|
\c 14 \v 1 ያን ጊዜ የኢዮርብዓም ልጅ አቢያ በጣም ታመመ፡፡ \v 2 ኢዮርብዓም ለሚስቱ እንዲህ አላት “ሚስቴ መሆንሽን ማንም እንዳያውቅ እራስሽን በአለባበስሽ ደብቂ፡፡ ከዚያም እኔ ንጉሥ እንደምሆን የተናገረው ነቢይ አኪያ ወደሚኖርበት ወደ ሴሎ ከተማ ሂጁ፡፡ \v 3 አሥር እንጀራ ጥቂት ሙልሙል ዳቦና አንድ ገንቦ ማር ውሰጂላት ያን ስጪውና ስለልጃችን ንገሪው እና ምን እንደሚደርስበት ይነግርሻል፡፡” |