\c 13 \v 1 «ኤፍሬም በተናገረ ጊዜ መንቀጥቀጥ ነበረ። በእስራኤል መካከል ራሱን ከፍ ከፍ አደረገ፥ ነገር ግን በአልን በማምለኩ በደለኛ ሆነ፥ ሞተም። \v 2 አሁንም አብዝተው ኃጢአት ሠሩ። ከብራቸው የተቀረጸ ምስል ሠሩ፥ ጣዖታት በሚቻለው መጠን በጥበብ ተሠርተዋል፥ ሁሉም የባለ ሙያ ሥራ ናቸው። ሕዝቡ ስለ እነርሱ እንዲህ ይላሉ፦ 'እነዚህ የሚሠው ሰዎች ጥጃዎችን ይስማሉ።'