\v 10 በዚያን ቀን ይላል ያህዌ፣ ከዓሣው በር ጩኸት፣ ከሁለተኛው አደባባይ ዋይታ፣ ከኮረብቶችም ታላቅ የጥፋት ድምፅ ይሰማል፡፡
\v 11 እናንት በገበያው ቦታ የምትኖሩ ዋይ በሉ፤ ነጋዴዎች ሁሉ ይደመሰሳሉ፤ በብር የሚነግዱትም ሁሉ ይጠፋሉ፡፡›