\v 4 ኃጢያትን የሚሠራ ሁሉ ዐመጽን ያደርጋል፣ ኃጢአትም ዐመጽ ነው፡፡ \v 5 ኃጢያትን ለማስወገድ ክርስቶስ እንደተገለፀ ታውቃላችሁ፣ በእርሱም ኃጢያት የለም፡፡ \v 6 በእርሱ የሚኖር ኃጢያት አያደርግም፡፡ ኃጢያት የሚያደርግ እርሱን አላየውም ወይም አላወቀውም፡፡