am_zep_text_ulb/01/07.txt

3 lines
572 B
Plaintext

\v 7 የያህዌ ቀን እየቀረበ ነውና በጌታ ያህዌ ፊት ጸጥ በሉ፤ ያህዌ መሥዋዕት አዘጋጅቷል፤ የጠራቸውንም እንግዶች ቀድሷል፡፡
\v 8 በያህዌ የመሥዋዕት ቀን መኳንንቱንና የንጉሡን ልጆች፣ እንግዳ ልብስ የሚለብሱትንም ሁሉ እቀጣለሁ፡፡
\v 9 በዚያን ቀን፣ በመድረኩ ላይ የሚዘልሉትን ሁሉ፣ የጌቶቻቸውን ቤት በዐመፅና በማጭበርበር የሚሞሉትንም ሁሉ እቀጣለሁ፡፡