# ሰሎሞን ሰሎሞን ከንጉሥ ዳዊት ልጆች አንዱ ነበር። የእናቱ ስም ቤርሳቤህ ይባል ነበር * ሰሎሞን በነገሠ ጊዜ ከእርሱ ማንኛውንም ነገር እንዲለምን እግዚአብሔር ነግሮት ነበር። ስለዚህም ሰሎሞን ሕዝቡን በአግባቡና በፍትሕ ማስተዳደር የሚችልበት ጥበብ እንዲሰጠው ጠየቀ። ሰሎሞን በቀረበው ጥያቄ እግዚአብሔር ደስ ስለተሰኘ ጥበብንና ብዙ ሀብትን ሰጠው * ሰሎሞን አባቱ ዳዊት ለመሥራት ፈልጎ የነበረውን በኢየሩሳሌም የነበረውን የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ሠራ * ምንም እንኳ ሰሎሞን በመጀመሪያው የአገዛዝ ዘመኑ በጥበብ ቢያስተዳድርም፣ በኋላ ግን በመታለል ባዕድ ሴቶች አገባ፤ አማልክቶቻቸውንም ማምለክ ጀመረ * ሰሎሞን ታማኝነትን በማጉደሉ፣ ከእርሱ ሞት ብኋላ እስራኤላውያን ለሁለት መንግሥታት ተከፈሉ፤ እስራኤልና ይሁዳ። አብዛኛውን ጊዜ እነዚህ መንግሥታት እርስ በርስ ይዋጉ ነበር