\v 18 በዚያን ቀን ከዱር አራዊት፥ ከሰማይ አእዋፍና በምድር ከሚንቀሳቀሱት ነገሮች ጋር ቃል ኪዳን አደርግላቸዋለሁ። ቀስትን፥ ሰይፍንና ጦርነትን ክምድሪቱ አስወግዳለሁ፥ በሰላምም እንድትጋደሙ አደርጋችኋለሁ።