\v 4 እኔ ናቡከደነፆር በቤቴ ደስ ብሎኝ፥ በቤተ መንግሥቴም በብልጽግና ፍሥሐ እያደረግሁ እኖር ነበር። \v 5 ነገር ግን የአስፈራኝን ሕልም አለምሁ፤ ተኝቼም ሳለሁ ያየኋቸው ምስሎችና የአእምሮዬ ራዕዮች አወኩኝ። \v 6 ስለዚህ ሕልሙን ይተረጉሙልኝ ዘንድ የባቢሎንን ጠቢባን ሁሉ በፊቴ እንዲያቀርቧቸው ትእዛዝ አወጣሁ።