28 lines
1.9 KiB
Markdown
28 lines
1.9 KiB
Markdown
# የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር
|
|
|
|
ይህንን በኢሳይያስ 1፡9 እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡
|
|
|
|
# ውብ ዘውድና የውበት አክሊል ይሆናል
|
|
|
|
እንደ እውነተኛ ንጉሣቸው ለብሰውት ለሚያከብሩት ሕዝብ እግዚአብሔር ውብ ዘውድ እንደሚሆን ተደርጎ ተነግሮአል፡፡ (ስዕላዊ ንግግር ተመልከት)
|
|
|
|
# ውብ ዘውድና የውበት አክሊል
|
|
|
|
የሁለቱም ትርጉም አንድ ነው፡፡ አት፡- "ውብ ዘውድ' (የሁለት ነገሮች ተመሳሳይነት ተመልከት)
|
|
|
|
# ሕዝብ፣ በፍርድ ወንበር ላይ ለሚቀመጥም የፍትህ መንፈስ፣ … ብርታትም
|
|
|
|
እንደ "ፍትህ' እና "ብርታት' ያሉ የነገር ስሞች በቅጽልነት እንዲገለጹ ይህ እንደገና ሊጻፍ ይችላል፡፡ አት፡- "ሕዝብ፣ እግዚአብሔር ዳኞችን ጻድቃን እንዲሆኑ ያደርጋል እንዲሁም ብርቱዎች ያደርጋቸዋል' (የነገር ስም ተመልከት)
|
|
|
|
# የፍትህ መንፈስ
|
|
|
|
የፍትህ መንፈስ ያለው ሰው የፍትሃዊነት ባሕርይ ያለውና ጻድቅ ሰው ነው፡፡ (ፈሊጣዊ ንግግር ተመልከት)
|
|
|
|
# በፍርድ ወንበር ላይ ለሚቀመጥ
|
|
|
|
ይህ ፈሊጣዊ ንግግር የዳኝነት ሥልጣን ያለው ሰው ማለት ነው፡፡ (ፈሊጣዊ ንግግር ተመልከት)
|
|
|
|
# በበራቸው ጠላቶቻቸውን ወደ ኋላ ለሚመልሱ ብርታትን
|
|
|
|
በዚህ ስፍራ "ወደ ኋላ ለሚመልሱ' የሚለው በጦርነት ለሚያሸነፉ የሚል ፈሊጣዊ ንግግር ነው፡፡ አት፡- "ጠላቶች ከተማቸውን ሲያጠቁ ጠላቶቻቸውን ያሸንፉ ዘንድ እግዚአብሔር ወታደሮቹን ብርቱዎች ያደርጋቸዋል' (ፈሊጣዊ ንግግር ተመልከት)
|