\v 3 የቆጵሮስን ደሴት ከሩቅ ባየን ጊዜ፣ ወደ ግራ ትተናት በባሕር ወደ ሶርያ ተጓዝን፤ መርከብዋ ጭነቷን የምታራግፈው በዚያ ስለ ነበር፣ ጢሮስ ወደብ ላይ ደረስን። \v 4 ደቀ መዛሙርቱን ካገኘን በኋላም፣ በዚያ ሰባት ቀን ተቀመጥን። እነዚህም ደቀ መዛሙርት ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዳይገባ በመንፈስ ቅዱስ ከለከሉት።