ግለጽም፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 3 ማንም ልዩ ትምህርትን ቢያስተምር፣ እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚረዳውን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶሰን ቃል እና የእኛንም ጤናማ ቃል ባይቀበል፣
|
|
\v 4 በትእቢት ተነፍቶአል አንዳችም አያውቅም፡፡ ነገር ግን በክርክርና በቃል በመዋጋት የተለከፈ ነው፣ ከዚህም ምቀኝነት፣ ክርክር፣ መሳደብ፣ ክፉ አሳብና፣ እርስ በርስ መናደድም ይወጣሉ፡፡
|
|
\v 5 እነርሱም አእምሮአቸው የተበላሸባቸው ከእውነትም የራቁ እግዚአብሔርን መምሰል ጥቅም ማግኛ የሚመስላቸው ናቸው፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 6 ባለው ለሚረካ ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፡፡
|
|
\v 7 ወደ ዓለም ምንም አላመጣንምና፣ አንዳችም ይዘን መሄድ አይቻለንም፡፡
|
|
\v 8 ምግብ እና ልብስ ካለን ያ ይበቃናል፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 9 ባለጠጋ ለመሆን የሚመኙ በፈተና ውስጥ ይወድቃሉ፣ በወጥመድ፣ ሞኝነት በመሰሉ አያሌ ጎጂ ምኞቶች፣ እንዲሁም ሰዎችን በሚያሰጥሙና በሚያጠፉ በሌሎች ነገሮች ላይ ይወድቃሉ፡፡
|
|
\v 10 የገንዘብ ፍቅር የክፋት ሁሉ ሥር ነውና፡፡ አንዳንድ ሰዎች ይህን ሲመኙ ከእምነት ስተው ራሳቸውን በብዙ ሐዘን ጎዱ፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 11 አንተ ግን፣ የእግዚአብሔር ሰው፣ ከእነዚሀ ነገሮች ሽሽ፡፡ ጽድቅን፣ እግዚአብሔርን መምሰል፣ ታማኝነትን፣ ፍቅርን፣ ጽናትን እና ለሰዎች መጠንቀቅን ተከታተል፡፡
|
|
\v 12 መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፡፡ የተጠራህለትን በብዙ ምሥክሮች ፊት ስለመልካምነቱ የመሰከርክለትን የዘላለምን ሕይወት ያዝ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 13 ሁሉን ነገር በፈጠረ፣ በእግዚአብሔር ፊት፣ በጴንጤናዊው በጲላጦስ ፊት እውነትን በመሰከረው፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት አዝዝሃለሁ፣
|
|
\v 14 ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪገለጥ ድረስ ያለነቀፋ ሆነህ ትእዛዛቱን በፍጹምነት ጠብቅ፡፡
|
|
\s5
|
|
\v 15 እርሱም መገለጡን የተባረከውና፣ ብቻውን ኃያል የሆነው፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶችም ጌታ በወሰነው በትክክለኛው ጊዜ ያሳያል፡፡
|
|
\v 16 እርሱ ብቻ የማይሞት ነው፤ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ውስጥ ይኖራል፡፡ ማንም ሰው አላየውም ሊያየውም አይችልም፡፡ ለእርሱ ክብር የዘላለምም ኃይል ይሁን፡፡ አሜን፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 17 በአሁኑ ዘመን ሀብታሞች ለሆኑት እንዳይታበዩ ንገራቸው፡፡ ደስ እንዲለን እግዚአብሔር በሚሰጠን እውነተኛ ብልጥግና እንጂ እርግጠኛ ባልሆነው በዚህ ምድራዊ ባለጠግነት ተስፋ እንዳያደርጉ እዘዛቸው፡፡
|
|
\v 18 በመልካም ሥራ ባለጠጎች እንዲሆኑ፣ መልካም የሆነውን እንዲያደርጉ ለማካፈልም ፈቃደኞች እንዲሆኑ ንገራቸው፡፡
|
|
\v 19 በዚህ ሁኔታ በሚመጣው ዓለም ለራሳቸው መልካም መሠረትን ይጥላሉ፣ እውነተኛውንም ሕይወት ይይዛሉ፡፡
|
|
\s5
|
|
\p
|
|
\v 20 ጢሞቴዎስ ሆይ፣ ለአንተ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ፡፡ የማይረባውን ወሬ አስወግድ፣ በሐሰት እውቀት ከተባለ እርስ በርሱ ከሚጋጭ ነገር ጋር ከመከራከር ራቅ፡፡
|
|
\v 21 አንዳንድ ሰዎች ይህ እውቀት አለን በማለት ከእምነት ርቀዋል፡፡ ጸጋ ከአንተ ጋር ይሁን፡፡
|