\v 6 እነዚህ ሰዎች የአሦርን ምድር በሰይፍ፣
የናምሩዱንም ምድር እጃቸው ላይ ባለው ሰይፍ ይገዛሉ፡፡
ወደ ምድራችን ሲመጡ
ወደ ድንበራችንም ሲገሠግሡ
እርሱ ከአሦራውያን ይድነናል፡፡
\v 7 የያዕቆብ ትሩፍ በብዙ ሕዝብ መካከል
ከያህዌ ዘንድ እንደሚወርድ ጠል፣
ሣር ላይ እንደሚጥል ካፊያ
ሰውን እንደማይጠብቅ፣
በሰው ልጆችም እንደማይተማመን ሰው ይሆናል፡፡