\v 14 በሕይወት ትኖሩ ዘንድ መልካሙን ፈልጉ፥ክፉውንም አይደለም። እርሱም እንደተናገራችሁት ነውና፥የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር በእርግጥ ከእናንተ ጋር ይሆናል። \v 15 ክፉውን ጥሉ፥መልካሙንም ውደዱ፥በከተማይቱም በር ፍትሕን አጽኑ፤ምናልባት የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር ለዮሴፍ ቅሬታ ይራራ ይሆናል።