24 lines
1.6 KiB
Markdown
24 lines
1.6 KiB
Markdown
|
# ከአፋቸው ስለሚወጣው ኃጢአትና ስለ ከንፈሮቻቸው ቃል
|
||
|
|
||
|
አፍና ከንፈር ሰዎች የሚናገሩትን ነገር ይወክላል። አ.ት፡ “በሚናገሩት ኃጢአትን ስለሚያደርጉ” ወይም “በሚናገሩት የኃጢአት ንግግር ምክንያት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
|
||
|
|
||
|
# በትዕቢታቸው ይያዙ
|
||
|
|
||
|
ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “በትዕቢታቸው ምክንያት ሰዎች ይያዟቸው” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)
|
||
|
|
||
|
# ስለሚገልጹት
|
||
|
|
||
|
“ስለሚሉት”
|
||
|
|
||
|
# በቁጣ አቃጥላቸው፣ ከእንግዲህ እንዳይገኙ አቃጥላቸው
|
||
|
|
||
|
እነርሱን ሙሉ በሙሉ ማጥፋት እንደ ማቃጠል ወይም መብላት ተደርጎ ተነግሯል። አ.ት፡ “ተቆጣቸው፣ አንዳቸውም እንዳይቀሩ አድርገህ አጥፋቸው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
|
||
|
|
||
|
# በያዕቆብ
|
||
|
|
||
|
እዚህ ጋ፣ ያዕቆብ የሚያመለክተው እስራኤልን ነው። አ.ት፡ “በእስራኤል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
|
||
|
|
||
|
# እስከ ምድር ዳርቻ
|
||
|
|
||
|
“በምድር ላይ እጅግ ሩቅ እስከሆነው ቦታ እንኳን”። ይህ በምድር ላይ ሁሉን ስፍራ ይወክላል። አ.ት፡ “በምድር ላይ በሁሉም ቦታ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
|