\v 5 ከዚያም ምድር ዘር ወሰደ በፍሬያማ እርሻም ተከለው። በብዙም ውኃ አጠገብ እንደ አኻያ ዛፍ አኖረው። \v 6 በበቀለም ጊዜ ቁመቱ ያጠረ አረጉም ወደ እርሱ የሚመለስ ሥሩም በበታቹ የነበረ ሰፊ ወይን ሆነ።