እነዚህን ነገሮች የጻፍኩአቸው ላሳፍራችሁ ሳይሆን እንደ ተወደዱ ልጆቼ አድርጌ እንድትታርሙ ልገስጻችሁ ነው። በክርስቶስ ብዙ እልፍ አዕላፋት አሳዳጊዎች ቢኖሩአችሁ እንኳ ብዙ አባቶች የሉአችሁም፤ እኔ ግን በኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል አማካይነት አባታችሁ ሆኜዋለሁ። እንግዲህ እኔን የምትመስሉ እንድትሆኑ አሳስባችኋለሁ።