\c 1 \v 1 በሚልክያስ በኩል ወደ እስራኤል የመጣው የያህዌ ቃል ዐዋጅ ይህ ነው።
\v 2 “እኔ ወድጃችኋለሁ” ይላል ያህዌ። እናንተ ግን፣ “እንዴት ወደድኸን?” ብላችኋል? “ዔሳው የያዕቆብ ወንድም አልነበረምን? ያዕቆብን ወደድሁ
\v 3 ዔሳውን ግን ጠላሁ። ተራራውን ባድማ አደረግሁ፤ ርስቱንም የምድረ በዳ ቀበሮዎች መኖሪያ አደረግሁ።”