am_jer_tn/15/05.txt

38 lines
3.2 KiB
Plaintext

[
{
"title": "አጠቃላይ መረጃ፡",
"body": "ያህዌ የሚያጠፏቸው አራት ወገኖችን እንደሚሰድባቸው ነገራቸው- ሰይፍን፣ ውሾችን፣ ወፎችን እና አራዊቶችን፡፡"
},
{
"title": "ኢየሩሳሌም ሆይ፣ ለአንቺ ማን ይራራልሻል? ማንስ ለአንቺ ያለቅስልሻል?",
"body": "ያህዌ ይህንን ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የተጠቀመው ማንም ለኢየሩሳሌም እንደማያለቅስላት ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡ \"ኢየሩሳሌም ሆይ፣ ማንም ለአንቺ አይራራልሽም፡፡ በመጥፋትሽ ማንም አያዝንም፡፡\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ኢየሩሳሌም ሆይ፣ ለአንቺ",
"body": "እዚህ ስፍራ \"ኢየሩሳሌም\" የሚለው ቃል የሚያመለክተው በዚያ የሚኖሩ ሰዎችን ነው፡፡ \"በኢየሩሳሌም የምትኖሩ እናንተ ሰዎች\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ) "
},
{
"title": "አንቺ እኔን ትተሽኛል… ከእኔ ርቀሽ ሄደሻል",
"body": "እነዚህ ሁለት ሀረጎች በመሰረቱ ተመሳሳይ ትርጉም ሲኖራቸው፣ በእርግጥም ህዝቡ ያህዌን ቸል ማለቱን ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ይህ የያህዌ አዋጅ/ትዕዛዝ ነው",
"body": "ያህዌ ስለ ራሱ በስሙ የሚናገረው/የሚምለው የተናገረው ነገር እርግጠኛ መሆኑን ለመግለጽ ነው፡፡ ይህ በኤርምያስ 1፡8 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ \"ያህዌ ያዘዘው ይህንን ነው\" ወይም \"እኔ ያህዌ ያዘዝኩት ይህንን ነው\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አንደኛ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ከእኔ ርቀዋል",
"body": "\"እኔን ትተዋል\" ወይም \"ከእኔ ርቀው ሄደዋል\""
},
{
"title": "በእጄ እመታችኋለሁ",
"body": "እዚህ ስፍራ \"እጅ\" የሚወክለው ሀይልን ነው፡፡ \"እናንተን ለመምታት ሀይሌን እጠቀማለሁ\" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "መንሽ",
"body": "ረጅም እጀታ እና የብረት ጣቶች ያለው በአየር ላይ ወደ ላይ በማንሳት እና በመጣል ጥራጥሬን ለመለየት የሚያገለግል የገበሬ መሳሪያ"
},
{
"title": "ሀዘንተኛ አደርጋቸዋለሁ",
"body": "\"ልጆቻቸው እንዲሞቱ አደርጋለሁ\" ወይም \"ጠላቶቻቸው ልጆቻቸውን እንዲገድሉ አደርጋለሁ\" "
}
]