\c 4 \v 1 የእስራኤል ሕዝብ ሆይ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ። እውነተኛነት፥ ለኪዳን ታማኝነት፥ እግዚአብሔርን ማወቅ በምድሪቱ የለምና እግዚ አብሔር በምድሪቱ ከሚኖሩ ጋር ሙግት አለው። \v 2 መርገም፥ መዋሽት፥ መግደል፥ መስረቅና ማመንዘር በዚያ አለ። ሕዝቡ ስምምነቶችን ሁሉ ያፈርሳሉ፥ ሳያቋርጡ ደም ይፋሰሳሉ።