\v 7 ታላቅ ክንፍና ብዙ ላባም ያለው ሌላ ታላቅ ንስር ነበረ። እነሆም፥ ውሀ ያጠጣው ዘንድ ይህ ወይን ሥሩን ወደ እርሱ አዘነበለ አረጉንም ከተተከለበት ከመደቡ ወደ እርሱ ሰደደ። \v 8 አረግም ያወጣ ፍሬም ያፈራ የከበረም ወይን እንዲሆን በመልካም ላይ በብዙም ውኃ አጠገብ ተተክሎ ነበር።