\c 41 \v 1 ከዚያም ሰውዬው ወደ መቅደሱም ቅዱስ ስፍራ አገባኝ፥ የግንቡንም አዕማድ ወርድ በዚህ ወገን ስድስት ክንድ በዚያም ወገን ስድስት ክንድ አድርጎ ለካ። \v 2 የመግቢያውም ወርድ አሥር ክንድ ነበረ፥ የመግቢያውም መቃኖች በዚህ ወገን አምስት ክንድ በዚያም ወገን አምስት ክንድ ነበሩ።ቀጥሎም ሰውዬው ቅዱስ ስፍራውን ርዝመቱ አርባ ክንድ ወርዱም ሀያ ክንድአድርጎ ለካ።