\c 2 \v 1 እስክትደቅቂ ድረስ የሚረግጥሽ እርሱ እየመጣ ነው፡፡ ስለዚህ ምሽጐችሽን አጠናክሪ መንገድሽን ጠብቂ፤ ወገብሽን ታጠቂ፤ ኃይልሽን ሁሉ አሰባስቢ፡፡
\v 2 አጥፊዎች ባድማ ቢያደርጓቸውም፣
የወይን ተክል ቦታቸውን ቢያጠፉባቸውም
እንደ እስራኤል ክብር ሁሉ ያህዌ
የያዕቆብንም ክብር ይመልሳል፡፡