\v 17 የእግዚአብሔር አገልጋዮች፥ ካህናቱ፥ በቤት መቅደሱ መግቢያ ደጅና በመሠዊያው መካከል ያልቅሱ። እንዲህም ይበሉ፦«እግዚአብሔር ሆይ ለሕዝብህ ራራ፥አሕዛብ ይገዙአቸው ዘንድ ርስትህን ለእፍረት አሳልፈህ አትስጥ።በአሕዛብ መካከል አምላካቸው ወዴት ነው? ስለ ምን ይበሉ።»