# የመጽሐፍ ቅዱስ ጊዜ፤ ትጋት መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን፣ “ትጋት” ይባል የነበረው አንድ የከተማ ጠባቂ ወይም ዘበኛ ጠላት ከሚሰነዝረው የትኛውም ጥቃት ለመጠበቅ ግዳጅ ላይ የሚሆንበት የሌሊቱ ጊዜ ነው። * በብሉይ ኪዳን ዘመን እስራኤላውያን፣ “ጅማሬ” (ከፀሐይ መጥለቅ እስከ ሌሊቱ 4 ሰዓት)፣ “መካከለኛ” (ክሌሊቱ 4 እስከ 8 ሰዓት) እና “ጠዋት” (ከ8 ሰዓት እስከ ፀሐይ መውጣት) በመባል የሚጠሩ ሦስት ትጋቶች ነበሩዋቸው። * በአዲስ ኪዳን ዘመን፣ አይሁድ የሮማውያንን ሥርዐት ስለ ተከተሉ “መጀመሪያ” (ከፀሐይ መጥለቅ እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት)፣ “ሁለተኛ” (ከ3 ሰዓት እስከ 12 ሰዓት እኩለ ሌሊት)፣ “ሦስተኛ” (ከ6 እስከ 9) እና፣ “አራተኛ” (9 ሰዓት እስከ ፀሐይ መውጣት ድረስ) አራት ትጋቶች ነበሯቸው። * እየተነገረ ባለው ትጋት መሠረት እነዚህም፣ “በጣም ሲመሽ” ወይም፣ “ዕኩለ ሌሊት” ወይም፣ “ጠዋት ማለዳ” በተሰኘ አጠቃላይ ቃሎች መተርጎም ይችላሉ።