58 lines
4.2 KiB
Plaintext
58 lines
4.2 KiB
Plaintext
[
|
|
{
|
|
"title": "አያያዥ ሀሳብ፡-",
|
|
"body": "እግዚአብሔር በይሁዳ ሕዝብ ላይ የሚያመጣውን ፍርድ መናገሩን ቀጥሏል፡፡"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "በዚያን ጊዜ",
|
|
"body": "በኤርምያስ 7:32 እስከ 34 ውሰጥ ያሉት ክስተቶች በሚፈጸሙበት ጊዜ፡፡"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "ይህ የእግዚአብሔር አዋጅ ነው",
|
|
"body": "እግዚአብሔር የሚናገረው ነገር እርግጠኛ እንደሆነ ለመግለጽ በስም ስለ ራሱ ይናገራል፡፡ ይህን በኤርምያስ 1፡8 ላይ እንዴት እንደተረጎምኸው ተመልከት፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር የተናገረው ይህ ነው” ወይም “እኔ እግዚአብሔር የተናገርሁት ይህ ነው” (አንደኛ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ) "
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "እነርሱ ያመጡአቸዋል",
|
|
"body": "እዚህ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል የይሁዳን ሕዝብ ጠላቶች ይወክላል፡፡"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "መኳንንቶቻቸው ",
|
|
"body": "“ነገስታቶቻቸው” ወይም “መሪዎቻቸው”"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "እነርሱን ይዘረጉአቸዋል",
|
|
"body": "“እነርሱን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በቀደመው ጥቅስ የተዘረዘሩትን ሰዎች አጥንቶች ነው፡፡"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "እነርሱ በተከተሏቸውና በአገለገሏቸው እንዲሁም አብረው በተጓዟቸውና በፈለጓቸው፣ ባመለኳቸው",
|
|
"body": "እዚህ ላይ “እነርሱ” የሚለው ቃል የይሁዳ ሕዝብን የሚያመለክት ነው፡፡ እነዚህ ሦስት ሀረጎች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፣ የተደጋገሙት አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "አብረው በተጓዟቸው",
|
|
"body": "ይህ ለማገልገልና ለማምለክ ተለዋጭ ዘይቤ ነው፡፡ ይህንን በኤርምያስ 2:23 ላይ እንዴት እንደተረጎምኸው ተመልከት፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "አጥንቶች አይሰበሰቡም ወይም እንደገና አይቀበሩም",
|
|
"body": "ይህ በገቢር ቅርጽ ሊተረጎም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አጥንቶቻቸውን ማንም ሰው አይሰበስበውም ወይም እንደገና አይቀብሯቸውም” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "እንደ ተጣለ ጉድፍ በምድር ገጽ ላይ ይበተናል",
|
|
"body": "አጥንቶች በምድር ላይ ካለ ጉድፍ ተነጻጽረዋል፣ ይህ ንጽጽር አጥንቶቹ አስጸያፊ እንደሚሆኑና እንደገና እንደማይቀበሩ አጽንዖት ለመስጠት ነው፡፡ (ተነፃፃሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "በምድረ ገጽ ላይ",
|
|
"body": "“በምድር ዙርያ ሁሉ”"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "እነርሱን ባሳደድኋቸው ስፍራ ሁሉ ",
|
|
"body": "“እነርሱን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የይሁዳ ሕዝብን ነው፡፡"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "ከዚህ ክፉ ሕዝብ አሁንም የቀሩት ሁሉ ከሕይወት ይልቅ ለራሳቸው ሞትን ይመርጣሉ",
|
|
"body": "“ከዚህ ክፉ ሕዝብ የቀሩት ሁሉ በሕይወት ከሚኖሩ መሞት ይፈልጋሉ”"
|
|
},
|
|
{
|
|
"title": "ይህ የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔር አዋጅ ነው ",
|
|
"body": "እግዚአብሔር የሚናገረው ነገር እርግጠኛ እንደሆነ ለመግለጽ በስም ስለ ራሱ ይናገራል፡፡ ተመሳሳይ ቃላትን በኤርምያስ 1፡8 ላይ እንዴት እንደተረጎምኸው ተመልከት፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የተናገረው ይህ ነው” ወይም “እኔ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የተናገርሁት ይህ ነው” (አንደኛ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ) "
|
|
}
|
|
] |