Tue Jun 26 2018 13:31:46 GMT+0300 (E. Africa Standard Time)
This commit is contained in:
parent
55fd53e55d
commit
fdfdcf3371
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 13 ናቡከደነፆርም በቤተ መቅደስና በቤተ መንግሥት የነበረውን ሀብት ሁሉ ጠራርጎ ወደ ባቢሎን ወሰደ፡፡ ቀደም ሲል እግዚብሔር በተናገውም ቃል መሠረት ንጉሥ ሰሎሞን ለእግዚብሔር ቤተ መቅደስ አሠርቶት የነበረውን የወርቅ ዕቃ ሁሉ ሰባበረ፡፡ \v 14 ናቡከደነፆር የኢየሩሳሌምን ሕዝብ ልዑላን፣ መሳፍንቱን ሁሉና ሌሎችንም ታላላቅ ሰዎች ጭምር በድምሩ ዐሥር ሺህ ሰዎች ማርኮ ወሰደ፡፡ ከእርሱም ጋር የዕደ ጥበብ ዐዋቂዎችንና የብረት አንጣሪዎችን ሁሉ ወሰደ፤ በይሁዳ እንዲቀሩ ያደረገው የመጨረሻዎቹን ድኾች ብቻ ነበር፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 15 ናቡከደነፆር ዮአኪንን አስሮ ከእናቱ፣ ከሚስቶቹ፣ ከአገልጋዮቹ፣ ከባለሥልጣኖቹና ከይሁዳ ታላላቅ ሰዎች ጋር በአንድነት ሰብስቦ ወደ ባቢሎን ወሰዳቸው፡፡ \v 16 የባቢሎን ንጉሥ ሰባት ሺህ ለውጊያ ብቃት ያላቸው ወንዶችን እንዲሁም አንድ ሺህ ብረት ቀጥቃጮችንና ዕደ ጥበበኞችን ወደ ባቢሎን ወሰደ፡፡ \v 17 ናቡከደነፆርም በዮአኪን ምትክ ማታንያ ተብሎ የሚጠራውን የዮአኪንን አጎት በይሁዳ አነገሠው፤ ስሙንም በመለወጥ ሴዴቅያስ ብሎ ጠራው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 18 ሴዴቅያስ በይሁዳ በነገሠ ጊዜ ዕድሜው ሃያ አንድ ዓመት ነበር፡፡ በኢየሩሳሌም ዐሥራ አንድ ዓመት ገዛ፡፡ እናቱም አሚጣል ተብላ የምትጠራ የልብና ከተማ ተወላጅ የነበረው የኤርምያስ ልጅ ነበረች፡፡ \v 19 እርሱም አባቱ ኢዮአቄም ባደረገው ዓይነት በእግዚአብሔር ክፉ አደረገ፡፡ \v 20 እግዚብሔር ከፊቱ እስኪያስወግዳቸው ድረስ በኢየሩሳሌምና በይሁዳ ሕዝብ ተቆጥቶ ነበር፡፡ ሴዴቅያስም በባቢሎን ንጉሥ ላይ ዐመፀ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\c 25 \v 1 ናቡከደነፆር መላው ሠራዊቱን አስከትቶ ሴዴቅያስ በነገሠ በዘጠነኛው ዓመት፣ ዐሥረኛው ወር በገባ በዐሥረኛው ቀን ከባቢሎን መጥቶ በኢየሩሳሌም ላይ ዘመተ፤ ወታደሮቹ ከከተማይቱ ውጪ ሰፍረው ዙሪያውን የሚከብብ አጥር ሠሩ፡፡ \v 2 ከበባው እስከ ሴዴቅያስ ዐሥራ አንደኛ ዓመት ዘመነ መንግሥት ድረስ ቆየ፡፡ \v 3 ስለዚህም አራተኛው ወር በገባ በዘጠነኛው ቀን ራቡ በጣም ስለ ጸና ሕዝቡ የሚመገበው እንዳችም ምግብ አልነበረም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 4 ከዚያም የከተማይቱ ቅጥር ተጣሰ፤ የባቢሎን ወታደሮች ከተማይቱን ዙሪያውን ከበው በመያዝ ቢጠብቁም እንኳ የይሁዳ ንጉሥ ወታደሮች በሌሊት አምልጠው ወጡ፤ ወደ ንጉሡ የአትክልት ቦታ ከሚያስገባው መንገድ ተነሥተው ሁለቱን ቅጥሮች በሚያያይዘው የቅጥር በር በኩል በማለፍ ወደ ዮርዳኖስ ሸለቆ አቅጣጫ ሸሹ፡፡ \v 5 ነገር ግን የከላደውያን ሠራዊት ንጉሥ ሴዴቅያስን በኢያሪኮ አጠገብ በሚገኝ ሜዳ ላይ አሳደደው፡፡ ወታደሮቹም ጥለውት ሸሹ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 6 ሴዴቅያስ ተይዞ በሪብላ ከተማ ወደሚገኘው ወደ ባቢሎን ንጉሥ ተወሰደ፡፡ በዚያም ፍርድ አስተላለፉበት፡፡ \v 7 ሴዴቅያስም ዐይኑ እያየ ልጆቹ በፊቱ ታረዱ፡፡ ከዚህም በኋላ ናቡከደነፆር የሴዴቅያስን ዐይኖች አውጥቶ አሳወረው፤ እጆቹንም በነሐስ ሰንሰለት አስሮ ወደ ባቢሎን ወሰደው፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 8 ናቡከደነፃር በባቢሎን በነገሠ በዐሥራ ዘጠነኛው ዓመት፣ አምስተኛው ወር በገባ በሰባተኛው ቀን ናቡዘረዳን ተብሎ የሚጠራው የናቡከደነፆር የክብር ዘበኞቹ አዛዥ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ \v 9 እርሱም ቤተ መቅደሱን፣ ቤተ መንግሥቱን፣ በከተማው የሚኖሩትን የታላላቅ ሰዎች ቤት፣ በከተማው ውስጥ የሚገኙትንም ሌሎች ቤቶች ሁሉ በእሳት አቃጠለ፡፡ \v 10 በክብር ዘቡ አዛዥ ሥር የነበሩት የባቢሎናውያን ወታደሮች በሙሉ የኢየሩሳሌምን ዙሪያ አጥር ደመሰሱ፡፡
|
|
@ -354,6 +354,13 @@
|
|||
"24-07",
|
||||
"24-08",
|
||||
"24-10",
|
||||
"25-title"
|
||||
"24-13",
|
||||
"24-15",
|
||||
"24-18",
|
||||
"25-title",
|
||||
"25-01",
|
||||
"25-04",
|
||||
"25-06",
|
||||
"25-08"
|
||||
]
|
||||
}
|
Loading…
Reference in New Issue