ንጉሡም ድምፁን ከፍ አድርጎ አስማተኞችን፣ ኮከብ ቆጣሪዎችንና መተተኞችን እንዲያስገቡለት አዘዘ፤ ለባቢሎናውያኑ ጠቢባን ንጉሡ እንዲህ አላቸው፤ “ይህን ጽሕፈት አንብቦ ትርጉሙን የሚነግረኝን ሐምራዊ መጎናጸፊያ አለብሰዋለሁ፤ የወርቅ ሐብልም በዐንገቱ አጠልቅለታለሁ፤ በመንግሥቴም ሥልጣን ሦስተኛውን ማዕረግ ይይዛል።”