\c 5 \v 1 በእናንተ በሁላችሁ ላይ ፍርድ እየመጣ ነውና፤ ካህናት ሆይ ይህን ስሙ! የእስራኤል ቤት ሆይ ልብ በሉ! የንጉሡ ቤት ሆይ ስሙ! እናንተ፥ በምጽጳ ላይ ወጥመድ፥ በታቦርም ላይ የተዘረጋ መረብ ሆናችኋል። \v 2 ዓመጸኞች በማረድ እጅግ በርትተዋል፥ ሁሉንም እገራቸዋለሁ።