am_jer_tn/02/14.txt

58 lines
5.4 KiB
Plaintext

[
{
"title": "በውኑ እስራኤል ባሪያ ነውን? የተወለደው በጌታው ቤት ነውን? ታዲያ ስለምን ለብዝበዛ ተዳረገ?",
"body": "ምንም እንኳ እግዚአብሔር የሚናገረው ለሕዝቡ ቢሆንም ስለ እስራኤል ለሌላ ሰው እንደሚናገር አድርጎ ሶስተኛ ሰው ተጠቅሟል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እስራኤል፣ አንተ ባሪያ ነህ እንዴ? የተወለድከው በቤት ነው? ታዲያ ለምን ለብዝበዛ ተዳረግህ? (አንደኛ ሁለተኛና ሶስተኛ መደብ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "እስራኤል ባሪያ ነውን? የተወለደው በጌታው ቤት ነውን? ",
"body": "እግዚአብሔር ይህን ጥያቄ የተጠቀመው እስራኤል ለብዝበዛ መዳረግ እንዳልነበረባት ምክንያቱን ለመናገር ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እስራኤል ባርያ አይደለም፡፡ እስራኤል በቤት አልተወለደም ነበር፡፡” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "የተወለደው በጌታው ቤት ነውን? ",
"body": "እዚህ ላይ “በጌታው ቤት ተወለደ” የሚለው ሀረግ ለባርነት መወለድን የሚያሳይ ምትክ ስም ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የተወለደው ባርያ ሆኖ ነው” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ታዲያ ስለምን ለብዝበዛ ተዳረገ?",
"body": "እግዚአብሔር ይህን ጥያቄ የተጠቀመው እስራኤል ለብዝበዛ መዳረግ እንዳልነበረባት ለማመልከት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ስለዚህ ለብዝበዛ መዳረግ አልነበረበትም፡፡” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ታዲያ ስለምን ለብዝበዛ ተዳረገ?",
"body": "እዚህ ላይ “ለብዝበዛ ተዳረገ” የሚለው ሀረግ ተጠቂ መሆንና ወደሌላ አገር ምርኮኛ ሆኖ መወሰድን የሚወክል ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ታዲያ እስራኤል እንደ ምርኮኛ ወደሌላ የተወሰደው ለምንድን ነው” ወይም “ታዲያ የእስራኤል ጠላቶች እስራኤልን እንደ ምርኮኛ ለምን ወሰዱት” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚእስለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "የአንበሳ ደቦሎች በእርሱ ላይ አገሡ፥ ብዙ ድምጽም አሰሙ",
"body": "እግዚአብሔር እስራኤልን ስላጠቋት የእስራኤል ጠላቶች ሲናገር ጠላቶቿ የሚያገሱና እስራኤልን የሚያጠቁ አንበሶች እንደሆኑ አድርጎ ገልጿቸዋል፡፡ (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "ምድሩንም ባድማ አድርገውታል",
"body": "ይህ ሕዝቡ ምድሩን ሲያዩ የሚያስፈራ እንደሆነ እስኪሰማቸው ድረስ ምድሩን ለማጥፋታቸው የሚወክል ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የእስራኤልን ምድር አፈራራሱ” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "የአንበሳ ደቦሎች አገሱ",
"body": "ማግሳት የዱር እንስሳት ሲያጠቁ የሚያሰሙት እጅግ በጣም ከፍ ያለ ጩኸት ነው፡፡"
},
{
"title": "ከተሞቹ ተቃጠሉ፣ የሚቀመጥባቸው ማንም የለም",
"body": "ይህ በገቢር ቅርጽ ሊገለጽ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የእስራኤልን ከተሞች አቃጠሉአቸው፣ አሁን በእነርሱ ውስጥ የሚኖር ማንም ሰው የለም” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "የሚቀመጥባቸው",
"body": "በአንድ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች"
},
{
"title": "ሜምፎስና ጣፍናስ",
"body": "እነዚህ በግብጽ ምድር የሚገኙ የሁለት ከተሞች ስሞች ናቸው፡፡ (ስሞች እንዴት ይተረጎማሉ የሚለውን ይመልከቱ)"
},
{
"title": "አናትሽን ይላጩሻል",
"body": "ግብጻውያን የባርያዎቻቸውን ራስ ይላጩ ነበር፣ ይህን የሚያደርጉት የባርያ ምልክት ለመስጠት ነው፡፡ "
},
{
"title": "አናትሽን ይላጩሻል",
"body": "አንዳንድ ትርጉሞች የዕብራይስጡን ጥቅስ “አናትሽን ሰንጥቀውሻል፡፡”"
},
{
"title": "በመንገድ የሚመራሽን፣ እግዚአብሔር አምላክሽን በመተውሽ፣ ይህን በራስሽ ላይ አላመጣሽምን?",
"body": "እግዚአብሔር ይህን ጥያቄ የተጠቀመው ጠላቶቻቸው ያጠቋቸው በራሳቸው ጥፋት እንደሆነ እስራኤልን ለማስታወስ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አምላካችሁ እግዚአብሔር በመንገድ ሁሉ እየመራችሁ ሳለ እናንተ ግን እርሱን በመተዋችሁ ይህን በራሳችሁ ላይ አመጣችሁ፡፡” (መልስ የማይሰጥባቸው ጥያቄዎች የሚለውን ይመልከቱ)"
}
]