39 የዑላ ወንዶች ልጆች ኤራ፣ ሐኒኤል፣ ሪጽያ ናቸው፡፡ 40 እነዚህ ሁሉ የአሴር ዘሮች ሲሆኑ፣ ሁሉም የቤተ ሰብ አለቆች ነበሩ፤ ጎበዝ መሪዎችና ጥሩ ተዋጊዎችም ነበሩ፡፡ በትውልድ መዝገባቸው እንደ ተጻፈው ሰራዊቱ ውስጥ ለማገልገል ብቁ የሆኑ ሃያ ስድስት ሺህ ሰዎች ነበሩዋቸው፡፡