\v 3 እግዚአብሔር ደግሞ ለእኔ እንደዚህ አለኝ፡- ‹‹ስላደረጓቸው ብዙ ኃጢአቶች የአራምን ዋና ከተማ የደማስቆስን ሕዝብ እቀጣለሁ፤ በገለዓድ አውራጃ በሚኖሩ ሕዝቦች ላይ ስለፈጸሙት ክፉ ተግባር እነርሱን ለመቅጣት የወሰንሁትን ውሳኔ አልለውጥም፡፡
\v 4 ንጉሥ አዛሄል ገንብቶ ይኖርበት የነበረውን ቤተ መንግሥት፣ ልጁ ቤን ሐዳድም ይኖበት የነበረውን ምሽግ በእሳት አቃጥላለሁ፡፡