\v 6 እኔ ግን በአንቺ ዘንድ ባለፍሁ ጊዜ በደምሽም ውስጥ ተለውሰሽ አየሁ፤ ስለዚህም በደምሽ እንዳለሽ "በሕይወት ኑሪ!" አልሁሽ። \v 7 በእርሻ ላይ እንዳለ ቡቃያ አሳደግሁሽ። አንቺም አደግሽ ታላቅም ሆንሽ፥ በእጅጉም አጌጥሽ። ጡቶችሽም አጐጠጐጡ ጠጕርሽም አደገ፥ ነገር ግን ዕርቃንሽን ሆነሽ፥ ተራቍተሽም ነበር።