\v 15 ወተትና ማርም ወደምታፈስሰው የምድር ሁሉ ጌጥ ወደምትሆን ልሰጣቸው ወዳሰብኩት ምድር አላመጣቸውም ብዬ በምድረ በዳ ማልሁባቸው። \v 16 ይህን የማልኩት ልባቸው ጣዖቶቻቸውን ስለተከተሉ፥ ፍርዴንም ስለጣሉ ፥ በሥርዓቴም ስላልሄዱ፥ ሰንበታቴንም ስላረከሱ ነው። \v 17 ነገር ግን ዓይኔ ራራችላቸው እኔም አላጠፋኋቸውም፥ በምድረ በዳም ፈጽሜ አልፈጀኋቸውም።