am_jer_tn/19/06.txt

46 lines
3.9 KiB
Plaintext

[
{
"title": "እዩ",
"body": "\"ተመልከቱ\" ወይም \"አድምጡ\" ወይም \"ለምነግራችሁ ነገር ትኩረት ስጡ\""
},
{
"title": "ይህ የያህዌ አዋጅ/ትዕዛዝ ነው",
"body": "ያህዌ ስለ ራሱ በስሙ የሚናገረው/የሚምለው የተናገረው ነገር እርግጠኛ መሆኑን ለመግለጽ ነው፡፡ ይህ በኤርምያስ 1፡8 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ \"ያህዌ ያዘዘው ይህንን ነው\" ወይም \"እኔ ያህዌ ያዘዝኩት ይህንን ነው\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ይህ ስፍራ ከእንግዲህ አይጠራም",
"body": "ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ \"ሰዎች ከእንግዲህ ይህን ስፍራ አይጠሩትም\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ቶፌት… የቤን ሄኖም ሸለቆ…የእርድ ሸለቆ ",
"body": "ይህ በኤርምያስ 7፡31 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡"
},
{
"title": "እኔ በጠላቶቻቸው ፊት በሰይፍ እንዲወድቁ አደርጋለሁ",
"body": "\"በሰይፍ እንዲወድቁ\" የሚለው ፈሊጥ በጦርነት ውስጥ እንዲሞቱ ማለት ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ \"ጠላቶቻቸው በሰይፍ እንዲገድሏቸው አደርጋለሁ\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ) "
},
{
"title": "እኔ እነርሱን…አደርጋለሁ ",
"body": "\"እነርሱ\" የሚለው ቃል የሚያመለክተው የይሁዳን እና እየሩሳሌምን ህዝቦች ነው፡፡"
},
{
"title": "ህይወታቸውን በሚፈልጉ ሰዎች እጅ",
"body": "ግሡ ከቀደመው ሀረግ ሊወሰድ ይችላል፡፡ \"በ…እጅ መውደቅ\" የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር በሰው መገደል የሚል ትርጉም ሲኖረው፣ \"እጅ\" ከሚለው ቃል ጋር የሚወክለው የሰውየውን ሁለንተና ነው፡፡ \"ሊገድሏችሁ የሚፈልጉ ሁሉ እንዲገድሏቸው አደርጋለሁ\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተዘለለ/የተተወ እና ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ እንደዚሁም ፈሊጣዊ አነጋገር የሚሉትን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "የጥላች ድምጽ አካል",
"body": "\"የጥላች ድምጽ\" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ጠንካራ የሆነ ያለ መቀበልን መግለጫ ድምጽ ሲሆን በግሳዊ ሀረግ ሊተረጎም ይችላል፡፡ \"ሰዎች ሁሌም የጥላቻ ድምጽ የሚያሰሙበት ነገር\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "እንዲበሏቸው አደርጋቸዋለሁ",
"body": "\"በእየሩሳሌም የሚኖሩ ሰዎችን እንዲበሉ አደርጋለሁ\""
},
{
"title": "በዚህ ከበባ ",
"body": "\"በከበባው ምክንያት\""
},
{
"title": "ከጠላቶቻቸው በደረሰባች ጭንቀት እና ህይወታቸውን በሚፈልጉ",
"body": "ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ \"ከጠላቶቻቸው እና ህይወታቸውን ከሚፈልጉ የተነሳ በላያቸው ጭንቀት ይመጣል\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)"
}
]