am_ezk_text_ulb/20/08.txt

1 line
595 B
Plaintext

\v 8 እነርሱ ግን ዐመፁብኝ ሊሰሙኝም አልወደዱም። እያንዳንዱ ርኩስ ነገሮችን ከአይኑ ፊት አላስወገደም የግብጽንም ጣዖታት አልተወም በዚህም ጊዜ። በግብጽ ምድር መካከል ቍጣዬን ልፈጽምባቸው መዓቴንም ላፈስባቸው ወሰንኩ። \v 9 ነገር ግን በመካከላቸው በሚኖሩበት ህዝብ መካከል እንዳይረክስ ስለ ስሜ ሰራሁ። ከግብጽ ምድር በማውጣት ራሴን በአይናቸው ፊት ገለጥኩላቸው።