|
\c 21 \v 1 ከጥቂት ጊዜ በኋላ ናቡቴ ተብሎ የሚጠራ ሰው በኢይዝራኤል በሚገኘው በንጉሥ አክዓብ ቤተ መንግሥት አጠገብ የራሱ ርስት የሆነ አንድ የወይን ተክል ቦታ ነበረው፡፡ \v 2 አንድ ቀን አክዓብ ናቡቴን የወይን ተክል ቦታህን ስጠኝ፤ በቤተ መንግሥቴ አጠገብ ስለ ሆነ የአትክልት ቦታ ላደርገው እፈልጋለሁ፤ በምትኩ ከእርሱ የተሻለ የወይን ተክል ቦታ እሰጥሃለሁ፤ ልትሸጠው ብትፈልግም የተሻለ ዋጋ እከፍልሃለሁ አለው፡፡ |