am_ulb/34-NAM.usfm

130 lines
10 KiB
Plaintext
Raw Permalink Normal View History

2018-09-24 19:54:20 +00:00
\id NAM
\ide UTF-8
\h ትንቢተ ናሆም
\toc1 ትንቢተ ናሆም
\toc2 ትንቢተ ናሆም
\toc3 nam
\mt ትንቢተ ናሆም
\s5
\c 1
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\p
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 1 ስለ ነነዌ የተነገረ ቃል፤ የአልቆሻዊው የናሆም ራእይ መጽሐፍ ይህ ነው፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 2 ያህዌ ቀናተኛና ተበቃይ ነው፤ ያህዌ የሚበቀል በመዓትም የተሞላ አምላክ ነው፡፡ ያህዌ ባላጋራዎቹን ይበቀላል፤ በጠላቶቹም ላይ ቁጣውን ይወርዳል፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 3 ያህዌ ለቁጣ የዘገየ፣ በኃይሉም ታላቅ ነው፤ በምንም ዐይነት ጠላቶቹን ንጹሕ ናችሁ አይልም፡፡ ያህዌ በወጀብና በዐውሎ ነፋስ ውስጥ መንገድ አለው፤ ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 4 ባሕርን ይገሥጻል፤ ያደርቀዋልም፤ እርሱ ወንዞችን ሁሉ ያደርቃል፡፡ ባሳንና ቀርሜሎስ ጠውልገዋል፤ የሊባኖስ አበቦችም ረግፈዋል፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 5 ተራሮች በእርሱ ፊት ተናወጡ፤ ኮረብቶችም ቀለጡ፤ ምድር በፊቱ፣ ዓለምና በውስጧ የሚኖሩ ሰዎችም ሁሉ ተናወጡ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 6 በቁጣው ፊት ማን መቆም ይችላል? ጽኑ ቁጣውንስ ማን መቋቋም ይችላል? መዓቱ እንደ እሳት ፈስሶአል፤ ዐለቶችም በፊቱ ተሰነጣጠቁ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 7 ያህዌ መልካም ነው፤ በመከራ ጊዜም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ ለሚታመኑበት ታማኝ ነው፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 8 ጠላቶቹን ግን በኃይለኛ ጐርፍ ያጥለቀልቃቸዋል፤ ወደ ጨለማም ያሳድዳቸዋል፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 9 እናንተ ሰዎች ያህዌ ላይ የምታሤሩት ምንድነው? እርሱ ፈጽሞ ያጠፋዋል፤ መከራም ዳግመኛ አይነሣም፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 10 እንደ እሾኽ ይጠላለፋሉ፤ በወይን ጠጃቸውም ይሰክራሉ፤ እሳት እንደ ገለባ ይበላቸዋል፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 11 ነነዌ ሆይ፣ ያህዌ ላይ የሚያሤር፣ ክፉ ምክር የሚመክር ከመካከላችሁ ወጥቷል፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\p
2020-12-18 23:07:48 +00:00
\v 12 ያህዌ እንዲህ ይላል፤ «ኅይለኞችና ቁጥራቸውም እጅግ የበዛ ቢሆን እንኳ ተቆርጠው ይጠፋሉ፤ ከእንግዲህም ሕዝባቸው አይኖም፡፡ ይሁዳ ሆይ፣ ከዚህ በፊት ባስጨንቅህም፣ ከእንግዲህ አላስጨንቅህም፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 13 አሁንም ቀንበራቸውን ከአንተ ላይ እሰብራለሁ፤ ስንሰለትህንም በጥሼ እጥላለሁ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2020-12-18 23:07:48 +00:00
\v 14 ነነዌ ሆይ፣ ስለ አንቺ ያህዌ እንዲህ ብሎ አዝዞአል፤ «ስም የሚያስጠራ ትውልድ አይኖራችሁም፡፡ የተቀረጹ ምስሎችና ቀልጠው የተሠሩ ጣዖቶችን ከአማልክቶቻችሁ ቤት አጠፋለሁ፡፡ እጅግ ክፉ ነህና መቀበሪያህን እምስልሃለሁ፡፡
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 15 የምሥራችን የሚያመጣና ሰላምን የሚያውጅ ሰው እግር በተራራው ላይ ናቸው! ይሁዳ ሆይ፣ በዓላትህን አክብር፤ ስእለትህንም ፈጽም፤ ከእንግዲህ ክፉዎች አይወርሩህም፤ እነርሱ ፈጽሞ ይጠፋሉ፡፡
\s5
\c 2
