ወንድሞችና እህቶች ሆይ፤ በእናንተ ያለውን የእግዚአብሔርን ጥሪ ተመልከቱ፤ብዙዎቻችሁ በሰው መለኪያ ጥበበኞች አልነበራችሁም፤ ብዙዎቻችሁ ኃያላን አልነበራችሁም፤ ብዙዎቻችሁም ባላባቶች አልነበራችሁም። ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን ያሳፍር ዘንድ የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ። ብርቱንም ነገር ለማሳፈር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ።