diff --git a/19/30.txt b/19/30.txt new file mode 100644 index 0000000..f16d4ba --- /dev/null +++ b/19/30.txt @@ -0,0 +1 @@ +\v 30 \v 31 \v 32 30 ጳውሎስ ወደ ሕዝቡ ጋጋታ ሊደባለቅ ፈልጎ ነበር፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ከለከሉት። 31 ደግሞም፣የጳውሎስ ወዳጆች የነበሩ አንዳንድ የአካባቢ ሹሞች ጳውሎስ ወደ ቲያትር ማሳያ ቦታ እንዳይገባ መልእክት ላኩበት። 32 ሕዝቡ ሁሉ ግራ ስለ ተጋባ፣ አንዳንዶቹ ስለ አንድ ነገር ሲጮኹ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ ስለ ሌላ ነገር ይጮኹ ነበር። አብዛኛዎቹ ደግሞ ለምን ተሰብስበው እንደ ወጡ እንኳ አያውቁም ነበር። \ No newline at end of file diff --git a/19/33.txt b/19/33.txt new file mode 100644 index 0000000..73db7f8 --- /dev/null +++ b/19/33.txt @@ -0,0 +1 @@ +\v 33 \v 34 33 አይሁድም እስክንድርን ገፋፍተው ወደ ሕዝቡ ፊት አወጡት። እስክንድርም ለሕዝቡ በእጅ ምልክት እያሳየ ሊያስረዳቸው ሞከረ። 34 ሕዝቡም አይሁዳዊ መሆኑን በተረዱ ጊዜ፣ “የኤፌሶንዋ ዲያና ታላቅ ናት” እያሉ ለሁለት ሰዓት ያህል ሁሉም በአንድ ድምፅ ጮኹ። \ No newline at end of file diff --git a/19/35.txt b/19/35.txt new file mode 100644 index 0000000..aae8c66 --- /dev/null +++ b/19/35.txt @@ -0,0 +1 @@ +\v 35 \v 36 \v 37 35 የከተማዋ ፀሐፊም ሕዝቡን ዝም ካሰኘ በኋላ፣ እንዲህ አለ፤ “እናንተ የኤፌሶን ሰዎች ሆይ፤ የኤፌሶን ከተማ የታላቅዋ ዲያናና ከሰማይ ለወረደው ምስል ቤተ መቅደስ ጠባቂ መሆንዋን የማያውቅ የትኛው ሰው ነው? 36 እንግዲህ ይህ የማይካድ ነገር መሆኑ ከታያችሁ፣ ጸጥ ልትሉና አንዳች ነገር በችኮላ እንዳታደርጉ ይገባል፤ 37 ምክንያቱም ቤተ መቅደስን ያልሰረቁ ወይም ሌቦችና አማልክታችንን ያልሰደቡ እነዚህን ሰዎች ወደዚህ ፍርድ ቤት አምጥታችኋል። \ No newline at end of file