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\p
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 1 እስክትደቅቂ ድረስ የሚረግጥሽ እርሱ እየመጣ ነው፡፡ ስለዚህ ምሽጐችሽን አጠናክሪ መንገድሽን ጠብቂ፤ ወገብሽን ታጠቂ፤ ኃይልሽን ሁሉ አሰባስቢ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 2 አጥፊዎች ባድማ ቢያደርጓቸውም፣ የወይን ተክል ቦታቸውን ቢያጠፉባቸውም እንደ እስራኤል ክብር ሁሉ ያህዌ የያዕቆብንም ክብር ይመልሳል፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 3 የወታደሮቹ ጋሻ ቀይ ነው፣ ተዋጊዎቹም ሐምራዊ ልብስ ለብሰዋል ዝግጁ በሆኑበት ቀን የሰረገሎቹ ብረት ያብረቀርቃል የጦሩ ዘንግ ይወዛወዛል፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 4 ሰረገሎቹ በየመንገዱ ይከንፋሉ፤ ሰፋፊ በሆኑት መንገዶች በፍጥነት ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡ የሚንቦገቦግ ችቦ ይመስላሉ፤ እንደ መብረቅም ይወረወራሉ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 5 እስክትደቂ ድረስ የሚረግጥሽ እርሱ የጦር ሹማምንቱን ይጠራል እነርሱም እየተደነቃቀፉ ወደ ፊት ይመጣሉ፣ ለማጥቃት ወደ ከተማ ቅጥር ይወጣሉ፤ የሚወረወርባቸውን ፍላጻ በትልቁ ጋሻቸው ይከላከላሉ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 6 በወንዙ በኩል ያሉ በሮች ወለል ብለው ይከፈታሉ ቤተ መንግሥቱም ተደመሰሰ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 7 ንግሥቲቱ ተማርካ ዕርቃኗን ተወሰደች ሴት አገልጋዮቿ ደረታቸውን እየደቁ እንደ ርግብ ያላዝናሉ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2020-12-18 23:07:48 +00:00
\v 8 ነነዌ ውሃ መያዝ እንደማይችል ኩሬ ናት፤ ሕዝቧም እንደ ፈጣን ወራጅ ውሃ ፈጥኖ ይሸሻል፡፡ ሌሎች «ቁሙ ቁሙ» ብለው ይጮኻሉ ዞር ብሎ የሚያይ ግን የለም፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 9 የነነዌ ሀብት ስፍር ቁጥር የለውም የከበሩ ድንጋዮቿ የተትረፈረፉ ናቸው ስለዚህ ብሩን ዝረፉ፣ ወርቁንም ንጠቁ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 10 ነነዌ ባዶ ሆነች፣ ተራቆተች፡፡ የሰዎች ልብ ቀለጠ፤ የሰው ሁሉ ጉልበት ተብረከረከ ሁሉም ተጨንቀዋል፤ ፊታቸው ገርጥቷል፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 11 የአንበሶች ዋሻ፣ የአንበሳ ደቦሎች የሚመገቡበት፣ ወንድ አንበሳና እንስት አንበሳ ምንም ሳይፈሩ ወዲያ ወዲህ ይሉበት የነበረ ቦታ የታል?
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 12 አንበሳ ለግልገሎቹ የሚበቃውን ያህል ገደለ፤ ለእንስቶቹ የሚበቃውንም ያህል አድኖ ያዘ የገደለውን በዋሻው፣ የነጠቀውንም በመኖሪያ ቦታው ሞልቶአል፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2020-12-18 23:07:48 +00:00
\v 13 የሰራዊት ጌታ ያህዌ እንዲህ ይላል፤ ሰረገሎችን አቃጥላለሁ፤ ደቦል አንበሶችህን ሰይፍ ይበላቸዋል፡፡ የዘረፍኸውን ከምድርህ አጠፋለሁ፤ ከእንግዲህ የመልእክተኞችህ ድምፅ አይሰማም፡፡»
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\s5
\c 3
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\p
