am_jer_tn/13/20.txt

30 lines
4.2 KiB
Plaintext

[
{
"title": "አጠቃላይ መረጃ፡- ",
"body": "እግዚአብሔር ለኢየሩሳሌም ሕዝብ እየተናገረ ነው፡፡"
},
{
"title": "ዓይናችሁን አንሥታችሁ እነዚህን ከሰሜን የሚመጡትን ተመልከቱ ",
"body": "እዚህ ላይ “ተመልከቱ” የሚለው ፈሊጥ ሲሆን ትኩረት ስጡና ምን እየሆነ እንዳለ አስተውሉ ማለት ነው፡፡ በተጨማሪ “ዓይናችሁን አንሥታችሁ” የሚለው ወደ አንድ ነገር መመከልት ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ትኩረት ስጡና እነዚህ ከሰሜን የሚመጡትን አስተውሉ” (ፈሊጥ እና ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "እነዚህን ከሰሜን የሚመጡትን ",
"body": "ይህ ከሰሜን የሚመጣውን የጠላት ጦር ሰራዊት ያመለክታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ከሰሜን የሚመጣውን የጠላት ጦር ሰራዊት” ወይም “ከሰሜን የሚዘምተውን የጠላት ጦር ሰራዊት” (ግምታዊ እውቀት እና ያልተገለጸ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "እርሱ ለአንቺ የሰጠሽ መንጋ፥ ለአንቺ የተዋበ መንጋ የነበረው ወዴት አለ?",
"body": "ይህ መልስ የማይሰጥበት ጥያቄ የተጠየቀው የይሁዳ ሕዝብ በጠላት ጦር ሰራዊት እንደሚማረክ አጽንዐት ለመስጠት ነው፡፡ ምንም እንኳ ይህ ክስተት ገና የተከናወነ ባይሆንም ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የይሁዳ ሕዝብ እንደተማረኩ ተደርጎ ነው፡፡ ይህ ጥያቄ እንደ ዓረፍተ ሃሳብና እንደ ወደፊት ጊዜ ተደርጎ ሊጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኔ የይሁዳን ሕዝብ እንደ ተወደዱ የበጎች መንጋ እንድትጠብቂያቸው ለአንቺ ሰጥቼሽ ነበር ነገር ግን የጠላት ጦር ሰራዊት ይማርካቸዋል፡፡” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች እና የተፈጸመ ትንቢታዊ ንግግር የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "መንጋ",
"body": "ይህ የይሁዳ መሪዎች እነርሱን ሊንከባከቧቸውና ሊጠብቋቸው እንደሚገባ አጽንዖት ለመስጠት የይሁዳን ሕዝብ እንደ በጎች “መንጋ” አድርጎ ይገልጻቸዋል፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ወዳጆችሽ እንዲሆኑ ያስተማርሻቸውን እግዚአብሔር በራስሽ ላይ አለቆች ባደረጋቸው ጊዜ ምን ትያለሽ?",
"body": "ይህ መልስ የማይሰጥበት ጥያቄ ጥቅም ላይ የዋለው የይሁዳ መሪዎች ይመሩት የነበረው ሕዝብ ከሚያሸንፏቸው መንግስታት ጋር ሰላም እንደሆኑ ያስቡ እንደነበር አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡ ይህ ጥያቄ እንደ ዓረፍተ ሃሳብ ሊጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የእናንተ ወዳጆች እንደሆኑ ያሰባችኋቸው ሕዝብ ያሸንፏችኋል ደግሞም በእናንተ ላይ ባለስልጣን ይሆናሉ፡፡” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "እነዚህ ነገሮች እንደምትወልድ ሴት አንቺን የሚይዙ የምጥ ጣር ጅማሬዎች አይደሉምን? ",
"body": "እግዚብሔር ይህን መልስ የማይሰጥበት ጥያቄ የተጠቀመው መማረካቸው የሚያልፉበት መከራ ጅማሬ እንደሆነ ለሕዝቡ ለመንገር ነው፡፡ ይህ ጥያቄ እንደ ዓረፍተ ሃሳብ ሊጻፍ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እነዚህ አንቺ የምትሰቃይባቸው ነገሮች ሴት ልጅ ስትወልድ የሚገጥማት የምጥ ሕመም ጅማሬ ዓይነት ነው፡፡” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ )"
}
]