am_jon_text_ulb/01/04.txt

2 lines
550 B
Plaintext

\v 4 ያህዌ ግን በባሕሩ ላይ ታላቅ ነፋስ ላከ፤ ከባድ ማዕበልም ተነሥቶ መርከቧን አናወጠ፤ ወዲያውኑ የምትሰበር መስሎ ታየ፡፡
\v 5 መርከበኞቹ በጣም ፈሩ፤ እያንዳንዱ ሰው ወደ አምላኩ ጮኸ ፡፡ የመርከቧ ክብደት እንዲቀልል በውስጧ የነበረው ሸክም ወደ ባሕሩ ተጣለ፡፡ ዮናስ ግን ወደ መርከቧ ታችኛ ክፍል ሄዶ ተኛ፤ ከባድ እንቅልፍ ላይም ነበር፡፡