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 1 ደም ለሞላባት ከተማ ወዮላት! ሐሰትና የተዘረፈ ንብረት ሞልቶበታል፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 2 አሁን ግን የአላንጋ ድምፅና የመንኰራኩር ኳኳታ ድምፅ፣ የፈጣን ፈረስ ኮቴ፣ የሰረገሎች መንጓጓት ይሰማል፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 3 የሚያብረቀርቅ ሰይፍና የሚያንጸባርቅ ጦር የያዙ ፈረሰኞች ጥቃት ያደርሳሉ፤ የሞተው ብዙ ነው፤ ሬሳ በሬሳ ተከምሮአል እጅግ ከመብዛቱ የተነሣ አጥቂዎቹ በሞቱት ሰዎች ሬሳ ይሰናከላሉ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 4 ይህ ሁሉ የሆነው ገደብ በሌለው የአመንዝራዋ ፍትወት ምክንያት ነው፤ እርሷ በዝሙቷ መንግሥታን፣ በጥንቆላዋም ሕዝቦችን ባሪያ አድርጋለች፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2020-12-18 23:07:48 +00:00
\v 5 የሰራዊት ጌታ ያህዌ እንዲህ ይላል፣ «እኔ በጠላትነት ተነሥቼብሻለሁ ዕርቃንሽን ለሕዝቦች፣ ኅፍረተ ሥጋሽን ለመንግሥታት አሳያለሁ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 6 በጣም የሚያስጸይፍ ቆሻሻ እደፋብሻለሁ፤ እንቅሻለሁ፤ ሰው ሁሉ እንዲሳለቅብሽ አደርጋለሁ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2020-12-18 23:07:48 +00:00
\v 7 የሚያይሽ ሁሉ ከአንቺ እየሸሸ፣ «ነነዌ ፈራርሳለች፤ ማን ያለቅስላታል? የሚያጽናናትንስ ከወዴት አገኛለሁ?» ይላል፡፡
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 8 ነነዌ ሆይ፣ ለመሆኑ አንቺ ዐባይ ወንዝ አጠገብ ከተሠራችውና በውሃ ከተከበበችው፣ ወንዙ መከላከያ፣ ባሕሩ ራሱ ቅጥራ ከሆነለት ከቴብስ ትበልጫለሽን?
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 9 ኢትዮጵያና ግብፅ ወሰን የለሽ ኃይሏ ነበሩ ፉጥና ሊቢያም ረዳቶቿ ነበሩ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 10 ያም ሆኖ፣ ቴብስ ተጋዘች፤ በምርኮም ተወሰደች ሕፃናቷ በየመንገዱ ማእዘን ላይ ተፈጠፈጡ፤ በመኳንንቷ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ፤ ታላላቅ ሰዎቿ ሁሉ በሰንሰለት ታሰሩ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 11 አንቺ ደግሞ ትሰክሪያለሽ መደበቅ ትሞክሪያለሽ ከጠላቶችሽ መሸሸጊያም ትፈልጊያለሽ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 12 ምሽጐችሽ ሁሉ ቀድሞ እንደ ደረሰ፣ ሲነቀነቅ በላተኛው አፍ ውስጥ እንደሚወድቅ የበለስ ፍሬ ሆነዋል፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 13 ወታደሮችሽ እንደ ሴት ፈሪዎች ሆነዋል የምድርሽ በሮች ወለል ብለው ለጠላቶችሽ ተከፍተዋል፡፡ መዝጊያዎቻቸውን እሳት በልቷቸዋል፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 14 ለከበባው ውሃ ቅጂ፣ ምሽጐችሽን አጠናክሪ፤ ጭቃ ረግጠሸ የሸክላ መሥሪያ አዘጋጂ፤ ጡብም ሥሪ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 15 በዚያ እሳት ይበላሻል፤ ሰይፍ ያጠፋሻል፤ አንበጣ ማንኛውንም ነገር እንደሚጠፉ ያጠፋሻል፡፡ ስለዚህ እንደ አንበጣ እርቢ እንደ ኩብኩባም ተባዢ፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 16 ነጋዴዎችሽን ከሰማይ ከዋክብት ይበልጥ አብዝተሻል፤ ይሁን እንጂ፣ ምድሪቱን እንደ አንበጣ ጋጡ፤ ከዚያም በርረው ሄዱ፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 17 መኳንንቶችሽ የአንበጦችን ያህል ብዙ ናቸው፣ የጦር መሪዎችሽ በብርድ ቀን ቅጥር ሥር እንደሚቀመጥ የኩብኩባ መንጋ ናቸው፡፡ ፀሐይ ሲወጣ ግን በርረው ይሄዳሉ፤ የት እንደሚሄዱም አይታወቅም፡፡
\s5
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 18 የአሦር ንጉሥ ሆይ፣ እረኞችህ አንቀላፉ መኳንንትህ ዐርፈው ተኙ፡፡ ሕዝብህ ሰብሳቢ አጥተው በየተራሮች ተበትነዋል፡፡
2023-01-02 15:08:57 +00:00
\q
2018-09-24 19:54:20 +00:00
\v 19 ቁስልህን መፈወስ የሚችል የለም፤ ቁስልህ እጅግ ጽኑ ነው፡፡ ስለ አንተ የሚሰማ ሁሉ በውድቀትህ ደስ ብሎት ያጨበጭባል፡፡ ወሰን ከሌለው ጭካኔህ ማን ያመለጠ አለ?