\v 13 ሳባና ድዳን የተርሴስም ነጋዴዎች ከወጣት ጦረኞቻችው ሁሉ ጋር እንዲህ ይሉሀል፥ 'የመጣኸው ምርኮን ለመማረክ ነው? ጦርህን የሰበሰብከው ብዝበዛን ለመበዝበዝ ብርንና ወርቅንስ ለመውሰድ፥ ከብትንና ዕቃንስ ለመውሰድ እጅግም ብዙ ምርኮ ለመማረክ ነው?'።